Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ፤ በምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " በትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ክህደት የፈፀመ ቡድን " ሲል ፈረጀ። በምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " ብሄራዊ ክህደት ፈፅሟል " ሲል የፈረጀው ማእከላዊ ኮሚቴ " ቡድኑ ከአፍራሽ ተግባሩ እንዲቆጠብ " መላው የትግራይ ህዝብ እና አባላት እንዲታገሉት…
#Tigray

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " - በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት

ለሁለት በተከፈሉት የህወሓት አመራሮች መካከል ያለው የመግለጫ ምልልስ አሁንም ቀጥሏል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ፤ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም ላወጣው መግለጫ መልስ ሰጥቷል።

በዚህም በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል ፈርጆታል። 

" በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደር ቃሉን አጥፈዋል በአጭር ጊዜ ልኩ ለማስገባት በማካሂደው ትግል ህዝቡ ከጎኔ ይቁም የሚል የሚያስደምም መግለጫ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም በመገናኛ ብዙሃን አሰራጭቷል " ሲል የአቶ ጌታቸው ቡድን ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድን " በመባል የተገለፀው በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " የፌደራል መንግስት የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት በሁለት ሳምንት እንዲነሳ ቀጠሮ ተሰጥቶኛል " ሲል እንዳልቆየ " ጊዚያዊ አስተዳደሩን በአጭር ጊዜ መልክ ለማስያዝ ወሰኜ ቃል ገብቻለሁ ተከተሉኝ " የሚል የክተት ጥሪ አቅርቧል ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" የዚህ አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ አካሄድ ለህዝብ አዲስ አይፈለም " ያለው መግለጫው  " ቡድኑ ከፌደራል መንግስት የሚነጋገረው እና የሚስማማው ሌላ ለትግራይ ህዝብ የሚለው ደግሞ ሌላ " ሲል ገልፆታል።

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን  እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " ሲል  በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ የትግራይን ህዝብ ከፌደራል መንግስት የሚያጋጭ አቅጣጫ እየተከተለ መሆኑ ያወጣው መግለጫ አመላካች ነው " ሲል አክሏል።

የደብረጽዮን (ዶ/ር) ቡድን ህዝቡ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ እንዲያምፅ የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው በሚል ተከሷል።

ከፌደራል መንግስት በድብቅ " የውጭ ሽምጋይ ሳያስፈልገን ጉዳያችን ብቻችን መጨረስ እንችላለን " በማለት ስልጣን ይለምናልም ተብሏል።

" ቡድኑ ከስልጣን ውጪ የትግራይ ህዝብ ጉዳይ እንደ ጉዳዩ የማይቆጥር ራስ ወዳድ " ሲል አቶ ጌታቸው የሚመሩት ህወሓት አብጠልጥሎታል።

ከዚህ በተጨማሪ ፤ " ለስልጣን ሲል ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዳይመለሱ የመከልከል እና የማደናቀፍ ስራውን ቀጥሎበታል ፣ ዴሞብላይዜሽን (DDR) እንዲደናቀፍ ሴራዎች እየሸረበ ነው " ሲል ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ ቃሉ እና ተግባሩ ለየቅል ናቸው ፤ የህዝብ ችግር እና መከራ እንዳይፈታ በማወሳሰብ እንደ ምክንያት ተጠቅሞ ህዝብን እና መንግስት በማቃቃር በአመፅ ስልጣን ላይ ለመቆየት  ሙጥኝ ያለ ፀረ ህዝብ ነው " ሲል  ፈርጆታል።

የትግራይ ህዝብ ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጡት አስተዳደራዊ ፣ ፓለቲካዊ ተልእኮዎች በተሰጠው ጊዜ አጠናቅቆ በህዝብ የተመረጠ መደበኛ መንግስት እንዲኖር የሚደረገው ትግል በመደገፍ  " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል የጠራውን የነ ደብረጽዮን (ዶ/ር) ቢድን " የሚያካሂደውን አፍራሽ ተግባር በፅኑ እንዲቃወመውና እንዲያመክነው ጥሪውን አቅርቧል።

ከትላትና በስቲያ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ፤ በምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " በትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ክህደት የፈፀመ ቡድን " ሲል መፈረጁ ይታወሳል።

አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በተገኙበት ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመሩት ውይይት ቢደረግም ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ጠንከር ባሉ መግለጫዎች አንድ ሁለት እየተባባሉ ነው።

የመግለጫዎቹ ይዘት ጠንካራ ከመሆናቸው አልፎ እየተወረወሩ ያሉት ቃላት ነገሩ ከመርገብ ይልቅ እየተካረረ እየሄደ እንዳለ ማሳያ ናቸው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/92842
Create:
Last Update:

#Tigray

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " - በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት

ለሁለት በተከፈሉት የህወሓት አመራሮች መካከል ያለው የመግለጫ ምልልስ አሁንም ቀጥሏል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ፤ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም ላወጣው መግለጫ መልስ ሰጥቷል።

በዚህም በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል ፈርጆታል። 

" በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደር ቃሉን አጥፈዋል በአጭር ጊዜ ልኩ ለማስገባት በማካሂደው ትግል ህዝቡ ከጎኔ ይቁም የሚል የሚያስደምም መግለጫ ታህሳስ 2/2017 ዓ.ም በመገናኛ ብዙሃን አሰራጭቷል " ሲል የአቶ ጌታቸው ቡድን ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድን " በመባል የተገለፀው በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " የፌደራል መንግስት የጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት በሁለት ሳምንት እንዲነሳ ቀጠሮ ተሰጥቶኛል " ሲል እንዳልቆየ " ጊዚያዊ አስተዳደሩን በአጭር ጊዜ መልክ ለማስያዝ ወሰኜ ቃል ገብቻለሁ ተከተሉኝ " የሚል የክተት ጥሪ አቅርቧል ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" የዚህ አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ አካሄድ ለህዝብ አዲስ አይፈለም " ያለው መግለጫው  " ቡድኑ ከፌደራል መንግስት የሚነጋገረው እና የሚስማማው ሌላ ለትግራይ ህዝብ የሚለው ደግሞ ሌላ " ሲል ገልፆታል።

" ከፌደራል መንግስት ስልጣን  እንዲቸረው የሚለምን አማፂ እና ቂመኛ ቡድን ሌሎችን በባንዳነትና እና በክህደት ለመፈረጅ መድፈሩ አስደማሚ ነው " ሲል  በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት ገልጿል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ የትግራይን ህዝብ ከፌደራል መንግስት የሚያጋጭ አቅጣጫ እየተከተለ መሆኑ ያወጣው መግለጫ አመላካች ነው " ሲል አክሏል።

የደብረጽዮን (ዶ/ር) ቡድን ህዝቡ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ላይ እንዲያምፅ የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው በሚል ተከሷል።

ከፌደራል መንግስት በድብቅ " የውጭ ሽምጋይ ሳያስፈልገን ጉዳያችን ብቻችን መጨረስ እንችላለን " በማለት ስልጣን ይለምናልም ተብሏል።

" ቡድኑ ከስልጣን ውጪ የትግራይ ህዝብ ጉዳይ እንደ ጉዳዩ የማይቆጥር ራስ ወዳድ " ሲል አቶ ጌታቸው የሚመሩት ህወሓት አብጠልጥሎታል።

ከዚህ በተጨማሪ ፤ " ለስልጣን ሲል ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዳይመለሱ የመከልከል እና የማደናቀፍ ስራውን ቀጥሎበታል ፣ ዴሞብላይዜሽን (DDR) እንዲደናቀፍ ሴራዎች እየሸረበ ነው " ሲል ከሷል።

" አማፂ እና ቂመኛ ቡድኑ ቃሉ እና ተግባሩ ለየቅል ናቸው ፤ የህዝብ ችግር እና መከራ እንዳይፈታ በማወሳሰብ እንደ ምክንያት ተጠቅሞ ህዝብን እና መንግስት በማቃቃር በአመፅ ስልጣን ላይ ለመቆየት  ሙጥኝ ያለ ፀረ ህዝብ ነው " ሲል  ፈርጆታል።

የትግራይ ህዝብ ጊዚያዊ አስተዳደሩ የተሰጡት አስተዳደራዊ ፣ ፓለቲካዊ ተልእኮዎች በተሰጠው ጊዜ አጠናቅቆ በህዝብ የተመረጠ መደበኛ መንግስት እንዲኖር የሚደረገው ትግል በመደገፍ  " አማፂ እና ቂመኛ " ሲል የጠራውን የነ ደብረጽዮን (ዶ/ር) ቢድን " የሚያካሂደውን አፍራሽ ተግባር በፅኑ እንዲቃወመውና እንዲያመክነው ጥሪውን አቅርቧል።

ከትላትና በስቲያ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ፤ በምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ህወሓት " በትግራይ ህዝብ ብሄራዊ ክህደት የፈፀመ ቡድን " ሲል መፈረጁ ይታወሳል።

አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በተገኙበት ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመሩት ውይይት ቢደረግም ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ጠንከር ባሉ መግለጫዎች አንድ ሁለት እየተባባሉ ነው።

የመግለጫዎቹ ይዘት ጠንካራ ከመሆናቸው አልፎ እየተወረወሩ ያሉት ቃላት ነገሩ ከመርገብ ይልቅ እየተካረረ እየሄደ እንዳለ ማሳያ ናቸው።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/92842

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram has become more interventionist over time, and has steadily increased its efforts to shut down these accounts. But this has also meant that the company has also engaged with lawmakers more generally, although it maintains that it doesn’t do so willingly. For instance, in September 2021, Telegram reportedly blocked a chat bot in support of (Putin critic) Alexei Navalny during Russia’s most recent parliamentary elections. Pavel Durov was quoted at the time saying that the company was obliged to follow a “legitimate” law of the land. He added that as Apple and Google both follow the law, to violate it would give both platforms a reason to boot the messenger from its stores. The Securities and Exchange Board of India (Sebi) had carried out a similar exercise in 2017 in a matter related to circulation of messages through WhatsApp. But because group chats and the channel features are not end-to-end encrypted, Galperin said user privacy is potentially under threat. After fleeing Russia, the brothers founded Telegram as a way to communicate outside the Kremlin's orbit. They now run it from Dubai, and Pavel Durov says it has more than 500 million monthly active users. Telegram was founded in 2013 by two Russian brothers, Nikolai and Pavel Durov.
from ca


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American