group-telegram.com/bookstorej/285
Last Update:
ያጣሁት። ይቅር በለኝ ሚኪ!"
አለ የራሱ ፊት ላይ አፍጥጦ ።ወደ ሚኪ በመመለስ ከሚኪ ጋር ስልክ ተለዋውጦ ከተረጋጋ በኋላ እንደሚደውልለት ነግሮት
ከሆቴሉ በመውጣት ወደ መኪናው ገብቶ ወደ ምኞት በረረ። ከምኞት ጋር አዲስ የተከራዩት ግቢ በር ላይ ሲደርስ ምኞትን
ሲያያት ምን ሊሰማው እንደሚችል ያውቀዋልና ወደ ውስጥ መግባት ፈራ። ለደቂቃዎች አዛው በሀሳብ ሲታመስ ከቆየ በኋላ ከመኪናው ወርዶ ወደ ውስጥ ዘለቀ የተዘጋውን በር በያዘው ቁልፍ ከፍቶ ወደ ቤት ሲገባ ፊልም እያየች የነበረችው ምኞት ብድግ ከማለቷ መሳይ ተንደርድሮ ተጠመጠመባት። ከእቅፉ እንዳትወጣ አጥብቆ እንደያዛት ቆየ ምኞት በሁኔታው ግራ ተጋባች ። በውስጧ በፍቅር አብረን እንሁን ጥያቄው ምላሹ ይቆይ ስላለችው የተረበሸ መስሎ ተሰማት ። እቅፉ ውስጥ እንዳለች እራሱን አዳመጠ። ናርዶስን አሰባት ማድረግ ያለበትን ወሰነ። ውሳኔውን ለመፈፀም ለራሱም ቃል ገባ ለሷ ግን ምንም አላላትም። በንጋታው በጠዋት ከሚኪ ጋር ተገናኝተው ናርዶስ ወዳለችበት
ከአዳስ አበባ 280 ኪሜ በላይ ወደሚርቀው ክፍለ ሀገር በሚቀጥለው ቀን ጥዋት ለመሄድ ቀጠሮ ያዙ።ወደ አንድ የቅርብ ጓደኛው በማምራት ከሚኪ ጋር በተቀጣጠሩበት በተመሳሳይ ሰዓት
ቀጠሮ ያዘ ያን ቀን ቀኑን ሙሉ ምኞትን ሲያጫውታት እና ሲንከባከባት ዋለ።
ማታ ላይ ነገ ጥዋት ከአባቱ ጋር ወደ ክፍለ ሀገረ ለአስፈላጊ ጉዳይ እንደሚሄዱ ነገራትና ተሰነባብተው ወደየ ክፍላቸው ገብተው ተኙ። በጠዋት ሊሄድ ሲነሳ ከሌላኛው ክፍል ድምፅ ሰማ ። ወደ
ማብሰያው ክፍል ሲሄድ ምኞት ቀድማው ተነስታ ቁርስ እያዘጋጀችለት ነበር። እስካሁን የተቆጣጠረውን እንባ ከዚ በላይ ሊገድበው አልቻለም። አነባ.. ምኞት እጅግ በጣም ተረበሸች ። መሳይ ላይ የምታየው ድንገት ስሜታዊ የመሆን ባህሪ ግራ ቢያጋባትም ምን ሆነሀል ብላ አልጠየቀችውም።ቀጣዩን ጥያቄ ፍራቻ።
ከቤት ወጥቶ በሄደ 20 ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ውስጥ አባቴ ቶሎ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመለስና እኔ ግን እዛ ለጉዳይ እንደሚቆይ ስለነገረኝ ብቻሽን ከምትሆኚ ብዬ እንዲያመጣሽ ጓደኛዬ ጋር ደውዬለታለው ከደቂቃዎች ቡሀላ አንቺ ጋር ይመጣል ተዘጋጂና ጠብቂው ብሎ በስጦታ መልክ ወደ ሰጣት ሞባይል መልዕክት ላከ።
ምኞት መልክቱን እንዳነበበች ለምን እንደሆነ ባይገባትም ሆዷ ኣካባቢ የፍርሀት ስሜት ተሰማት። ቢሆንም መዘጋጀት ጀመረች ስትጨርስ የክላክስ ድምፅ ሰምታ ስትወጣ የመሳይ ጓደኛ ነበር እነ መሳይ ከሄዱ ከደቂቃዎች በኋላ ናርዶስ ከአባቷ ጋር ተደብቃ እምትኖርበት ቤት ደረሱ በሩን ሲያንኳኩ የከፈተችው. እራሳ ነበረች ስታየው ወደ ጀርባዋ ወደቀች መሳይ እሷ ላይ ተደፍቶ ሲያነባ
ሁሉም በሁኔታቸው ማለቀስ ጀመሩ።
ከቆይታ ቡሀላ መሳይ እየነዳ ናርዶስ አጠገቡ ጋቢና ውስጥ ተቀምጣለች ከኋላ ሚኪ እና ፅናት ተቀምጠው ይዟቸው በመውጣት ከአንድ ጭር ካለ ሰፈር ውስጥ ሲደርስ ከአንድ ግቢ በር
ላይ አቆማት ለምን እዛ አምጥቶ እንዳቆማት ከሱ ውጪ የሚያውቅ የለም። ከነሱ ፊት ለፊት ከሩቅ አንዲት መኪና ወደነሱ እየመጣች ነው። የመሳይ መኪና ጋር ከመድረሷ በፊት ራቅ ብላ ቆመች ። የመሲ ጓደኛ የሚነዳት መኪና ነች ውስጥ ደግሞ ምኞት ብቻዋን
ከውኻላ ተቀምጣለች። የመሳይ ጓደኛ ምኞትን " ያውልሽ የመሳይ መኪና እየሄድሽ ጠብቂኝ መኪናዋን አስተካክዬ ላቁማት።" አላት ለምን መጠጋት
እንዳልፈለገ ግራ እየገባት ለመውረድ ተዘጋጀች። መሳይ ሚኪን " ውረድ !" አለው ሚኪ "ለምን? አለ ። "እሺ በለኝና
በሩን ከፍተህ ውረድ" አለው።
"ወርጄ ምን ልስራ?
"ነው ሚኪ ተወው በቃ አትውረድ ከሰከንዶች በኋላ በሩን ከፍተህ
ሳይሆን ገንጥለህ ካልወረድክ መሳይ ምን አለ በለኝ !" አለው። ሚኪም " ይሄ ሰው ምንድነው ሚለው ናርዶሴ ገላግይኝ እንጂ!" ብሏት ቀና ሲል••• ምኞትን ፊት ለፊት ከቆመው መኪና ውስጥ ወርዳ ስትመጣ ተመለከታት። ያቺ ኮንዶሚኒየም ውስጥ ጥሏት የሄደው ምኞት ሳትሆን
መጀመሪያ ፌስ ቡክ ላይ ያያት ውበቷ ልብ የሚንደው ምኞት ከላይ እስከታች መሳይ በገዛላት የሚያምር ልብስ ተሽቀርቅራ እነሱ ወዳሉበት መኪና ስትመጣ ተመለከተ። " ፅናቴ እኔ የማየው ላንቺም እየታየሽ ነው ያቺ የምትመጣው እውነት የኔ ምኞት ነች አለ ፍቅር በገደለው ድምፅ መሳይ አንባው
ግጥም አለ። መሪው ላይ ተደፋ።
ሚኪ የመኪናው በር እንዴት እንደሚከፈት ጠፋበት ለመክፈት ይሞክራል ሳይከፍተው መልሶ ይተወውና ምኞትን ይመለከታል ። የሚኪን ሁኔታ መግለፅ ፍቅርን በአካል ምን እንደሚመስል
የማሳየት ያኽል ይከብድ ነበር። መኪና ውስጥ ፈንጅ ጠምደው በሩን ከቆለፉበት ሰውም በላይ የቱን እንደሚይዝ የቱን እንደሚነካ ቤት በኩል እንደሚወጣ ግራ ገብቶት ሲርበተበት ለተመለከተው ሰው ከምንም በላይ የሚንበረከከው ለፍቅር ብቻ መሆኑን ያረጋግጣል። ምኞት እየቀረበች ነው። በደመነፍስ በሩን ከፍቶ ከመኪናው ወረደ። ቆሞ ሲመለከታት አየችው። አይኖቹ እንባ እንዳዘሉ በፍቅር ፀሀይ በርተው ተመለከተች። በድንጋጤ ባለችበት ቀጥ ብላ ቆመች። ሮጦ በማቀፍ ሽቅብ አንስቷት እንደ እብድ መጮህ ጀመረ።
ከሶስት ወር ቡሀላ••
ለሁለቱ ጥንዶች ባንድ ላይ ድል ያለ ሰርግ ተደገሰ። በዛ ሰርግ ላይ ፅናት እራሷን ስታ ወደቀች ። ለሙሹሮቹ የፅናትን መውደቅ የነገራቸው አልነበረም። ፅናት ከተሻላት ቡሀላ ኢትዬጲያን ለቃ ወደ ሀገረ እንግሊዝ አቀናች። ፅናት በሄደች በሁለተኛው ወር
በመጀመሪያው እሁድ ። ሚኪ ፣ መሳይ፣ ምኞት እና ናርዶስ ወደ አማኑኤል የኧእምሮ ህሙማን
መታከሚያ ሆስፒታል ሰው ለመጠየቅ መጡ። ከሌሎቹ ህሙማን ጋር አልግባባ በማለቱ ለብቻው ተገሎ በአንድ ሰፊ ክፍል ውስጥ እንዲቀመጥ ወደ ተፈረደበት አንድ የአይምሮ ህመምተኛ ( እብድ ) ክፍል እንደደረሱ ወደ መስኮት ተጠግተው ወደ ውስጥ ሲመለከቱ•••
ክፍሉ ሰፊና ባዶ ነው። እክፍሉ ግድግዳ ላይ ሁለት ስዕሎች አሉ። አንደኛው ስዕል የሴት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ የወንድ ስዕል ነው። ከስዕሎቹ ፊት ህመምተኛው ቆሟል። የወንዱን ስዕል በቡጢና በቴስታ ይመታል ግንባሩና እጁ ተጋግጧል ። የሴቷን ስዕል እየደጋገመ በፍቅር ይስማል። ወንዱን ሚኪ ሴቷን ፅናቴ እያለ
ይጠራ ነበር ። .................ይሄው ሰው ያው ብሩክ ነበር።
.
.
.
.
🔥****ተፈፀመ******"**🔥
#ታሪኩ ይሄን ይመስላል...
BY Book store
Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260
Share with your friend now:
group-telegram.com/bookstorej/285