Telegram Group & Telegram Channel
“ ገዢው ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም ” - አዲሱ  የመኢአድ ተሿሚ ፕሬዜዳንት

መላው ኢትዮጵያ አንድነት ደርጅት (መኢአድ) በቅርቡ ፓርቲውን ለስድስት ዓመታት በመሩት አቶ ማሙሸት አማረ ምትክ አቶ አብርሃም ጌጡን ፕሬዜዳንት አድርጎ ሾሟል።

አንዲሱ የፓርቲው ፕሬዜዳንትም ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገዢውን ፓርቲ በብርቱ ተችተዋል።

" ጠባብ " የሚል ትችት የሚሰነዘርበት የኢትዮጵያ የፓለቲካ ምህዳርን ለመቋቋም ምን ያህል ተዘጋጅተዋል ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ተሿሚው ብርቱ ትችት ያነገበ ምላሽ ሰጥተዋል።

አዲሱ የመኢዓድ ተሿሚ ፕሬዚዳንት አቶ አብርሃም ጌጡ ምን አሉ ?

“ እንደ ተመራጭ መሪ በድንገት አይደለም የመጣሁት፡፡ ለ26 አካካቢ ዓመታት ፖልቲካሊ አክቲቭ ሆኘ ረጅም ትግል እያደረኩ ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር የመኢአድ አባላትም ከፍተኛውን ድምጽ ሰጥተውኛል፡፡

በኢትዮጵያ ፖለቲካ መጻዒው እጣ ፋንታችን ስናየው እውነት ለመናገር የአሁኑን ገዢ ፓርቲ ፓርቲ ነው ብለን ለመናገርም ይከብዳል፡፡ ገዢ ፓርቲ የሚባለው ሁሉንም እኩል የሚገዛ ነውና፡፡ መልቲ ፓርቲ ሲስተም የተገነባባቸው ዓለማት የሚመሩት በዴሞክራሲ ህግ ነው፡፡

የዴሞክራሲ ስርዓት የሚያድግ የነበረው ደግሞ በዚያች አገር በሚኖረው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ የኛ አገር የፖለቲካ ሂደትና ባህሪ ምን ነበር ? አሁንስ ምን እየሆንን ነው? ብለን ስናስብ ገዢ ፓርቲ አለ ማለት አይቻልም፡፡ 

ገዢ ፓርቲ የፖለቲካ ስፔሱ ነጻ ሆኖ የፓለቲካ አክተሮች ሜዳው ላይ ወርደው፣ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ ሰጥተው መራጩም ተመራጩም ተሳትፎ ወደ ስልጣን የሚመጣበት መሆን አለበት፡፡

የመረጠውንም ያልመረጠውንም እኩል ማስተዳደር፣ ኃላፊነቱን፣ ግዴታውን ሲወጣ ገዢ ፓርቲ ይባላል፡፡ ከዚህ አንፃር ገዢውን ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም፡፡ ፓርቲ በውስጡ ብዙ ነገሮችን መያዝ አለበት።

የፓለቲካ ፓርቲ ማለት የራሱ ፕሮግራም፣ ርዕዮተዓለም፣ አደረጃጀት ያለው ነው፡፡ አሁን ስልጣን ላይ ያለው የፖለቲካ ኃይል ፋንዳሜንታል የሆኑ ነገሮች በውስጡ የሉትም፡

ዝም ብሎ የተደራጀ፣ የሕዝብ፣ ብሶትና ትግል በአጋጣሚ አስፈንጥሮ ወስዶ ቤተ መንግስት ያስቀመጠው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ ህዝቡ ከነበረበት የለውጥ ፍላጎት ተነስቶ መርጦታል፡፡ 

ከተመረጠ በኋላ ግን አገሪቱ ወዴት እየሄደች ነው? ምንድን ነው የሆነችው? ሰርቫይዝ ማድረግ የምትችልብት መሰረታዊ አገራዊ ምሰሶዎች አሉ ወይ? ተብሎ ሲታሰብ በጣም አደጋ ነው፡፡ 

ድሮ ኢትዮጵያ መስቀልኛ ጥያቄ ገብታለች እንል ነበር። መስቀልኛ ጥያቄ የሚባለው በመስቀልኛ ቦታ ተቁሞ ግራ ቀኝ ሲታይ ነውና አሁን ግን መቆምም አይቻለም፡፡ መቆሚያ፣ መንቀሳቀሻ መሬት የለም።

የጸጥታና ሰላምን የሚያስከብር ኃይል በሌለበት ቀጣይ የአገሪቱ የፖለቲካ እጣፋንታ ምን ይሆናል? ለሚለው ጥያቄ ፈጣሪ እጁን ዘርግቶ ኢትዮጵያን ካልጠበቃት አሁን ባለው ተጨባጪ ሁኔታ ከባድ አደጋ ላይ ናት።

ይህን ብለን ግን በዝምታ ቁጭ እንልም፡፡ መኢዓድ ፓርቲ ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም በቀጣይ አሸናፊ ሆኖ ሊወጣ ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም የአንድንት ኃይሎች የሚባሉትን አሰብስብን የፖለቲካ ትግል ያደርጋል።

መንግስት የህዝብን ድምጽና ሰቆቃ አዳምጦ የፖለቲካ መፍትሄ ሊሰጥ ተቋቋመ ተቋም መሆን አለበትና አብሶሉት ሞናርኪዎች ሲያደርጉት እንደነበረው እንዲያደርግ አንፈቅድለትም፡፡ ለዚህም ብርቱ ትግል እናደርጋለን፡፡
 
ሰው ሚያሳድዱ፣ የሚያግቱ፣ በመሳሪያ የሚጨፈጭፉ አካላት ስልጣንን መከታ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ግን በየትኛውም መስኮት ሂደው መደበቅ አይችሉም፡፡ ይህን እንነግራቸዋለን። የፖለቲካ ጥበቡ ለህዝብ መፍትሄ መፈለግ ነውና እሱን እናሳያለን ” ብለዋል።


በቀጣዩ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ያላቸውን ዝግጅትና ፓለቲካዊ አስቻይ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ጠይቀናቸው በሰጡን ምላሽ፣ “ የመጀመሪያ ስራችን በምርጫና ሥራ ወደ ስልጣን መምጣት ነው ” ሲሉ መልሰዋል።

“ ይህን ለማድረግ ጠንክረን እንሰራለን። ህዝቡ በቲፎዞ ካርድ መብቱን ሰጥቶ እንደአሁኑ ቤቱ እንዲፈርስ፣ ህልውናውን እንዲያጣ አናደርግም። ኢትዮጵያ በከፍተኛ ችግር እንዳለች የሚጠባ ህጻን የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡ ይህንን አስተካክለን ጥሩ ተመራጮች ሆነን ለመቅረብ ዝግጅት እያደረግን ነው ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94387
Create:
Last Update:

“ ገዢው ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም ” - አዲሱ  የመኢአድ ተሿሚ ፕሬዜዳንት

መላው ኢትዮጵያ አንድነት ደርጅት (መኢአድ) በቅርቡ ፓርቲውን ለስድስት ዓመታት በመሩት አቶ ማሙሸት አማረ ምትክ አቶ አብርሃም ጌጡን ፕሬዜዳንት አድርጎ ሾሟል።

አንዲሱ የፓርቲው ፕሬዜዳንትም ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገዢውን ፓርቲ በብርቱ ተችተዋል።

" ጠባብ " የሚል ትችት የሚሰነዘርበት የኢትዮጵያ የፓለቲካ ምህዳርን ለመቋቋም ምን ያህል ተዘጋጅተዋል ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ተሿሚው ብርቱ ትችት ያነገበ ምላሽ ሰጥተዋል።

አዲሱ የመኢዓድ ተሿሚ ፕሬዚዳንት አቶ አብርሃም ጌጡ ምን አሉ ?

“ እንደ ተመራጭ መሪ በድንገት አይደለም የመጣሁት፡፡ ለ26 አካካቢ ዓመታት ፖልቲካሊ አክቲቭ ሆኘ ረጅም ትግል እያደረኩ ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር የመኢአድ አባላትም ከፍተኛውን ድምጽ ሰጥተውኛል፡፡

በኢትዮጵያ ፖለቲካ መጻዒው እጣ ፋንታችን ስናየው እውነት ለመናገር የአሁኑን ገዢ ፓርቲ ፓርቲ ነው ብለን ለመናገርም ይከብዳል፡፡ ገዢ ፓርቲ የሚባለው ሁሉንም እኩል የሚገዛ ነውና፡፡ መልቲ ፓርቲ ሲስተም የተገነባባቸው ዓለማት የሚመሩት በዴሞክራሲ ህግ ነው፡፡

የዴሞክራሲ ስርዓት የሚያድግ የነበረው ደግሞ በዚያች አገር በሚኖረው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ የኛ አገር የፖለቲካ ሂደትና ባህሪ ምን ነበር ? አሁንስ ምን እየሆንን ነው? ብለን ስናስብ ገዢ ፓርቲ አለ ማለት አይቻልም፡፡ 

ገዢ ፓርቲ የፖለቲካ ስፔሱ ነጻ ሆኖ የፓለቲካ አክተሮች ሜዳው ላይ ወርደው፣ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ ሰጥተው መራጩም ተመራጩም ተሳትፎ ወደ ስልጣን የሚመጣበት መሆን አለበት፡፡

የመረጠውንም ያልመረጠውንም እኩል ማስተዳደር፣ ኃላፊነቱን፣ ግዴታውን ሲወጣ ገዢ ፓርቲ ይባላል፡፡ ከዚህ አንፃር ገዢውን ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም፡፡ ፓርቲ በውስጡ ብዙ ነገሮችን መያዝ አለበት።

የፓለቲካ ፓርቲ ማለት የራሱ ፕሮግራም፣ ርዕዮተዓለም፣ አደረጃጀት ያለው ነው፡፡ አሁን ስልጣን ላይ ያለው የፖለቲካ ኃይል ፋንዳሜንታል የሆኑ ነገሮች በውስጡ የሉትም፡

ዝም ብሎ የተደራጀ፣ የሕዝብ፣ ብሶትና ትግል በአጋጣሚ አስፈንጥሮ ወስዶ ቤተ መንግስት ያስቀመጠው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ ህዝቡ ከነበረበት የለውጥ ፍላጎት ተነስቶ መርጦታል፡፡ 

ከተመረጠ በኋላ ግን አገሪቱ ወዴት እየሄደች ነው? ምንድን ነው የሆነችው? ሰርቫይዝ ማድረግ የምትችልብት መሰረታዊ አገራዊ ምሰሶዎች አሉ ወይ? ተብሎ ሲታሰብ በጣም አደጋ ነው፡፡ 

ድሮ ኢትዮጵያ መስቀልኛ ጥያቄ ገብታለች እንል ነበር። መስቀልኛ ጥያቄ የሚባለው በመስቀልኛ ቦታ ተቁሞ ግራ ቀኝ ሲታይ ነውና አሁን ግን መቆምም አይቻለም፡፡ መቆሚያ፣ መንቀሳቀሻ መሬት የለም።

የጸጥታና ሰላምን የሚያስከብር ኃይል በሌለበት ቀጣይ የአገሪቱ የፖለቲካ እጣፋንታ ምን ይሆናል? ለሚለው ጥያቄ ፈጣሪ እጁን ዘርግቶ ኢትዮጵያን ካልጠበቃት አሁን ባለው ተጨባጪ ሁኔታ ከባድ አደጋ ላይ ናት።

ይህን ብለን ግን በዝምታ ቁጭ እንልም፡፡ መኢዓድ ፓርቲ ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም በቀጣይ አሸናፊ ሆኖ ሊወጣ ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም የአንድንት ኃይሎች የሚባሉትን አሰብስብን የፖለቲካ ትግል ያደርጋል።

መንግስት የህዝብን ድምጽና ሰቆቃ አዳምጦ የፖለቲካ መፍትሄ ሊሰጥ ተቋቋመ ተቋም መሆን አለበትና አብሶሉት ሞናርኪዎች ሲያደርጉት እንደነበረው እንዲያደርግ አንፈቅድለትም፡፡ ለዚህም ብርቱ ትግል እናደርጋለን፡፡
 
ሰው ሚያሳድዱ፣ የሚያግቱ፣ በመሳሪያ የሚጨፈጭፉ አካላት ስልጣንን መከታ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ግን በየትኛውም መስኮት ሂደው መደበቅ አይችሉም፡፡ ይህን እንነግራቸዋለን። የፖለቲካ ጥበቡ ለህዝብ መፍትሄ መፈለግ ነውና እሱን እናሳያለን ” ብለዋል።


በቀጣዩ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ያላቸውን ዝግጅትና ፓለቲካዊ አስቻይ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ጠይቀናቸው በሰጡን ምላሽ፣ “ የመጀመሪያ ስራችን በምርጫና ሥራ ወደ ስልጣን መምጣት ነው ” ሲሉ መልሰዋል።

“ ይህን ለማድረግ ጠንክረን እንሰራለን። ህዝቡ በቲፎዞ ካርድ መብቱን ሰጥቶ እንደአሁኑ ቤቱ እንዲፈርስ፣ ህልውናውን እንዲያጣ አናደርግም። ኢትዮጵያ በከፍተኛ ችግር እንዳለች የሚጠባ ህጻን የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡ ይህንን አስተካክለን ጥሩ ተመራጮች ሆነን ለመቅረብ ዝግጅት እያደረግን ነው ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94387

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The regulator said it has been undertaking several campaigns to educate the investors to be vigilant while taking investment decisions based on stock tips. The Security Service of Ukraine said in a tweet that it was able to effectively target Russian convoys near Kyiv because of messages sent to an official Telegram bot account called "STOP Russian War." You may recall that, back when Facebook started changing WhatsApp’s terms of service, a number of news outlets reported on, and even recommended, switching to Telegram. Pavel Durov even said that users should delete WhatsApp “unless you are cool with all of your photos and messages becoming public one day.” But Telegram can’t be described as a more-secure version of WhatsApp. This ability to mix the public and the private, as well as the ability to use bots to engage with users has proved to be problematic. In early 2021, a database selling phone numbers pulled from Facebook was selling numbers for $20 per lookup. Similarly, security researchers found a network of deepfake bots on the platform that were generating images of people submitted by users to create non-consensual imagery, some of which involved children. Despite Telegram's origins, its approach to users' security has privacy advocates worried.
from ca


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American