Telegram Group & Telegram Channel
🔊 #የሠራተኞችድምጽ

" ቋሚ ሠራተኞች ሆነን ሳለ በደሞዝ ማሻሻያው አልተካተትንም " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ሠራተኞች

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ተከትሎ የሚከሰቱ የኑሮ ዉድነትና ተያያዥ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የመንግስት ሠራተኞች ደሞዝ ማሻሻያ ተደርጎ ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ መሆኑ ይታወቃል።

በሲዳማ ክልል፤ ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን፤ ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሰሩ የመንግስት ሠራተኞች ግን " ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ በቋሚነት ተቀጥረን እየሰራን ያለን ቢሆንም በአዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ አልተካተትንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ቅሬታቸዉን ካደረሱን መካከል ፦
- በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን፣
- ማዘጋጃ ቤቶች፣
- በትምህርት ዘርፍ ፣
- በሴቶችና ሕፃናት እንዲሁም በሕብረት ስራ ጽ/ቤቶች የሚሰሩ ሠራተኞች ናቸው።

" በወቅቱ በአግባቡ ማስታወቂያ ወጥቶ ተመዝግበንና ተወዳድረን ማለፋችን ተረጋግጦ የቋሚነት ደብዳቤ ተሰጥቶን ላለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት ደሞዝ ሲከፈለን በቆየንባቸው መደቦች ላይ እየሰራን ባለንበት በአዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ አለመካተታችን ለዘርፈ ብዙ ችግሮች ዳርጎናል " ብለዋል።

" ለወረዳዉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት እና ለክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ቅሬታችንን በአካልና በፅሁፍ ብናቀርብም ተገቢዉ ምላሽ አልተሰጠንም ጉዳዩን ለኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ለማቅረብ መረጃ እያደራጀን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ፤ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃይሉ አቢኖ ፥ " በወረዳዉ በ2012 ዓ/ም የነበረው አግባብነት በሌለው ቅጥር በአንድ መደብ ሶስትና አራት ሰዎችን በተደራራቢነት የመቅጠር ሁኔታዎች አሁን ለተፈጠረው ችግር ዋነኛ ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከዞኑና የክልሉ ፐብልክ ሰርቪስ ጋር በመናበብ መፍትሔ እያፈላለጉ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

በወቅቱ ይህን ተግባር የፈፀሙ አመራሮች እና የሰዉ ሃብት ልማት ኃላፊዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የሚናገሩት ኃላፊዉ በወረዳዉ በዚህ መልክ ተጠቀጥረዉ በአዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ያልካተቱና በቀጣይ መፍትሔ የሚፈለግላቸዉ 470 በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ዉስጥ የተለዩ ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ አክለዋል።

የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ፐብልክ ሰርቪስና የሰዉ ሃይል ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በዛብህ ባርሶ በበኩላቸው በ2011 እና 2012 በአከባቢው ሕገወጥ ቅጥሮች መፈፀማቸውን ገልጸዋል።

በወረዳዉ አጣሪ ቡድን ተቋቁሞ በአዲሱ ደሞዝ ያልተካተቱንና በወረዳው ቅጥር ያልተፈፀመባቸዉ ክፍት መደቦችን የመለየት ስራ መከናወኑን አንስተዉ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ብቻ 407 ክፍት መደቦች መኖራቸዉን ለማወቅ መቻሉን ገልፀዋል።

የክልሉ የበላይ አመራሮች በሚያስቀምጡት አቅጣጫ መሰረት እነዚህን ሠራተኞች በነዚህ ክፍት መደቦች የመደልደልና ሌሎችም ሕጋዊ አመራጮች በመፈለግ በአጭር ጊዜ ዉስጥ እልባት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስከመጨረሻ ተከታትሎ መረጃውን ይልካል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94381
Create:
Last Update:

🔊 #የሠራተኞችድምጽ

" ቋሚ ሠራተኞች ሆነን ሳለ በደሞዝ ማሻሻያው አልተካተትንም " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ሠራተኞች

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ተከትሎ የሚከሰቱ የኑሮ ዉድነትና ተያያዥ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የመንግስት ሠራተኞች ደሞዝ ማሻሻያ ተደርጎ ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ መሆኑ ይታወቃል።

በሲዳማ ክልል፤ ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን፤ ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሰሩ የመንግስት ሠራተኞች ግን " ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ በቋሚነት ተቀጥረን እየሰራን ያለን ቢሆንም በአዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ አልተካተትንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ቅሬታቸዉን ካደረሱን መካከል ፦
- በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን፣
- ማዘጋጃ ቤቶች፣
- በትምህርት ዘርፍ ፣
- በሴቶችና ሕፃናት እንዲሁም በሕብረት ስራ ጽ/ቤቶች የሚሰሩ ሠራተኞች ናቸው።

" በወቅቱ በአግባቡ ማስታወቂያ ወጥቶ ተመዝግበንና ተወዳድረን ማለፋችን ተረጋግጦ የቋሚነት ደብዳቤ ተሰጥቶን ላለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት ደሞዝ ሲከፈለን በቆየንባቸው መደቦች ላይ እየሰራን ባለንበት በአዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ አለመካተታችን ለዘርፈ ብዙ ችግሮች ዳርጎናል " ብለዋል።

" ለወረዳዉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት እና ለክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ቅሬታችንን በአካልና በፅሁፍ ብናቀርብም ተገቢዉ ምላሽ አልተሰጠንም ጉዳዩን ለኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ለማቅረብ መረጃ እያደራጀን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ፤ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃይሉ አቢኖ ፥ " በወረዳዉ በ2012 ዓ/ም የነበረው አግባብነት በሌለው ቅጥር በአንድ መደብ ሶስትና አራት ሰዎችን በተደራራቢነት የመቅጠር ሁኔታዎች አሁን ለተፈጠረው ችግር ዋነኛ ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከዞኑና የክልሉ ፐብልክ ሰርቪስ ጋር በመናበብ መፍትሔ እያፈላለጉ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

በወቅቱ ይህን ተግባር የፈፀሙ አመራሮች እና የሰዉ ሃብት ልማት ኃላፊዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የሚናገሩት ኃላፊዉ በወረዳዉ በዚህ መልክ ተጠቀጥረዉ በአዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ያልካተቱና በቀጣይ መፍትሔ የሚፈለግላቸዉ 470 በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ዉስጥ የተለዩ ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ አክለዋል።

የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ፐብልክ ሰርቪስና የሰዉ ሃይል ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በዛብህ ባርሶ በበኩላቸው በ2011 እና 2012 በአከባቢው ሕገወጥ ቅጥሮች መፈፀማቸውን ገልጸዋል።

በወረዳዉ አጣሪ ቡድን ተቋቁሞ በአዲሱ ደሞዝ ያልተካተቱንና በወረዳው ቅጥር ያልተፈፀመባቸዉ ክፍት መደቦችን የመለየት ስራ መከናወኑን አንስተዉ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ብቻ 407 ክፍት መደቦች መኖራቸዉን ለማወቅ መቻሉን ገልፀዋል።

የክልሉ የበላይ አመራሮች በሚያስቀምጡት አቅጣጫ መሰረት እነዚህን ሠራተኞች በነዚህ ክፍት መደቦች የመደልደልና ሌሎችም ሕጋዊ አመራጮች በመፈለግ በአጭር ጊዜ ዉስጥ እልባት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስከመጨረሻ ተከታትሎ መረጃውን ይልካል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94381

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Two days after Russia invaded Ukraine, an account on the Telegram messaging platform posing as President Volodymyr Zelenskiy urged his armed forces to surrender. Telegram, which does little policing of its content, has also became a hub for Russian propaganda and misinformation. Many pro-Kremlin channels have become popular, alongside accounts of journalists and other independent observers. READ MORE Telegram has become more interventionist over time, and has steadily increased its efforts to shut down these accounts. But this has also meant that the company has also engaged with lawmakers more generally, although it maintains that it doesn’t do so willingly. For instance, in September 2021, Telegram reportedly blocked a chat bot in support of (Putin critic) Alexei Navalny during Russia’s most recent parliamentary elections. Pavel Durov was quoted at the time saying that the company was obliged to follow a “legitimate” law of the land. He added that as Apple and Google both follow the law, to violate it would give both platforms a reason to boot the messenger from its stores. Lastly, the web previews of t.me links have been given a new look, adding chat backgrounds and design elements from the fully-features Telegram Web client.
from ca


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American