Telegram Group & Telegram Channel
" ለቅሬታችን ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘታችን ለርዕሰ መስተዳድሩ አቅርበናል " - የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መምህራን

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ክፍያ " አልተከፈለንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

በቁጥር ከአንድ መቶ በላይ የሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአድራሻ የፃፉትንና የተፈራረሙበትን የቅሬታ ደብዳቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ሰራተኞቹ በሰጡት ቃልም " መንግስት ለኑሮ ዉድነት ማካካሻ በማለት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1/2017ዓ/ም ጀምሮ ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም እስካሁን የማሻሻያዉ ልዩነት አልተከገለንም " ሲሉ ገልፀዋል።

" ስራ ሳናቆም ተደጋጋሚ ቅሬታ ስናቀርብ ቆይተናል " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ከዚህ ቀደም ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ አብዘኞቻችን የተሰጠንን የደረጃ ዕድገት ክፊያ ተግባራዊ አልተደረገም በዚያ ላይ ይህ ሲጨመርበት ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነዉ " ብለዋል።

ኮሌጁ ስለ ጉዳዩ ምን ይላል ?

የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ጻድቁ ሳሙኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የደሞዝ ማሻሻያው አለመከፈሉ ትክክል መሆኑን አረጋግጠዋል።

" የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ በክልሉ ያሉ የሁሉም ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎችን መረጃ በአጭር ጊዜ ዉስጥ በመሰብሰብና በማደረጃት ክፍያዉን እንደሚፈፅም ምላሽ ስለሰጠ እየተጠባበቅን እንገኛለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደቡብ ኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮን ምላሽም ጠይቋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቢዮት ደምሴ በቢሯቸዉና በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ እጅ ያለዉ የሰራተኞች ቁጥር መረጃ ከ5 መቶ በላይ ሰዉ የቁጥር ልዩነት በማሳየቱ የማጣራቱ ስራ እስኪጠናቀቅ ክፍያው አለመፈፀሙን ተናግረዋል።

" አሁን ላይ ሁሉም ኮሌጆች መረጃዎችን አጠናቀዉ ወደ ፐብሊክ ሰርቪስ የመላኩ ስራ ስለተጠናቀቀ በአጭር ቀናት ዉስጥ ችግሩ ይፈታል " ሲቡ ያላቸዉን ሙሉ እምነት ገልፀዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክንክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ስር 35 ኮሌጆች መኖራቸዉን ከነዚህም ዉስጥ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ አረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ150 በላይ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94351
Create:
Last Update:

" ለቅሬታችን ተገቢዉን ምላሽ ባለማግኘታችን ለርዕሰ መስተዳድሩ አቅርበናል " - የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ መምህራን

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች አዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ ክፍያ " አልተከፈለንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

በቁጥር ከአንድ መቶ በላይ የሆኑ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአድራሻ የፃፉትንና የተፈራረሙበትን የቅሬታ ደብዳቤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ሰራተኞቹ በሰጡት ቃልም " መንግስት ለኑሮ ዉድነት ማካካሻ በማለት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከጥቅምት 1/2017ዓ/ም ጀምሮ ክፍያ የፈፀመ ቢሆንም እስካሁን የማሻሻያዉ ልዩነት አልተከገለንም " ሲሉ ገልፀዋል።

" ስራ ሳናቆም ተደጋጋሚ ቅሬታ ስናቀርብ ቆይተናል " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ከዚህ ቀደም ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ አብዘኞቻችን የተሰጠንን የደረጃ ዕድገት ክፊያ ተግባራዊ አልተደረገም በዚያ ላይ ይህ ሲጨመርበት ለዘርፈ ብዙ ችግሮች እየዳረገን ነዉ " ብለዋል።

ኮሌጁ ስለ ጉዳዩ ምን ይላል ?

የአረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ዲን አቶ ጻድቁ ሳሙኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ የደሞዝ ማሻሻያው አለመከፈሉ ትክክል መሆኑን አረጋግጠዋል።

" የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ በክልሉ ያሉ የሁሉም ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛዎችን መረጃ በአጭር ጊዜ ዉስጥ በመሰብሰብና በማደረጃት ክፍያዉን እንደሚፈፅም ምላሽ ስለሰጠ እየተጠባበቅን እንገኛለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደቡብ ኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮን ምላሽም ጠይቋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አቢዮት ደምሴ በቢሯቸዉና በክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ እጅ ያለዉ የሰራተኞች ቁጥር መረጃ ከ5 መቶ በላይ ሰዉ የቁጥር ልዩነት በማሳየቱ የማጣራቱ ስራ እስኪጠናቀቅ ክፍያው አለመፈፀሙን ተናግረዋል።

" አሁን ላይ ሁሉም ኮሌጆች መረጃዎችን አጠናቀዉ ወደ ፐብሊክ ሰርቪስ የመላኩ ስራ ስለተጠናቀቀ በአጭር ቀናት ዉስጥ ችግሩ ይፈታል " ሲቡ ያላቸዉን ሙሉ እምነት ገልፀዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክንክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ስር 35 ኮሌጆች መኖራቸዉን ከነዚህም ዉስጥ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ በሚገኘዉ አረካ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ከ150 በላይ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ ከኮሌጁ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA










Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94351

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Perpetrators of such fraud use various marketing techniques to attract subscribers on their social media channels. The Dow Jones Industrial Average fell 230 points, or 0.7%. Meanwhile, the S&P 500 and the Nasdaq Composite dropped 1.3% and 2.2%, respectively. All three indexes began the day with gains before selling off. In the United States, Telegram's lower public profile has helped it mostly avoid high level scrutiny from Congress, but it has not gone unnoticed. He floated the idea of restricting the use of Telegram in Ukraine and Russia, a suggestion that was met with fierce opposition from users. Shortly after, Durov backed off the idea. The picture was mixed overseas. Hong Kong’s Hang Seng Index fell 1.6%, under pressure from U.S. regulatory scrutiny on New York-listed Chinese companies. Stocks were more buoyant in Europe, where Frankfurt’s DAX surged 1.4%.
from ar


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American