Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ሰባት

እጁን ዘርግቶ የተራቆተ እግሯን ሸፈነላት። ምን ነካኝ? አለ ራሱን ቆጣ ብሎ። የተገተረበትን ቦታ ለቆ ወደ መኝታ ቤቱ አመራና አልጋው ላይ ተወረወረ። ጎጃምን ለቆ ሲወጣ የሚያስታውሰው ነገር የለም። በዛን ጊዜ በጣም ልጅ ነበረ። ነገሮች ተረስተውታል። አንድ የማይረሳው ነገር ግን አለ። ታናሽ ወንድሙ እዮብ። በሁለት አመት ውስጥ አከታትላ የወለደቻቸው እናታቸው የ አራት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች እናት ናት። የእድሜ ልዩነታቸው ብዙም ስላይደለ እዮብና አልአዛር መንታ ይመስላሉ።

አባታቸው በእናታቸው ላይ የሚያደርሰውን ግፍ ማየት የሚችልበት ጥንካሬ ስላጣ አንድ ቀን ወንድሙ እዮብን ብቻ ተሰናብቶ ጎጃምን ለቀቀ። ለቀቀ የሚለው ቃል አልአዛር እዚህ ቦታ ለመድረስ ያየው መከራና ጊዜ ባይገልፀውም እንዲሁ ለቀቀ ይባል። የወሰደበት ጊዜ ረጅም ነው ምን አልባትም የእድሜውን እኩሌታ ያህላል።

እዮብ ወደእዚህ አገር ሲመጣ አልአዛር ትንሽ ሱቅ ከፍቶ በመነገድ ላይ ነበር። የስጋ ነገር ሆነና እንደገና ለመገናኘት ዝምድናቸውንም ለማደስ ጊዜ አልፈጀባቸውም። እዮብ አዲስ አበባ ሲመጣ እናታቸው ሆነ አባታቸው ወንድም እህቶቻቸው በወረርሽኝ አልቀው ነበር። ብቻውን የቀረው አንድ እዮብም የተመደበበት ወደነበረው ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ በጎጃም የቀረው አንድም ቤተሰብ የለም። ሁሉም አልቀዋል። ለዚህም ተጠያቂው በምንቸገረኝነት ከዳር ሆኖ ሲመለከት የነበረው መንግስት ለመሆኑ ደምድሟል።

ልቡ በቀልን እንዳረገዘ ዩኒቨርስቲውን ተቀላቀለ። ከአንድ ወር በኃላም በልጅነቱ የተለየውን ወንድሙን አገኘና የብቸኝነቱን ስቃይ መቋቋም ቻለ። የእዮብና የአልአዛር ገበያ ግንኙነት በሚስጥር እንዲሆን ሀሳብ ያቀረበው እዮብ ነበር። አልአዛር ከአገሩ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን ስም ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። "አንተነህ" ምን አይነት አስቀያሚ ስም ነው ሲል አሰበ። ገና አዲስ አበባ እንደገባ ወደ አልአዛር ቀየረ። ወንድማማቾቹ በእረፍት ቀናቸው በድብቅ ተገናኝተው ይወያያሉ። በመካከላቸው የነበረው ፍቅር ጠንካራ ነው። አልአዛር ወሩንና ቀኑን ባያስታውሰውም ብቻ የሆነ ቀን ወንድሙ እዮብ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ወደ እሱ ሲሮጥ ተመለከተ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጉቶ ስለነበር የእዮብ ትንፋሽ መለስ እስኪል ራሱ አልጠበቀም። ምን እንደሆነ ለማወቅ በጥያቄ ያጣድፈው ጀመር።

ፍቅር ይዞኛል! አለው ከእሱ መፍትሔ ያገኝ ይመስል። ታዲያ ምን ችግር አለው? አለ አልአዛር በፍቅር መያዝ እንዲህ ወንድሙን ያስጨነቀበት ምክንያት አልገባሁም። ባክህ አድምጠኝ አለ እዮብ የወንድሙ ቸልታ ቅር አሰኝቶት። የተማሪዎች ህብረት አባል ነኝ። ልጅቷም እንዲሁ አለ እዮብ ከወንድሙ የደበቀውን ሚስጥር ማጋለጡ እያስፈራው።

አልአዛር ስጋቱ እውን ሆኖ ሲያየው የሚያደርገውን አሳጣው። ድሮውኑ የወንድሙን ቆራጥነት ያውቀዋል። የህብረቱ አባል መሆን ማለት ራስን በሸምቀቆ ወደተዘጋጀ ገመድ ማስገባት ማለት ነው። የእዮብን ግትር ውሳኔ ማስቀረት ፍፁም እንደማይቻለው ስለተገነዘበ በሀዘን አንገቱን አቀርቅሮ ዝምታን መረጠ።

አሊ አንድ ነገር በል እንጂ! አለ እዮብ የወንድሙን ዝምታ ጠልቶ። ምን ልበልህ? ራስህን ለሞት አሳልፈህ ስትሰጥ ዳር ሆኖ ከመመልከት ውጪ ምን አይነት ምርጫ አለኝ? አለ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ። ከተል አድርጎም ነግረአታል? አለ አልአዛር ንግግሩ ህይወት አልባ ነበር። አልነገርኳትም ልነግራትም አልፈልግም። የህብረቱ አባል እንዳትሆን ያላዴግኩት ጥረት አልነበረም ሊሳካልኝ አልቻለም እንጂ።

ህብረታችን በቅርቡ በመንግስት ሀይል ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅት አድርጓል። በዚህ ነገር ላይ እንዳትሳተፍ ብፈልግም ቁርጠኛ ሀሳቧን ማስቀየር የማይቻል ነገር ነው። ይህንን ለወንድሙ መንገሩ እፎይታን ሰጥቶታል። አልአዛር ግራ ተጋብቶ ወንድሙ ላይ አሁንም እንዳፈጠጠ ነው። እርዳታ ሲያሻት ወደ አንተ ትመጣለች። ለእኔ ስትል እንዳታሳፍራት። አለ ታላቅ ወንድሙን እያየ። ብሌንን አደራ መስጠቱ አርክቶታል። ፍቅሩ በአስተማማኝ እጆች ላይ ትሆናለች። ይህ ደግሞ ለእሱ ትልቅ ረፍት ነው። የልቡን አውጥቶ መንገር አለመፈለጉ የብሌንን እሺታን አልያም እምቢታን ማወቅ የለመፈለጉ ምክንያት ለአልአዛር አልተገለጠለትም።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/122
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ሰባት

እጁን ዘርግቶ የተራቆተ እግሯን ሸፈነላት። ምን ነካኝ? አለ ራሱን ቆጣ ብሎ። የተገተረበትን ቦታ ለቆ ወደ መኝታ ቤቱ አመራና አልጋው ላይ ተወረወረ። ጎጃምን ለቆ ሲወጣ የሚያስታውሰው ነገር የለም። በዛን ጊዜ በጣም ልጅ ነበረ። ነገሮች ተረስተውታል። አንድ የማይረሳው ነገር ግን አለ። ታናሽ ወንድሙ እዮብ። በሁለት አመት ውስጥ አከታትላ የወለደቻቸው እናታቸው የ አራት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች እናት ናት። የእድሜ ልዩነታቸው ብዙም ስላይደለ እዮብና አልአዛር መንታ ይመስላሉ።

አባታቸው በእናታቸው ላይ የሚያደርሰውን ግፍ ማየት የሚችልበት ጥንካሬ ስላጣ አንድ ቀን ወንድሙ እዮብን ብቻ ተሰናብቶ ጎጃምን ለቀቀ። ለቀቀ የሚለው ቃል አልአዛር እዚህ ቦታ ለመድረስ ያየው መከራና ጊዜ ባይገልፀውም እንዲሁ ለቀቀ ይባል። የወሰደበት ጊዜ ረጅም ነው ምን አልባትም የእድሜውን እኩሌታ ያህላል።

እዮብ ወደእዚህ አገር ሲመጣ አልአዛር ትንሽ ሱቅ ከፍቶ በመነገድ ላይ ነበር። የስጋ ነገር ሆነና እንደገና ለመገናኘት ዝምድናቸውንም ለማደስ ጊዜ አልፈጀባቸውም። እዮብ አዲስ አበባ ሲመጣ እናታቸው ሆነ አባታቸው ወንድም እህቶቻቸው በወረርሽኝ አልቀው ነበር። ብቻውን የቀረው አንድ እዮብም የተመደበበት ወደነበረው ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ በጎጃም የቀረው አንድም ቤተሰብ የለም። ሁሉም አልቀዋል። ለዚህም ተጠያቂው በምንቸገረኝነት ከዳር ሆኖ ሲመለከት የነበረው መንግስት ለመሆኑ ደምድሟል።

ልቡ በቀልን እንዳረገዘ ዩኒቨርስቲውን ተቀላቀለ። ከአንድ ወር በኃላም በልጅነቱ የተለየውን ወንድሙን አገኘና የብቸኝነቱን ስቃይ መቋቋም ቻለ። የእዮብና የአልአዛር ገበያ ግንኙነት በሚስጥር እንዲሆን ሀሳብ ያቀረበው እዮብ ነበር። አልአዛር ከአገሩ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን ስም ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። "አንተነህ" ምን አይነት አስቀያሚ ስም ነው ሲል አሰበ። ገና አዲስ አበባ እንደገባ ወደ አልአዛር ቀየረ። ወንድማማቾቹ በእረፍት ቀናቸው በድብቅ ተገናኝተው ይወያያሉ። በመካከላቸው የነበረው ፍቅር ጠንካራ ነው። አልአዛር ወሩንና ቀኑን ባያስታውሰውም ብቻ የሆነ ቀን ወንድሙ እዮብ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ወደ እሱ ሲሮጥ ተመለከተ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጉቶ ስለነበር የእዮብ ትንፋሽ መለስ እስኪል ራሱ አልጠበቀም። ምን እንደሆነ ለማወቅ በጥያቄ ያጣድፈው ጀመር።

ፍቅር ይዞኛል! አለው ከእሱ መፍትሔ ያገኝ ይመስል። ታዲያ ምን ችግር አለው? አለ አልአዛር በፍቅር መያዝ እንዲህ ወንድሙን ያስጨነቀበት ምክንያት አልገባሁም። ባክህ አድምጠኝ አለ እዮብ የወንድሙ ቸልታ ቅር አሰኝቶት። የተማሪዎች ህብረት አባል ነኝ። ልጅቷም እንዲሁ አለ እዮብ ከወንድሙ የደበቀውን ሚስጥር ማጋለጡ እያስፈራው።

አልአዛር ስጋቱ እውን ሆኖ ሲያየው የሚያደርገውን አሳጣው። ድሮውኑ የወንድሙን ቆራጥነት ያውቀዋል። የህብረቱ አባል መሆን ማለት ራስን በሸምቀቆ ወደተዘጋጀ ገመድ ማስገባት ማለት ነው። የእዮብን ግትር ውሳኔ ማስቀረት ፍፁም እንደማይቻለው ስለተገነዘበ በሀዘን አንገቱን አቀርቅሮ ዝምታን መረጠ።

አሊ አንድ ነገር በል እንጂ! አለ እዮብ የወንድሙን ዝምታ ጠልቶ። ምን ልበልህ? ራስህን ለሞት አሳልፈህ ስትሰጥ ዳር ሆኖ ከመመልከት ውጪ ምን አይነት ምርጫ አለኝ? አለ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ። ከተል አድርጎም ነግረአታል? አለ አልአዛር ንግግሩ ህይወት አልባ ነበር። አልነገርኳትም ልነግራትም አልፈልግም። የህብረቱ አባል እንዳትሆን ያላዴግኩት ጥረት አልነበረም ሊሳካልኝ አልቻለም እንጂ።

ህብረታችን በቅርቡ በመንግስት ሀይል ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅት አድርጓል። በዚህ ነገር ላይ እንዳትሳተፍ ብፈልግም ቁርጠኛ ሀሳቧን ማስቀየር የማይቻል ነገር ነው። ይህንን ለወንድሙ መንገሩ እፎይታን ሰጥቶታል። አልአዛር ግራ ተጋብቶ ወንድሙ ላይ አሁንም እንዳፈጠጠ ነው። እርዳታ ሲያሻት ወደ አንተ ትመጣለች። ለእኔ ስትል እንዳታሳፍራት። አለ ታላቅ ወንድሙን እያየ። ብሌንን አደራ መስጠቱ አርክቶታል። ፍቅሩ በአስተማማኝ እጆች ላይ ትሆናለች። ይህ ደግሞ ለእሱ ትልቅ ረፍት ነው። የልቡን አውጥቶ መንገር አለመፈለጉ የብሌንን እሺታን አልያም እምቢታን ማወቅ የለመፈለጉ ምክንያት ለአልአዛር አልተገለጠለትም።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/122

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram has become more interventionist over time, and has steadily increased its efforts to shut down these accounts. But this has also meant that the company has also engaged with lawmakers more generally, although it maintains that it doesn’t do so willingly. For instance, in September 2021, Telegram reportedly blocked a chat bot in support of (Putin critic) Alexei Navalny during Russia’s most recent parliamentary elections. Pavel Durov was quoted at the time saying that the company was obliged to follow a “legitimate” law of the land. He added that as Apple and Google both follow the law, to violate it would give both platforms a reason to boot the messenger from its stores. The Russian invasion of Ukraine has been a driving force in markets for the past few weeks. In this regard, Sebi collaborated with the Telecom Regulatory Authority of India (TRAI) to reduce the vulnerability of the securities market to manipulation through misuse of mass communication medium like bulk SMS. That hurt tech stocks. For the past few weeks, the 10-year yield has traded between 1.72% and 2%, as traders moved into the bond for safety when Russia headlines were ugly—and out of it when headlines improved. Now, the yield is touching its pandemic-era high. If the yield breaks above that level, that could signal that it’s on a sustainable path higher. Higher long-dated bond yields make future profits less valuable—and many tech companies are valued on the basis of profits forecast for many years in the future. As a result, the pandemic saw many newcomers to Telegram, including prominent anti-vaccine activists who used the app's hands-off approach to share false information on shots, a study from the Institute for Strategic Dialogue shows.
from br


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American