Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
“ዶክተር አንዷለም ተተኩሶበት ተመትቶ ተገኘ መኪናው ውስጥ። አንድ ሀኪማችንም ተተኩሶበት መኪናው ሁለት፤ ሦስቴ ተመትቶታል” - ጤና ሳይንስ ኮሌጁ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥበበ ግዮን ግቢ ስፔሻላንስድ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር አንዷለም ዳኘ በተተኮሰባቸው ጥይት መገዳላቸውን ዩኒቨርሲቲውና ኢንተርን ሀኪሞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ለደህንነታቸው…
' በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን ! '

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት በፊት ሥራ ቦታ ላይ አንድ የኮሌጁ ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” - የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር

የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር (ባሕር ዳር) “በጥይት ተገደሉ” በተባሉት በዶክተር አንዷለም ዳኘ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፤ “ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ማኀበሩ ይህን ያለው በኮሌጁ አካላትም ሆነ በኢንተርን ሀኪሞች የግድያና የዘረፋ ሙከራዎች እየተደረጉባቸው መሆናቸውን በመግለጽ ጭምር ነው።

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት  በፊት ሥራ ስራ ቦታ ላይ የነበረ አንድ የህክምና ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” ሲልም አስታውሷል።

ማኀበሩ ስለዶክተር አንዷለም ግድያና ስለስጋቱ ምን አሉ?

“ የዶክተር አንዷለም ዳኘ የቀብር ሥነ ስርዓት በድባንቄ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

ዶክተር አንዷለም ትሁት ሀኪም ነበር። ስለሞተ ሳይሆን እውነታው ይሄው ስለሆነ ነው ይህን የምንለው። ስለሞተ ለመሞጋገስ አይደለም። ከሰውም ሰው ስለነበር እንጂ።

አሟሟቱም ልብ ሰባሪ ነው። ሙያው ሰብ ስፔሻሊስት ነው። አንቱ በሚባልበትና ህዝብን የሚያገለግልበት እድሜ ላይ ነው ያጣነው። እንደ ህክምና ተማሪዎች የእውቀት አባታችንን፤ ወንድማችንን ነው ያጣነው።

ይህን የመሰለ ሰብ ስፔሻሊቲ ሀኪም ማጣት እንደ ሀገርም እንደ ህዝብም በጣም ያማል። መራር ሀዘን ገጥሞናል።

በነገራችን ላይ ተደጋጋሚ ችግሮች አሉ። የሆስፒታሉ ዳይሬክተር ስልክ ተቀምቶ፣ በሽጉጥ ማንገራገር ገጥሞት ነበር፤ በኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ይደረጋል።

በዚሁ የተነሳ ሰብ ስፔሻሊስቶች አገር እየለቀቁ፤ እየሸሹ ነው። ይሄ ባለበት ሁኔታ ጥበቃ፣ ከለላ አለመደረጉ በጣም ያሳዝናል። በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን። የሆስፒታሉ ኃላፊ፣ ኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ተደርጎባቸል።

የኮሌጁ ኃላፊዎችም ከአቅማቸው በላይ የሆነባቸው ይመስለናል። ምንም ከለላ የለም። ግቢ ያሉ ጥበቃዎችም የተጠናከረ አይደለም። ውጪ ላይ ይቅርና ግቢ ውስጥ ራሱ ከፍተኛ ስጋት አለ። አቤት የምንልበት አጥተን ነው እንጂ ” ብሏል።

በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎች መጪውን ጊዜ ለማስተካከል እንዲተጉ፣ ስለመብታቸው ዘብ እንዲቆሙ፣ አንድነት በመፍጠር የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ ማኀበሩ አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94208
Create:
Last Update:

' በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን ! '

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት በፊት ሥራ ቦታ ላይ አንድ የኮሌጁ ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” - የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር

የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር (ባሕር ዳር) “በጥይት ተገደሉ” በተባሉት በዶክተር አንዷለም ዳኘ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፤ “ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ማኀበሩ ይህን ያለው በኮሌጁ አካላትም ሆነ በኢንተርን ሀኪሞች የግድያና የዘረፋ ሙከራዎች እየተደረጉባቸው መሆናቸውን በመግለጽ ጭምር ነው።

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት  በፊት ሥራ ስራ ቦታ ላይ የነበረ አንድ የህክምና ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” ሲልም አስታውሷል።

ማኀበሩ ስለዶክተር አንዷለም ግድያና ስለስጋቱ ምን አሉ?

“ የዶክተር አንዷለም ዳኘ የቀብር ሥነ ስርዓት በድባንቄ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

ዶክተር አንዷለም ትሁት ሀኪም ነበር። ስለሞተ ሳይሆን እውነታው ይሄው ስለሆነ ነው ይህን የምንለው። ስለሞተ ለመሞጋገስ አይደለም። ከሰውም ሰው ስለነበር እንጂ።

አሟሟቱም ልብ ሰባሪ ነው። ሙያው ሰብ ስፔሻሊስት ነው። አንቱ በሚባልበትና ህዝብን የሚያገለግልበት እድሜ ላይ ነው ያጣነው። እንደ ህክምና ተማሪዎች የእውቀት አባታችንን፤ ወንድማችንን ነው ያጣነው።

ይህን የመሰለ ሰብ ስፔሻሊቲ ሀኪም ማጣት እንደ ሀገርም እንደ ህዝብም በጣም ያማል። መራር ሀዘን ገጥሞናል።

በነገራችን ላይ ተደጋጋሚ ችግሮች አሉ። የሆስፒታሉ ዳይሬክተር ስልክ ተቀምቶ፣ በሽጉጥ ማንገራገር ገጥሞት ነበር፤ በኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ይደረጋል።

በዚሁ የተነሳ ሰብ ስፔሻሊስቶች አገር እየለቀቁ፤ እየሸሹ ነው። ይሄ ባለበት ሁኔታ ጥበቃ፣ ከለላ አለመደረጉ በጣም ያሳዝናል። በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን። የሆስፒታሉ ኃላፊ፣ ኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ተደርጎባቸል።

የኮሌጁ ኃላፊዎችም ከአቅማቸው በላይ የሆነባቸው ይመስለናል። ምንም ከለላ የለም። ግቢ ያሉ ጥበቃዎችም የተጠናከረ አይደለም። ውጪ ላይ ይቅርና ግቢ ውስጥ ራሱ ከፍተኛ ስጋት አለ። አቤት የምንልበት አጥተን ነው እንጂ ” ብሏል።

በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎች መጪውን ጊዜ ለማስተካከል እንዲተጉ፣ ስለመብታቸው ዘብ እንዲቆሙ፣ አንድነት በመፍጠር የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ ማኀበሩ አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA









Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94208

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

But the Ukraine Crisis Media Center's Tsekhanovska points out that communications are often down in zones most affected by the war, making this sort of cross-referencing a luxury many cannot afford. A Russian Telegram channel with over 700,000 followers is spreading disinformation about Russia's invasion of Ukraine under the guise of providing "objective information" and fact-checking fake news. Its influence extends beyond the platform, with major Russian publications, government officials, and journalists citing the page's posts. But because group chats and the channel features are not end-to-end encrypted, Galperin said user privacy is potentially under threat. "We as Ukrainians believe that the truth is on our side, whether it's truth that you're proclaiming about the war and everything else, why would you want to hide it?," he said. DFR Lab sent the image through Microsoft Azure's Face Verification program and found that it was "highly unlikely" that the person in the second photo was the same as the first woman. The fact-checker Logically AI also found the claim to be false. The woman, Olena Kurilo, was also captured in a video after the airstrike and shown to have the injuries.
from ca


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American