Telegram Group & Telegram Channel
የነጻነት ፡ መዘዝ ፡ የአምልኮ ፡ ነጻነት
በበጐቹ ፡ መግቢያ ፡ ትኩሎች ፡ ዘው ፡ አሉበት
ሥርዓት ፡ የሌለበት ፡ ገደብ ፡ የሌለበት
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ለንግድ ፡ ጨረታ ፡ የወጣበት
አወይ ፡ ነጻነት ፤ አወይ ፡ ነጻነት ፤ አወይ ፡ ነጻነት

ለአምልኮ ፡ ነጻነት ፡ ሱባኤ ፡ ተገብቶ
መሰደድም ፡ ቀረ ፡ ከላይ ፡ ትዕዛዝ ፡ ወጥቶ
መግቢያ ፡ በሩ ፡ ሰፋ ፡ ሰው ፡ ተግተለተለ
እንክርዳዱ ፡ ስንዴ ፡ ተኩላው ፡ በግ ፡ መሰለ
የድል ፡ አጥቢያ ፡ አርበኛ ፡ ዘለቀ ፡ ሆ ፡ ብሎ
ውጪያዊ ፡ ምስሉን ፡ ወጉን ፡ አስተካክሎ

በየጓዳው ፡ ፈላ ፡ ቤተክርስቲያን ፡ ሰሪ
ራሱ ፡ ፈላጭ ፡ ቆራጭ ፡ ባለሚኒስትሪ
ዶክትሪኑ ፡ በዛ ፡ መድረክ ፡ ጠበበ
ጥራት ፡ ሳይሆን ፡ ብዛት ፡ ስንቱን ፡ ሰበሰበ
ግርግር ፡ እንዳይሉት ፡ ወይ ፡ ዘመነ ፡ ጥፉ
የአምልኮ ፡ ነጻነት ፡ ብለውት ፡ አረፉ

ኦሆ ፡ ኦሆ ፡ ነጻነት
ነጻነት ፡ እያሉ
ሲያሞግሱሽ ፡ ዋሉ
ጉድሽ ፡ ግን ፡ ብዛቱ
ላወቀው ፡ ለስንቱ

[አዝማች]...

መጽሃፍ ፡ ቅዱስ ፡ ኮሌጅ ፡ አጠናቅቄያለሁ
ምስክር ፡ ወረቀት ፡ ቆቤንም ፡ ጭኛለሁ
አንግዲህ ፡ የቀረኝ ፡ ሀያ ፡ ሰው ፡ ሰብስቤ
ኪሳቸው ፡ ኪሴ ፡ ነው ፡ ለወጭ ፡ ለቀለቤ
እያሉ ፡ የሚያልሙ ፡ ወንጌል ፡ ተጡዋሪዎች
ዙሪያችን ፡ ፈልተዋል ፡ ሥራ ፡ ጠላቱዎች (፪x)

ቀላዋጮች ፡ ብዙ ፡ ተንባዮች ፡ ለእንጐቻ
መረቅ ፡ ላጠጣቸው ፡ ላበላቸው ፡ ብቻ
እንደ ፡ መተተኛ ፡ እዚህ ፡ እዛ ፡ እያሉ
ቅልጥም ፡ ላገኙበት ፡ ይተነብያሉ
የነጻነት ፡ ውልዶች ፡ ስንቱን ፡ ያሞኛሉ
በግርግር ፡ መጥተው ፡ የተቀላቀሉ ፡ የተቀላቀሉ

ኦሆ ፡ ኦሆ ፡ ነጻነት
ነጻነት ፡ እያሉ
ሲያሞግሱሽ ፡ ዋሉ
ጉድሽ ፡ ግን ፡ ብዛቱ
ላወቀው ፡ ለስንቱ

[አዝማች]...

ራሱን ፡ የሚያዳንቅ ፡ አገልጋይ ፡ሞልቶናል
ሥሙን ፡ ሲያስተዋውቅ ፡ ፎቶውን ፡ አይተናል
ስብከቴ ፡ ነክቶአቸው ፡ እልፍ ፡ ሰዎች ፡ ዳኑ
አጋንንቶች ፡ ወጡ ፡ ብሎ ፡ ማጋነኑ
ራሱ ፡ እንዳደረገው ፡ በኃይል ፡ በጥበቡ
እውቁልኝ ፡ ብሎ ፡ ሥሙን ፡ ማነብነቡ (፪x)

ባለድርጂቱስ ፡ በጐ ፡ አድራጊ ፡ መሳይ
በሙት ፡ ልጆች ፡ ነጋጅ ፡ ጫና ፡ ጫንቃቸው ፡ ላይ
በድሀ ፡ ሥም ፡ ዞሮ ፡ ባከማቸው ፡ ሁሉ
ፎቁን ፡ ገንብቶበት ፡ የሚታይ ፡ ለሁሉ
ምናልባት ፡ ሲተርፈው ፡ ከርሱን ፡ ካጠገበ
ትርፍራፊው ፡ ሲቀር ፡ ድሆቹን ፡ አሰበ

ኦሆ ፡ ኦሆ ፡ ነጻነት
ነጻነት ፡ እያሉ
ሲያሞግሱሽ ፡ ዋሉ
ጉድሽ ፡ ግን ፡ ብዛቱ
ላወቀው ፡ ለስንቱ ፤ ላወቀው ፡ ለስንቱ (፪x)

ጉድሽ ፡ ግን ፡ ብዛቱ
ላወቀው ፡ ለስንቱ ፤ ላወቀው ፡ ለስንቱ (፪x)


የአምልኮ ፡ ነጻነት (Yeamleko Netsanet) - ደረጀ ፡ ከበደ

ዜና ክርስቶስ || Christ Chronicles



group-telegram.com/ZenaKristos/295
Create:
Last Update:

የነጻነት ፡ መዘዝ ፡ የአምልኮ ፡ ነጻነት
በበጐቹ ፡ መግቢያ ፡ ትኩሎች ፡ ዘው ፡ አሉበት
ሥርዓት ፡ የሌለበት ፡ ገደብ ፡ የሌለበት
የኢየሱስ ፡ ሥም ፡ ለንግድ ፡ ጨረታ ፡ የወጣበት
አወይ ፡ ነጻነት ፤ አወይ ፡ ነጻነት ፤ አወይ ፡ ነጻነት

ለአምልኮ ፡ ነጻነት ፡ ሱባኤ ፡ ተገብቶ
መሰደድም ፡ ቀረ ፡ ከላይ ፡ ትዕዛዝ ፡ ወጥቶ
መግቢያ ፡ በሩ ፡ ሰፋ ፡ ሰው ፡ ተግተለተለ
እንክርዳዱ ፡ ስንዴ ፡ ተኩላው ፡ በግ ፡ መሰለ
የድል ፡ አጥቢያ ፡ አርበኛ ፡ ዘለቀ ፡ ሆ ፡ ብሎ
ውጪያዊ ፡ ምስሉን ፡ ወጉን ፡ አስተካክሎ

በየጓዳው ፡ ፈላ ፡ ቤተክርስቲያን ፡ ሰሪ
ራሱ ፡ ፈላጭ ፡ ቆራጭ ፡ ባለሚኒስትሪ
ዶክትሪኑ ፡ በዛ ፡ መድረክ ፡ ጠበበ
ጥራት ፡ ሳይሆን ፡ ብዛት ፡ ስንቱን ፡ ሰበሰበ
ግርግር ፡ እንዳይሉት ፡ ወይ ፡ ዘመነ ፡ ጥፉ
የአምልኮ ፡ ነጻነት ፡ ብለውት ፡ አረፉ

ኦሆ ፡ ኦሆ ፡ ነጻነት
ነጻነት ፡ እያሉ
ሲያሞግሱሽ ፡ ዋሉ
ጉድሽ ፡ ግን ፡ ብዛቱ
ላወቀው ፡ ለስንቱ

[አዝማች]...

መጽሃፍ ፡ ቅዱስ ፡ ኮሌጅ ፡ አጠናቅቄያለሁ
ምስክር ፡ ወረቀት ፡ ቆቤንም ፡ ጭኛለሁ
አንግዲህ ፡ የቀረኝ ፡ ሀያ ፡ ሰው ፡ ሰብስቤ
ኪሳቸው ፡ ኪሴ ፡ ነው ፡ ለወጭ ፡ ለቀለቤ
እያሉ ፡ የሚያልሙ ፡ ወንጌል ፡ ተጡዋሪዎች
ዙሪያችን ፡ ፈልተዋል ፡ ሥራ ፡ ጠላቱዎች (፪x)

ቀላዋጮች ፡ ብዙ ፡ ተንባዮች ፡ ለእንጐቻ
መረቅ ፡ ላጠጣቸው ፡ ላበላቸው ፡ ብቻ
እንደ ፡ መተተኛ ፡ እዚህ ፡ እዛ ፡ እያሉ
ቅልጥም ፡ ላገኙበት ፡ ይተነብያሉ
የነጻነት ፡ ውልዶች ፡ ስንቱን ፡ ያሞኛሉ
በግርግር ፡ መጥተው ፡ የተቀላቀሉ ፡ የተቀላቀሉ

ኦሆ ፡ ኦሆ ፡ ነጻነት
ነጻነት ፡ እያሉ
ሲያሞግሱሽ ፡ ዋሉ
ጉድሽ ፡ ግን ፡ ብዛቱ
ላወቀው ፡ ለስንቱ

[አዝማች]...

ራሱን ፡ የሚያዳንቅ ፡ አገልጋይ ፡ሞልቶናል
ሥሙን ፡ ሲያስተዋውቅ ፡ ፎቶውን ፡ አይተናል
ስብከቴ ፡ ነክቶአቸው ፡ እልፍ ፡ ሰዎች ፡ ዳኑ
አጋንንቶች ፡ ወጡ ፡ ብሎ ፡ ማጋነኑ
ራሱ ፡ እንዳደረገው ፡ በኃይል ፡ በጥበቡ
እውቁልኝ ፡ ብሎ ፡ ሥሙን ፡ ማነብነቡ (፪x)

ባለድርጂቱስ ፡ በጐ ፡ አድራጊ ፡ መሳይ
በሙት ፡ ልጆች ፡ ነጋጅ ፡ ጫና ፡ ጫንቃቸው ፡ ላይ
በድሀ ፡ ሥም ፡ ዞሮ ፡ ባከማቸው ፡ ሁሉ
ፎቁን ፡ ገንብቶበት ፡ የሚታይ ፡ ለሁሉ
ምናልባት ፡ ሲተርፈው ፡ ከርሱን ፡ ካጠገበ
ትርፍራፊው ፡ ሲቀር ፡ ድሆቹን ፡ አሰበ

ኦሆ ፡ ኦሆ ፡ ነጻነት
ነጻነት ፡ እያሉ
ሲያሞግሱሽ ፡ ዋሉ
ጉድሽ ፡ ግን ፡ ብዛቱ
ላወቀው ፡ ለስንቱ ፤ ላወቀው ፡ ለስንቱ (፪x)

ጉድሽ ፡ ግን ፡ ብዛቱ
ላወቀው ፡ ለስንቱ ፤ ላወቀው ፡ ለስንቱ (፪x)


የአምልኮ ፡ ነጻነት (Yeamleko Netsanet) - ደረጀ ፡ ከበደ

ዜና ክርስቶስ || Christ Chronicles

BY ዜና ክርስቶስ || Christ Chronicles




Share with your friend now:
group-telegram.com/ZenaKristos/295

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Asked about its stance on disinformation, Telegram spokesperson Remi Vaughn told AFP: "As noted by our CEO, the sheer volume of information being shared on channels makes it extremely difficult to verify, so it's important that users double-check what they read." I want a secure messaging app, should I use Telegram? So, uh, whenever I hear about Telegram, it’s always in relation to something bad. What gives? But Telegram says people want to keep their chat history when they get a new phone, and they like having a data backup that will sync their chats across multiple devices. And that is why they let people choose whether they want their messages to be encrypted or not. When not turned on, though, chats are stored on Telegram's services, which are scattered throughout the world. But it has "disclosed 0 bytes of user data to third parties, including governments," Telegram states on its website. Founder Pavel Durov says tech is meant to set you free
from us


Telegram ዜና ክርስቶስ || Christ Chronicles
FROM American