group-telegram.com/ZenaKristos/285
Last Update:
የሕማማት የሳምንት - እሮብ
ይሁዳ ኢየሱስን አሳልፎ ለመስጠት ተስማማ
"በዚያን ጊዜ የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ። ምን ልትሰጡኝ ትወዳላችሁ እኔም አሳልፌ እሰጣችኋለሁ? እነርሱም ሠላሳ ብር መዘኑለት። ከዚያችም ሰዓት ጀምሮ አሳልፎ ሊሰጠው ምቹ ጊዜ ይሻ ነበር። "
ማቴዎስ 26:14-16
ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ከጠራበት ጊዜ ጀምሮ የነበረው የአስቆሮቱ ይሁዳ፤ ብዙ ተአምራትን፤ ብዙ ድሎችን እንዲሁም ብዙ ትምህርቶችን በኢየሱስ ዘንድ ቢያገኝም፤ ለገንዘብ ያለው ጥልቅ ፍቅር የገዛ መምህሩም እንኳን እንዲከዳ አድርጎታል። ኢየሱስ ከዚህ በፊት ሲያስተምር የገንዘብ ፍቅር የኃጢያት ሁሉ ሥር ነው ብሏል። ያንን ትምህርት የአስቆሮቱ ይሁዳ ሰምቶ ነበር፤ ቢሆንም ግን ወደ ልቡ ገብቶ እዚህ ግባ የሚባል ለውጥ ስላላመጣ፤ በኋላ ላይ የገዛ መምህሩም፣ አምላኩን እና ጌታውን በሥላሳ ብር ሊሰጥ ተስማማ። በዚህም ዘመን ብዙዎች ክርስቶስን የወደዱ መስሏቸው የገንዘብ ፍቅራቸው ከክርስቶስ ጋር አጣልቷቸው ይገኛል። ወገኖች ሆይ የገንዘብ ፍቅር ከክርስቶስ እዳይለየን በዚህ የሕማማት ጊዜ በፀሎት እና በምልጃ በእግዚአብሔር ፊት እንቅረብ። እግዚአብሔር ይርዳን። አሜን!
ድህረ ገፃችንን ይጎብኙ፡
Https://zenakristos.org/images
BY ዜና ክርስቶስ || Christ Chronicles
![](https://photo.group-telegram.com/u/cdn4.cdn-telegram.org/file/JMYVXKGiFB5ID9edcqCDgFTOL1yM1QGwZ2FPA_u42j_dnbw473QX5xOQ3Qd4qk4e99Bwuw_-ZgjM3vZGqmoHZrw8oyQc7cj6H9vJVf3fJQcIefKO81s2-Uiy7GwcedJgQiN1FTLJDLhHdycuMmZRYJuRuRLyBklU5rX_Z9mx8c9KrABEF6FxD8Ayth4vmW3rPSIRWugODT3R7_CtOS6amsbn3BTMgCHNCq5jlVDmKyPFSqdaZGLVK6MhbGrV7GpdiEl9Dm3n1D143YpYU28uO78Mm5YQmj3Ze1MRPUyreh8yM4mi6J3RH8DHPgAkh5Gb7POwvqYYQVcGe8ggJXET1w.jpg)
Share with your friend now:
group-telegram.com/ZenaKristos/285