Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል አስራ ሶስት
ትዝታ ከቤት እንደወጣች ብሌን በእፎይታ ሶፋው ላይ ተወረወረች። እዮብ ቢሆን እንደዚች አይነቷን አይደለም ለጓደኝነት ለአይንም ቢሆን ይጠየፋት ነበር ስትል አሰበች። መልካቸው ብቻ ነው ለካ የሚመሳሰለው አለች በልቧ። ምንም ስለአልአዛር የግል ህይወት አያገባኝም! ግን ምን ሲሆን ከእንደዚች አይነቷ ጋር ሆነ? ብሌን ከቅሬታዋ በላይ የሚሰማት ብስጭት መንስኤውን አለማወቋ አሳሰባት። ምን አልባት አልአዛርን እንደ እዮብ ቆጥራው ይሆናል። ወይም የወንድሙ ውለታ ስለሱ እንድትጨነቅ አስገድዷትም ይሆናል። ብቻ ተበሳጭታለች። ማታ አልአዛር እስኪመጣ መታገስ አቃታት።

እንደምንም መሸና አልአዛር ቤት መጣ። እራት ካቀረበች በኃላ "ትዝታ የምትባል ሴት መጥታ ነበር።" እዚ ስታጣህ ሱቅ ይኖራል ብዬ ብነግራትም ነገ መጣለው ብላ ሄደች አለች በዝምታ የተዋጠውን ማዕድ በማደፍረስ። እና ምን አለችሽ? የሚያስቀይም ነገር ተናገረችሽ? ጥያቄውን አከታትሎ ጠየቃት። አይ ምንም አልተናገረችም የናትናኤል እጮኛ ነኝ ብዬ ስነግራት ያመነችኝ ትመስላለች ... ብሌን እናቷን ስትዋሻት ሁሌም ታውቅባት ነበር። ትዝታ ግን አለማወቋ አስደስቷታል።

አልአዛር የብሌን ትዝታን ማየት ረፍት ነሳው። የትዝታ መጥፎ ባህሪያቶች ብቻ ሳይሆን ብሌን ከነጭራሹ ከትዝታ ጋር የነበረውን ነገር ባታውቅበት ይመርጣል። ዛሬ ካለወትሮው ወደ ስራ ለምን እንደሄደ አሰበ "ሽሽት" አለ በሆዱ። እኮ ከምን? መልሶ ራሱን ጠየቀ። ከብሌን? እሱማ አይሆንም በሌላ ያሳበበው ስጋቱ እየተገለጠ ነው።

ጠዋት ይወጣል ማታ ይገባል። በሚገናኙበት ጊዜም ብዙም እንዲያወሩ አይፈልግም። የብሌን ትህትና መልክ አነጋገር ለወንዶች ቀዝቃዛ ወጥመድም ነው። በወጥመዱም ላለመያዝ ይሸሻል ግን ስሜቱ ባላወቀው መንገድ የተሸነፈ ይመስላል ወንድሙን እዮብን የከዳ ቃልኪዳኑን ያጠፈ ስሜት እስኪሰማው ያህል።

መሸሻ ፈለገ ከቤቱ የት ይሂድ? ብሌን ደግሞ እሷን ለአይኑ እንኳን የጠላት መስሏታል። ሊያናግራት አለመፈለጉ አይኖቹን ከእሷ ማሸሹ  ለወንድሙ ሞት ተጠያቂ እሷ የሆነች አድርጎ ያሰበ መሰላት። ትክክል ነው ከኔ ውጪ ለእዮብ ሞት ተጠያቂ ማነው? እዮብን ስታስብ በፀፀት ልትሞት ትደርሳለች። ስለ እሱም ላለመስማት ላለማሰብ ጥረት አድርጋለች ግን ከጭንቅላቷ ሊወጣላት አልቻለም። ቀስ በቀስ ድባቴ ውስጥ መግባት ጀመረች። ቀን ላይ ስለነበራት ህይወት አሁን ስላለችበት ስለወደፊቷ በማሰብ ራሷን ታስጨንቃለች። መሽቶም አልአዛር ሲመጣ ከአንድ ሁለት ቃላት ውጪ ንግግር ስለማይኖራቸው የመሰልቸት የተጠያቂነት ስሜቷ አየለባት።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/129
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል አስራ ሶስት
ትዝታ ከቤት እንደወጣች ብሌን በእፎይታ ሶፋው ላይ ተወረወረች። እዮብ ቢሆን እንደዚች አይነቷን አይደለም ለጓደኝነት ለአይንም ቢሆን ይጠየፋት ነበር ስትል አሰበች። መልካቸው ብቻ ነው ለካ የሚመሳሰለው አለች በልቧ። ምንም ስለአልአዛር የግል ህይወት አያገባኝም! ግን ምን ሲሆን ከእንደዚች አይነቷ ጋር ሆነ? ብሌን ከቅሬታዋ በላይ የሚሰማት ብስጭት መንስኤውን አለማወቋ አሳሰባት። ምን አልባት አልአዛርን እንደ እዮብ ቆጥራው ይሆናል። ወይም የወንድሙ ውለታ ስለሱ እንድትጨነቅ አስገድዷትም ይሆናል። ብቻ ተበሳጭታለች። ማታ አልአዛር እስኪመጣ መታገስ አቃታት።

እንደምንም መሸና አልአዛር ቤት መጣ። እራት ካቀረበች በኃላ "ትዝታ የምትባል ሴት መጥታ ነበር።" እዚ ስታጣህ ሱቅ ይኖራል ብዬ ብነግራትም ነገ መጣለው ብላ ሄደች አለች በዝምታ የተዋጠውን ማዕድ በማደፍረስ። እና ምን አለችሽ? የሚያስቀይም ነገር ተናገረችሽ? ጥያቄውን አከታትሎ ጠየቃት። አይ ምንም አልተናገረችም የናትናኤል እጮኛ ነኝ ብዬ ስነግራት ያመነችኝ ትመስላለች ... ብሌን እናቷን ስትዋሻት ሁሌም ታውቅባት ነበር። ትዝታ ግን አለማወቋ አስደስቷታል።

አልአዛር የብሌን ትዝታን ማየት ረፍት ነሳው። የትዝታ መጥፎ ባህሪያቶች ብቻ ሳይሆን ብሌን ከነጭራሹ ከትዝታ ጋር የነበረውን ነገር ባታውቅበት ይመርጣል። ዛሬ ካለወትሮው ወደ ስራ ለምን እንደሄደ አሰበ "ሽሽት" አለ በሆዱ። እኮ ከምን? መልሶ ራሱን ጠየቀ። ከብሌን? እሱማ አይሆንም በሌላ ያሳበበው ስጋቱ እየተገለጠ ነው።

ጠዋት ይወጣል ማታ ይገባል። በሚገናኙበት ጊዜም ብዙም እንዲያወሩ አይፈልግም። የብሌን ትህትና መልክ አነጋገር ለወንዶች ቀዝቃዛ ወጥመድም ነው። በወጥመዱም ላለመያዝ ይሸሻል ግን ስሜቱ ባላወቀው መንገድ የተሸነፈ ይመስላል ወንድሙን እዮብን የከዳ ቃልኪዳኑን ያጠፈ ስሜት እስኪሰማው ያህል።

መሸሻ ፈለገ ከቤቱ የት ይሂድ? ብሌን ደግሞ እሷን ለአይኑ እንኳን የጠላት መስሏታል። ሊያናግራት አለመፈለጉ አይኖቹን ከእሷ ማሸሹ  ለወንድሙ ሞት ተጠያቂ እሷ የሆነች አድርጎ ያሰበ መሰላት። ትክክል ነው ከኔ ውጪ ለእዮብ ሞት ተጠያቂ ማነው? እዮብን ስታስብ በፀፀት ልትሞት ትደርሳለች። ስለ እሱም ላለመስማት ላለማሰብ ጥረት አድርጋለች ግን ከጭንቅላቷ ሊወጣላት አልቻለም። ቀስ በቀስ ድባቴ ውስጥ መግባት ጀመረች። ቀን ላይ ስለነበራት ህይወት አሁን ስላለችበት ስለወደፊቷ በማሰብ ራሷን ታስጨንቃለች። መሽቶም አልአዛር ሲመጣ ከአንድ ሁለት ቃላት ውጪ ንግግር ስለማይኖራቸው የመሰልቸት የተጠያቂነት ስሜቷ አየለባት።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/129

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Stocks closed in the red Friday as investors weighed upbeat remarks from Russian President Vladimir Putin about diplomatic discussions with Ukraine against a weaker-than-expected print on U.S. consumer sentiment. "We as Ukrainians believe that the truth is on our side, whether it's truth that you're proclaiming about the war and everything else, why would you want to hide it?," he said. The Security Service of Ukraine said in a tweet that it was able to effectively target Russian convoys near Kyiv because of messages sent to an official Telegram bot account called "STOP Russian War." He floated the idea of restricting the use of Telegram in Ukraine and Russia, a suggestion that was met with fierce opposition from users. Shortly after, Durov backed off the idea. On Telegram’s website, it says that Pavel Durov “supports Telegram financially and ideologically while Nikolai (Duvov)’s input is technological.” Currently, the Telegram team is based in Dubai, having moved around from Berlin, London and Singapore after departing Russia. Meanwhile, the company which owns Telegram is registered in the British Virgin Islands.
from cn


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American