group-telegram.com/ZenaKristos/98
Last Update:
ሐዋርያው ዮሐንስ በዓለም ታሪክ ውስጥ እጅግ አስደናቂ የሆነውን መስዋዕትነት በአንድ ቀላል ቃል ገልጿል። "ሰቀሉት" የሚለው ግሥ ስም ወይም አድራጊው ወታደሮቹ ብቻ እንዳልሆኑ ማሳየቱ ትኩረት የሚስብ ነው። ዮሐንስ ኢየሱስን የሰቀሉት “ የሮማ ወታደሮች” ናቸው ብሎ አልጻፈም፤ ምንም እንኳን በእንጨት ላይ ያዋሉት እነሱ ቢሆኑም። ኢየሱስን የሰቀሉትን “አይሁዶች” ብቻ ናቸው ብሎ አልጻፈም፣ ምንም እንኳን በሰው እይታ ለሞት ያበቃው የሕዝቡ ጩኸት ቢሆንም። በዚህ ዓለም የሕይወት ስጦታ የተሰጠው እያንዳንዱ ሰው ኢየሱስን በመስቀል እንጨት ላይ የመቸነከሩን ኃላፊነት ይጋራል (ኢሳ 53፡5፣6)። እያንዳንዳቹ በሀጥያታቹ ምክንያት ኢየሱስ ክርስቶስን ሰቅላችሁታል።
መስቀሉ የእግዚአብሔርን ከባድ ፍትህ እና የኃጢአት አስከፊ መዘዝ በግልፅ ያሳየናል(ሕግ)። እንዲሁም የጌታችንን ፍቅር እና ርህራሄ ለማይገባቸው ኃጢአተኞች ያሳየናል(ወንጌል)። እንደተለመደው ሁለቱም መልእክቶች ለአድማጭ መቅረብ አለባቸው። ህግና ወንጌል።
መስቀሉ፡ የአዳኛችን ሙሉ ስራ ማስረጃ
1. ትንቢትን ሁሉ ይፈጽማል
2. ፍጹም እና ቅዱስ የሆነውን ሕይወቱን ይመሰክራል
3. ሞቱን ያስታውሰናል
ንጉሥን ሰቀሉት!
1. ምንም ያላጠፋውን ንጉሥ
2. በሕዝቡ የተጠላ ንጉሥ
3. በፍቅር ተልዕኮ ላይ ያለ ንጉስ
[1] ጲላጦስ በኢየሱስ ላይ ምንም ዓይነት ሕጋዊ ክስ ሊያገኝ አለመቻሉን እናያለን።
[2] ብዙዎች ኢየሱስን ከእግዚአብሔር የተላከ አይደለም ብለው ክደውታል።
[3] ኢየሱስ ንጉሥ ሆኖ ያልተቀበሉትን ጨምሮ ለሁሉም ሰዎች መከራ ለመቀበልና ለመሞት በፈቃደኝነት በሐዘን መንገድ መጓዙን ለማስታወስ ይጠቅማል።
°ለኢየሱስ ሞት ተጠያቂ የሆኑ ውስን ቡድኖች ላይ ጣት አንቀስር። ከዚህ ይልቅ እኛ ኃጢአት ስለሰራን፣ ኢየሱስን እንደ ንጉሣችን ባለመቀበላችን ጥፋተኞች መሆናችንን እና እርሱ ለእኛ ሲል ወደ ጎልጎታ በህማም መንገድ መሄዱን ለማስታወስ ይሁን። ተባረኩ።
ዜና ክርስቶስ || Christ Chronicles
BY ዜና ክርስቶስ || Christ Chronicles
![](https://photo.group-telegram.com/u/cdn4.cdn-telegram.org/file/DOYPPQUiiBA9H3c7MN7q3p4j39-H02ZlvYuGizSvDaq8s3Co5iFtZSYA46AHBtlYkvC0YQpZ4J3MAH9rY3rdtJf_r9fYcQy7fJcKpsGvV2S2hFFnQXtFM-gOTy9oCIWAjwYUGFXR71tswFgE7CN-scHGU4AG9h7lLVRN4xRcZ4zkVAZ8pFEq6wUo7zeaS2p3LDQ9ZfIuNE4lOWTU72ld-SHXVNLrcF6SaxFN0lZueZun5R2KEeXomtAR1wEuyNbtty_35qYp7yi_Hc3qLW6Uef-J5FKFMaw0Zv1TgR7JXv-zoHuehuZNNCtMt7dEocp3VKiLISd9czTxzmNM7qgH7Q.jpg)
![](https://photo.group-telegram.com/u/cdn4.cdn-telegram.org/file/vjuC0UzkYqa7svsWggIOYl8ye6GI4mC1JokV-J_6Nc5CEwxneTc2GHdRscsMlqQqcm0ixmi8NMxoL-WLK6LPwMhh9Opa_gtdPrQvRoaF_6BZKmKNiOqz42Ivxq_z7lQuBA-Wp9mJTKLEYyhE-67W2vx-MbUr9nAPgeo9stj3I-cLdDRfsnJk_XcvV_WeG1HINUlNUllvlgthPKV76-UNXRahj_6zYppudgshr77KbE_8lHwbqywjLT8bTP3Z2JAQv1rZeBBBQmVm50o675D0idJAtMiXwaE117kD0pKUIxUup9VgFtVRc4b2xrOazORHHzPAq7CQ1SX4Kaw5Up97sg.jpg)
Share with your friend now:
group-telegram.com/ZenaKristos/98