Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

🔴 “ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን ” - ሙስሊም ተማሪዎች

🔵 “ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማትን አስተዳደርና መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” - ዲላ ዩኒቨርሲቲ 

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ እንዳይለብሱ በመከልከላቸው ከትምህርታቸው እየተስተጓጎሉ በመሆኑ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጠንከር ያለ ስሞታ አቅርበዋል።

የተማሪዎቹ ዝርዝር ስሞታ ምንድን ነው ?

“ ኒቃብና ጥቁር ማስክ እንዳንለብስ ነው የተከለከልነው። ክልከላው የጀመረው ከአንድ ወር በፊት ነበር። በዚህም ማመልከቻ አስገብተን ነበር መልበስ እንዲፈቀድልን። ሆኖም ግን ምላሽ ሳይሰጠን ቆዬ።

ትምህርታችን በስርዓት እንዳንከታተል አስተጓጎሉን። ቅዳሜ፣ አንዲት እህት ማስክ አድርጋ፣ ሂጃብ ለብሳ በምትገባበት ወቅት ኦዲያ ካምፓስ በሁለቱም በሮች እንዳትገባ ከልክለዋታል።

እንዲያውም ወንዶቹ የግቢው ጥበቆች አስፈራርተው ፊቷን አስከፍተዋታል። እንደዛም ሆኖ ማስክ ለብሳ ወደ ግቢ መግባት እንደማትችል ነግረው መልሰዋታል። 

ቅዳሜ ከሰዓት ሁለት ኒቃብ የለበሱ ተማሪዎች ግቢ ሊገቡ ሲሉ ተከልክለዋል። ለምን እንደተከለከሉ ሲጠይቁ ‘ ለደህንነት ሲባል ፊታችሁ መሸፈን የለበትም ’ አሏቸው።

ለደኅንነት ሲባል ከሆነ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በሴት ጥበቃ ተፈትሸው፣ አይዲያቸውን አሳይተው እንዲገቡ ሲጠይቋቸው ‘ ያንችን ፊት ማየት ምንም አይሰራልኝም። ፊትሽን ለምታሳይው አሳይ ’ የሚል መልስ ተሰጠን።

ከዚያ በኋላም ሰኞ እለት ደግሞ ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ መልበስ እንደማይቻል በፕሬዜዳንቱ ጭምር ተወሰነ። የተማሪ ተወካዮች ጠርተው ይህን አሳወቋቸው።

ጥበቃዎቹም ውሳኔውን በመጥቀስ ‘አናስገባም’ አሉን። ማክሰኞ እለት ማታ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን።

ረቡዕ ጠዋትም ከለር ማስክ አድርገው የገቡትን በፌደራል ጭምር አስፈራርተው ፊታቸውን እንዲገልጡ አድርገው፣ ሂጃብም ማውለቅ እንዳለባቸው አሳሰቧቸው።

ከሰኞ ጀምሮ ክላስም እየተከታተልን አይደለም፣ ኤግዛም አልፎናል፣ አሳይመንትም እያለፈን ነው። ማውለቅ ስለማንችል ከግቢ ውጪ ነን። በቃ ከተማሪነት ውጪ ባለ ህይወት ነን። እንደ ሴትነታችን ትልቅ የመብት ጥሰት ነው የተፈጸመብን። 

ከምሽቱ 3 ሰዓት እንዳንገባ ሲከለክሉን የት እንድናድር፣ ምን እንድንለብስ፣ ምን እንደምንምገብ ያሰቡትን አናውቅም። ስለዚህ እንደንገባ ቢፈቅዱም እንዲህ ያደርጉበት ምክንያትን ሊጠየቁ ይገባል ”
ሲሉ ተናግረዋል።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅናቸው ስማቸው እንዲነገር ያልፈቀዱ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ ስለጉዳዩ በዩኒቨርሲቲው ፌስ ቡክ ገጽ የወጣውን መረጃ እንድንጠቀም ጠቁመዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተማሪዎቹ ነቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰው እንዳይገቡ ተከልክለው ከግቢ ውጪ በመሆናቸው ትምህርት እያለፋቸው እንደሆነ ገልጸዋል፤ መከልከሉ ልክ ነው ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል።

በምላሻቸው፣ “ እንዲህ አይነት ነገር የለም። የተሳሳተ መረጃ ነው። ማንም ተማሪ እዚህ ግቢ በተፈቀደለት ሰዓት ይገባል፤ ይወጣል ” ሲሉ መልሰዋል።

“ የተቋሙንም ሆነ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት አስተዳደር መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” ብለዋል።

ተማሪዎቹ በተጨባጭ ከግቢ ውጪ እንደሆኑ፣ ክላስ እያለፋቸው እንደሆነ በድጋሚ የገለጽንላቸው እኝሁ አካል፣ በድጋሚም “ የለም ” የሚል ማስተባበያ ነው የሰጡት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የጌዴኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን ተማሪዎች ደረሰብን የሚሉት ክልከላ ምንድነው ? ዩኒቨርሲቲው “ ሀሰተኛ መረጃ ነው ” ብሏልና እናንተ ጉዳዩን አይታችሁት ነበር ? ሲል ማረጋገጫ ጠይቋል።

ምክር ቤቱ ምን መለሰ ?

“ ጉዳዩ ከወር በፊት ደርሶን ነበር። እየቆየ ከፍ እያለ መጥቶ ተማሪዎች ግቢ ለመግባት ሲከለከሉ እኛም ደብዳቤ ፅፈን ነበር ችግሩ እንዲፈታ።

ዩኒቨርሲቲው እርከን ያልጠበቀ ጉዳይ ተደርጎ ታይቶ ነው፤ ተማሪዎቹን እናገኛቸዋለን የሚል ጥሩ ስሜት ነበረው። 

የእስልምና አለባበስ ከጥንት ጀምሮ ራሱን የቻለ ሊቃውንቶች ያስቀመጡት ነው። ይሄ የተሻለውና ተመራጭ የሆነው አለባበስ ነው ” ብሏል።


(ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94023
Create:
Last Update:

#Update

🔴 “ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን ” - ሙስሊም ተማሪዎች

🔵 “ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማትን አስተዳደርና መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” - ዲላ ዩኒቨርሲቲ 

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ እንዳይለብሱ በመከልከላቸው ከትምህርታቸው እየተስተጓጎሉ በመሆኑ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጠንከር ያለ ስሞታ አቅርበዋል።

የተማሪዎቹ ዝርዝር ስሞታ ምንድን ነው ?

“ ኒቃብና ጥቁር ማስክ እንዳንለብስ ነው የተከለከልነው። ክልከላው የጀመረው ከአንድ ወር በፊት ነበር። በዚህም ማመልከቻ አስገብተን ነበር መልበስ እንዲፈቀድልን። ሆኖም ግን ምላሽ ሳይሰጠን ቆዬ።

ትምህርታችን በስርዓት እንዳንከታተል አስተጓጎሉን። ቅዳሜ፣ አንዲት እህት ማስክ አድርጋ፣ ሂጃብ ለብሳ በምትገባበት ወቅት ኦዲያ ካምፓስ በሁለቱም በሮች እንዳትገባ ከልክለዋታል።

እንዲያውም ወንዶቹ የግቢው ጥበቆች አስፈራርተው ፊቷን አስከፍተዋታል። እንደዛም ሆኖ ማስክ ለብሳ ወደ ግቢ መግባት እንደማትችል ነግረው መልሰዋታል። 

ቅዳሜ ከሰዓት ሁለት ኒቃብ የለበሱ ተማሪዎች ግቢ ሊገቡ ሲሉ ተከልክለዋል። ለምን እንደተከለከሉ ሲጠይቁ ‘ ለደህንነት ሲባል ፊታችሁ መሸፈን የለበትም ’ አሏቸው።

ለደኅንነት ሲባል ከሆነ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በሴት ጥበቃ ተፈትሸው፣ አይዲያቸውን አሳይተው እንዲገቡ ሲጠይቋቸው ‘ ያንችን ፊት ማየት ምንም አይሰራልኝም። ፊትሽን ለምታሳይው አሳይ ’ የሚል መልስ ተሰጠን።

ከዚያ በኋላም ሰኞ እለት ደግሞ ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ መልበስ እንደማይቻል በፕሬዜዳንቱ ጭምር ተወሰነ። የተማሪ ተወካዮች ጠርተው ይህን አሳወቋቸው።

ጥበቃዎቹም ውሳኔውን በመጥቀስ ‘አናስገባም’ አሉን። ማክሰኞ እለት ማታ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን።

ረቡዕ ጠዋትም ከለር ማስክ አድርገው የገቡትን በፌደራል ጭምር አስፈራርተው ፊታቸውን እንዲገልጡ አድርገው፣ ሂጃብም ማውለቅ እንዳለባቸው አሳሰቧቸው።

ከሰኞ ጀምሮ ክላስም እየተከታተልን አይደለም፣ ኤግዛም አልፎናል፣ አሳይመንትም እያለፈን ነው። ማውለቅ ስለማንችል ከግቢ ውጪ ነን። በቃ ከተማሪነት ውጪ ባለ ህይወት ነን። እንደ ሴትነታችን ትልቅ የመብት ጥሰት ነው የተፈጸመብን። 

ከምሽቱ 3 ሰዓት እንዳንገባ ሲከለክሉን የት እንድናድር፣ ምን እንድንለብስ፣ ምን እንደምንምገብ ያሰቡትን አናውቅም። ስለዚህ እንደንገባ ቢፈቅዱም እንዲህ ያደርጉበት ምክንያትን ሊጠየቁ ይገባል ”
ሲሉ ተናግረዋል።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅናቸው ስማቸው እንዲነገር ያልፈቀዱ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ ስለጉዳዩ በዩኒቨርሲቲው ፌስ ቡክ ገጽ የወጣውን መረጃ እንድንጠቀም ጠቁመዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተማሪዎቹ ነቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰው እንዳይገቡ ተከልክለው ከግቢ ውጪ በመሆናቸው ትምህርት እያለፋቸው እንደሆነ ገልጸዋል፤ መከልከሉ ልክ ነው ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል።

በምላሻቸው፣ “ እንዲህ አይነት ነገር የለም። የተሳሳተ መረጃ ነው። ማንም ተማሪ እዚህ ግቢ በተፈቀደለት ሰዓት ይገባል፤ ይወጣል ” ሲሉ መልሰዋል።

“ የተቋሙንም ሆነ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት አስተዳደር መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” ብለዋል።

ተማሪዎቹ በተጨባጭ ከግቢ ውጪ እንደሆኑ፣ ክላስ እያለፋቸው እንደሆነ በድጋሚ የገለጽንላቸው እኝሁ አካል፣ በድጋሚም “ የለም ” የሚል ማስተባበያ ነው የሰጡት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የጌዴኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን ተማሪዎች ደረሰብን የሚሉት ክልከላ ምንድነው ? ዩኒቨርሲቲው “ ሀሰተኛ መረጃ ነው ” ብሏልና እናንተ ጉዳዩን አይታችሁት ነበር ? ሲል ማረጋገጫ ጠይቋል።

ምክር ቤቱ ምን መለሰ ?

“ ጉዳዩ ከወር በፊት ደርሶን ነበር። እየቆየ ከፍ እያለ መጥቶ ተማሪዎች ግቢ ለመግባት ሲከለከሉ እኛም ደብዳቤ ፅፈን ነበር ችግሩ እንዲፈታ።

ዩኒቨርሲቲው እርከን ያልጠበቀ ጉዳይ ተደርጎ ታይቶ ነው፤ ተማሪዎቹን እናገኛቸዋለን የሚል ጥሩ ስሜት ነበረው። 

የእስልምና አለባበስ ከጥንት ጀምሮ ራሱን የቻለ ሊቃውንቶች ያስቀመጡት ነው። ይሄ የተሻለውና ተመራጭ የሆነው አለባበስ ነው ” ብሏል።


(ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA







Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94023

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Right now the digital security needs of Russians and Ukrainians are very different, and they lead to very different caveats about how to mitigate the risks associated with using Telegram. For Ukrainians in Ukraine, whose physical safety is at risk because they are in a war zone, digital security is probably not their highest priority. They may value access to news and communication with their loved ones over making sure that all of their communications are encrypted in such a manner that they are indecipherable to Telegram, its employees, or governments with court orders. A Russian Telegram channel with over 700,000 followers is spreading disinformation about Russia's invasion of Ukraine under the guise of providing "objective information" and fact-checking fake news. Its influence extends beyond the platform, with major Russian publications, government officials, and journalists citing the page's posts. The last couple days have exemplified that uncertainty. On Thursday, news emerged that talks in Turkey between the Russia and Ukraine yielded no positive result. But on Friday, Reuters reported that Russian President Vladimir Putin said there had been some “positive shifts” in talks between the two sides. "The argument from Telegram is, 'You should trust us because we tell you that we're trustworthy,'" Maréchal said. "It's really in the eye of the beholder whether that's something you want to buy into." "He has to start being more proactive and to find a real solution to this situation, not stay in standby without interfering. It's a very irresponsible position from the owner of Telegram," she said.
from ar


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American