Telegram Group & Telegram Channel
አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት  ዕጩ ሆነው ቀረቡ።

በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ/ም  ፓርላማ ቀርበዋል።

ሌሎች አራት ዕጩዎችም መቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

አቶ ብርሃኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት ሲሆን የመጨረሻ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ነበር።

ከኃላፊነታቸው የተነሱት " በቀረበባቸው ቅሬታ " መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ ከ10 ዓመታት በፊት ዘግቧል።

" ከሠራተኞች እና ከተቋሙ ደንበኞች ቅሬታዎች ይቀርቡባቸው እንደነበር " ጋዜጣው በወቅቱ ዘግቧል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ ብርሃኑን ከዚህ ኃላፊነት ማንሳታቸውም የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል።

አቶ ብርሃኑ የአዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬከተር ሆነው ከመሾማቸው በፊት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው ከ1996 እስከ 2002 ዓ.ም. ለ6 ዓመታት አገልግለዋል።

በሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ መሠረት አቶ ብርሃኑ ከዚህ ኃላፊነታቸው የተነሱትም በቀረበባቸው ቅሬታ ምክንያት ነው።

ከተወለዱበት ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች አዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በአቶ ብርሃኑ ላይ የተፈራረሙትን ቅሬታ በጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትር ለነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ማቅረባቸውን የሪፖርተር ዘገባ ያስታውሳል።

ይህን ተከትሎ " በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ባቀረበባቸው ሪፖርት ከካቢኔ ጉዳይ ሚኒስትርነታቸው እና ከኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲነሱ " መደረጉን ሪፖርተር ከ10 ዓመታት በፊት በሠራው ዘገባ ጠቅሷል።

አቶ ብርሃኑ በመንግሥታዊ ተቋማት ከነበራቸው ኃላፊነት በተጨማሪ አወዛጋውን የ1997 ምርጫ ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ነበሩ።

የትምህርት ሁኔታቸው ምን ይመስላል ?

ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው። በዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብቶች ከሕንድ አገር የማስተርስ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል።

የስራ ህይወታቸው ምን ይመስላል ?

- ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲ አስተምረዋል።

- በዞን ፋይናንስ መምሪያ የህግ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።

- የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ባገኙበት የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የህግ ፋካልቲ ለ3 ዓመታት አስተምረዋል።

- በቀድሞው ደቡብ ክልል የፍትህ ቢሮ ኃላፊነት ላይ ሰርተዋል። ከዛ በመቀጠልም በቀረበባቸው ቅሬታዎች ከስልጣን ወደተነሱባቸው የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት አቅንተዋል።

- ከመንግስታዊ የሥራ ኃላፊ ከተነሱ በኋላ ላለፉት 10 ዓመታት በጥብቅና እና በህግ ማማከር ስራ ላይ መሰማራታቸውን ለፓርላማ አባላት የቀረበው የስራ ልምድ ያሳያል።

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94129
Create:
Last Update:

አቶ ብርሃኑ አዴሎ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት  ዕጩ ሆነው ቀረቡ።

በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ/ም  ፓርላማ ቀርበዋል።

ሌሎች አራት ዕጩዎችም መቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

አቶ ብርሃኑ ከዚህ ቀደም በተለያዩ መንግሥታዊ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት ሲሆን የመጨረሻ መንግሥታዊ ኃላፊነታቸው የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ነበር።

ከኃላፊነታቸው የተነሱት " በቀረበባቸው ቅሬታ " መሆኑን ሪፖርተር ጋዜጣ ከ10 ዓመታት በፊት ዘግቧል።

" ከሠራተኞች እና ከተቋሙ ደንበኞች ቅሬታዎች ይቀርቡባቸው እንደነበር " ጋዜጣው በወቅቱ ዘግቧል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ አቶ ብርሃኑን ከዚህ ኃላፊነት ማንሳታቸውም የሪፖርተር ዘገባ ያሳያል።

አቶ ብርሃኑ የአዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬከተር ሆነው ከመሾማቸው በፊት የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው ከ1996 እስከ 2002 ዓ.ም. ለ6 ዓመታት አገልግለዋል።

በሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ መሠረት አቶ ብርሃኑ ከዚህ ኃላፊነታቸው የተነሱትም በቀረበባቸው ቅሬታ ምክንያት ነው።

ከተወለዱበት ካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ነዋሪዎች አዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በአቶ ብርሃኑ ላይ የተፈራረሙትን ቅሬታ በጊዜው ጠቅላይ ሚኒስትር ለነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ማቅረባቸውን የሪፖርተር ዘገባ ያስታውሳል።

ይህን ተከትሎ " በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የተቋቋመ አጣሪ ኮሚቴ ባቀረበባቸው ሪፖርት ከካቢኔ ጉዳይ ሚኒስትርነታቸው እና ከኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው እንዲነሱ " መደረጉን ሪፖርተር ከ10 ዓመታት በፊት በሠራው ዘገባ ጠቅሷል።

አቶ ብርሃኑ በመንግሥታዊ ተቋማት ከነበራቸው ኃላፊነት በተጨማሪ አወዛጋውን የ1997 ምርጫ ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ነበሩ።

የትምህርት ሁኔታቸው ምን ይመስላል ?

ከሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪ አላቸው። በዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብቶች ከሕንድ አገር የማስተርስ ዲግሪያቸውን ተቀብለዋል።

የስራ ህይወታቸው ምን ይመስላል ?

- ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ ዩኒቨርሲቲ አስተምረዋል።

- በዞን ፋይናንስ መምሪያ የህግ አማካሪ ሆነው አገልግለዋል።

- የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ባገኙበት የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የህግ ፋካልቲ ለ3 ዓመታት አስተምረዋል።

- በቀድሞው ደቡብ ክልል የፍትህ ቢሮ ኃላፊነት ላይ ሰርተዋል። ከዛ በመቀጠልም በቀረበባቸው ቅሬታዎች ከስልጣን ወደተነሱባቸው የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት አቅንተዋል።

- ከመንግስታዊ የሥራ ኃላፊ ከተነሱ በኋላ ላለፉት 10 ዓመታት በጥብቅና እና በህግ ማማከር ስራ ላይ መሰማራታቸውን ለፓርላማ አባላት የቀረበው የስራ ልምድ ያሳያል።

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94129

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In 2014, Pavel Durov fled the country after allies of the Kremlin took control of the social networking site most know just as VK. Russia's intelligence agency had asked Durov to turn over the data of anti-Kremlin protesters. Durov refused to do so. In the United States, Telegram's lower public profile has helped it mostly avoid high level scrutiny from Congress, but it has not gone unnoticed. 'Wild West' The channel appears to be part of the broader information war that has developed following Russia's invasion of Ukraine. The Kremlin has paid Russian TikTok influencers to push propaganda, according to a Vice News investigation, while ProPublica found that fake Russian fact check videos had been viewed over a million times on Telegram. Recently, Durav wrote on his Telegram channel that users' right to privacy, in light of the war in Ukraine, is "sacred, now more than ever."
from br


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American