Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-93253-93254-93255-93256-93257-93258-93259-93260-93261-93262-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/93260 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ በተመሳሳይ ሰዓት እንደሚካሄድ ተገለጸ።

ይህንን የገለጸው አዘጋጁ የኢትዮጵያ ጃንደረባ ትውልድ / ኢጃት ማኅበር ነው።

የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት ምክንያት በማድረግ የሚዘጋጀው ይህ የዝማሬ መርሐግብር በበዓሉ ዋዜማ ታኅሣሥ 28/ 2017 ዓ/ም ይካሄዳል።

በአዲስ አበባ ከተማ የዝማሬ መርሐግብሩ አምና በተካሄደበት በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል (ቦሌ መድኃኔዓለም) እንደሚካሄድ ነው አዘጋጆቹ ያሳወቁት።

" የጌታችንን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት በዝማሬ እናክብር " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የልደት በዓልን ዋዜማ በቤተክርስቲያን ተገኝተው በዝማሬ እንዲያከብሩ ተብሏል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ አዘጋጆቹ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ካዘጋጁት " የአእላፋት ዝማሬ  / The Melody of Myriads " መርሐግብር ውጭ ሌላ እንዳላዘጋጁ እንዲሁም ለዚህ መርሐግብር ተብሎ የሚደረግ ምዝገባም እንደሌለና ምዕመኑ ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ  ጥሪ አቅርበዋል።

ባለፈው ዓመት በአዲስ አበባ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል በተካሄደው " የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኦርቶዶክሳዊ ወጣት የልደት ዋዜማን በዝማሬና በፀሎት ተቀብሎ ነበር።

መርሐግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትና ብፁአን አባቶች ተገኝተው እንደነበር አይዘነጋም።

ከመርሐግብሩ ቀደም ብሎ ምዕመናን በተለይም ወጣቶች የተዘጋጁ መዝሙሮችን አጥንተው እንዲመጡ መዝሙሮቹ በኦንላይን ሲሰራጩ ነበር።

ዘንድሮም በተመሳሳይ ለመርሃግብሩ የተዘጋጁ መዝሙሮች በማኅበሩ  የማህበራዊ ሚዲያዎች (Janderbaw Media Youtube) ተጭነው ምዕመኑ ጋር እንዲዳረሱ እየተደረገ ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93260
Create:
Last Update:

" የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ በተመሳሳይ ሰዓት እንደሚካሄድ ተገለጸ።

ይህንን የገለጸው አዘጋጁ የኢትዮጵያ ጃንደረባ ትውልድ / ኢጃት ማኅበር ነው።

የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት ምክንያት በማድረግ የሚዘጋጀው ይህ የዝማሬ መርሐግብር በበዓሉ ዋዜማ ታኅሣሥ 28/ 2017 ዓ/ም ይካሄዳል።

በአዲስ አበባ ከተማ የዝማሬ መርሐግብሩ አምና በተካሄደበት በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል (ቦሌ መድኃኔዓለም) እንደሚካሄድ ነው አዘጋጆቹ ያሳወቁት።

" የጌታችንን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት በዝማሬ እናክብር " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የልደት በዓልን ዋዜማ በቤተክርስቲያን ተገኝተው በዝማሬ እንዲያከብሩ ተብሏል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ አዘጋጆቹ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ካዘጋጁት " የአእላፋት ዝማሬ  / The Melody of Myriads " መርሐግብር ውጭ ሌላ እንዳላዘጋጁ እንዲሁም ለዚህ መርሐግብር ተብሎ የሚደረግ ምዝገባም እንደሌለና ምዕመኑ ከሀሰተኛ መረጃዎች ራሱን እንዲጠብቅ  ጥሪ አቅርበዋል።

ባለፈው ዓመት በአዲስ አበባ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል በተካሄደው " የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኦርቶዶክሳዊ ወጣት የልደት ዋዜማን በዝማሬና በፀሎት ተቀብሎ ነበር።

መርሐግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትና ብፁአን አባቶች ተገኝተው እንደነበር አይዘነጋም።

ከመርሐግብሩ ቀደም ብሎ ምዕመናን በተለይም ወጣቶች የተዘጋጁ መዝሙሮችን አጥንተው እንዲመጡ መዝሙሮቹ በኦንላይን ሲሰራጩ ነበር።

ዘንድሮም በተመሳሳይ ለመርሃግብሩ የተዘጋጁ መዝሙሮች በማኅበሩ  የማህበራዊ ሚዲያዎች (Janderbaw Media Youtube) ተጭነው ምዕመኑ ጋር እንዲዳረሱ እየተደረገ ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA














Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93260

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In a statement, the regulator said the search and seizure operation was carried out against seven individuals and one corporate entity at multiple locations in Ahmedabad and Bhavnagar in Gujarat, Neemuch in Madhya Pradesh, Delhi, and Mumbai. "And that set off kind of a battle royale for control of the platform that Durov eventually lost," said Nathalie Maréchal of the Washington advocacy group Ranking Digital Rights. Although some channels have been removed, the curation process is considered opaque and insufficient by analysts. Telegram, which does little policing of its content, has also became a hub for Russian propaganda and misinformation. Many pro-Kremlin channels have become popular, alongside accounts of journalists and other independent observers. Founder Pavel Durov says tech is meant to set you free
from ar


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American