Telegram Group & Telegram Channel
🔊 #የሠራተኞችድምጽ

" ቋሚ ሠራተኞች ሆነን ሳለ በደሞዝ ማሻሻያው አልተካተትንም " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ሠራተኞች

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ተከትሎ የሚከሰቱ የኑሮ ዉድነትና ተያያዥ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የመንግስት ሠራተኞች ደሞዝ ማሻሻያ ተደርጎ ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ መሆኑ ይታወቃል።

በሲዳማ ክልል፤ ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን፤ ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሰሩ የመንግስት ሠራተኞች ግን " ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ በቋሚነት ተቀጥረን እየሰራን ያለን ቢሆንም በአዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ አልተካተትንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ቅሬታቸዉን ካደረሱን መካከል ፦
- በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን፣
- ማዘጋጃ ቤቶች፣
- በትምህርት ዘርፍ ፣
- በሴቶችና ሕፃናት እንዲሁም በሕብረት ስራ ጽ/ቤቶች የሚሰሩ ሠራተኞች ናቸው።

" በወቅቱ በአግባቡ ማስታወቂያ ወጥቶ ተመዝግበንና ተወዳድረን ማለፋችን ተረጋግጦ የቋሚነት ደብዳቤ ተሰጥቶን ላለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት ደሞዝ ሲከፈለን በቆየንባቸው መደቦች ላይ እየሰራን ባለንበት በአዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ አለመካተታችን ለዘርፈ ብዙ ችግሮች ዳርጎናል " ብለዋል።

" ለወረዳዉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት እና ለክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ቅሬታችንን በአካልና በፅሁፍ ብናቀርብም ተገቢዉ ምላሽ አልተሰጠንም ጉዳዩን ለኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ለማቅረብ መረጃ እያደራጀን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ፤ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃይሉ አቢኖ ፥ " በወረዳዉ በ2012 ዓ/ም የነበረው አግባብነት በሌለው ቅጥር በአንድ መደብ ሶስትና አራት ሰዎችን በተደራራቢነት የመቅጠር ሁኔታዎች አሁን ለተፈጠረው ችግር ዋነኛ ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከዞኑና የክልሉ ፐብልክ ሰርቪስ ጋር በመናበብ መፍትሔ እያፈላለጉ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

በወቅቱ ይህን ተግባር የፈፀሙ አመራሮች እና የሰዉ ሃብት ልማት ኃላፊዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የሚናገሩት ኃላፊዉ በወረዳዉ በዚህ መልክ ተጠቀጥረዉ በአዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ያልካተቱና በቀጣይ መፍትሔ የሚፈለግላቸዉ 470 በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ዉስጥ የተለዩ ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ አክለዋል።

የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ፐብልክ ሰርቪስና የሰዉ ሃይል ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በዛብህ ባርሶ በበኩላቸው በ2011 እና 2012 በአከባቢው ሕገወጥ ቅጥሮች መፈፀማቸውን ገልጸዋል።

በወረዳዉ አጣሪ ቡድን ተቋቁሞ በአዲሱ ደሞዝ ያልተካተቱንና በወረዳው ቅጥር ያልተፈፀመባቸዉ ክፍት መደቦችን የመለየት ስራ መከናወኑን አንስተዉ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ብቻ 407 ክፍት መደቦች መኖራቸዉን ለማወቅ መቻሉን ገልፀዋል።

የክልሉ የበላይ አመራሮች በሚያስቀምጡት አቅጣጫ መሰረት እነዚህን ሠራተኞች በነዚህ ክፍት መደቦች የመደልደልና ሌሎችም ሕጋዊ አመራጮች በመፈለግ በአጭር ጊዜ ዉስጥ እልባት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስከመጨረሻ ተከታትሎ መረጃውን ይልካል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94381
Create:
Last Update:

🔊 #የሠራተኞችድምጽ

" ቋሚ ሠራተኞች ሆነን ሳለ በደሞዝ ማሻሻያው አልተካተትንም " - የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ሠራተኞች

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ተከትሎ የሚከሰቱ የኑሮ ዉድነትና ተያያዥ ጉዳዮችን ታሳቢ በማድረግ የመንግስት ሠራተኞች ደሞዝ ማሻሻያ ተደርጎ ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ መሆኑ ይታወቃል።

በሲዳማ ክልል፤ ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን፤ ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሰሩ የመንግስት ሠራተኞች ግን " ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ በቋሚነት ተቀጥረን እየሰራን ያለን ቢሆንም በአዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ አልተካተትንም " ሲሉ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።

ቅሬታቸዉን ካደረሱን መካከል ፦
- በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን፣
- ማዘጋጃ ቤቶች፣
- በትምህርት ዘርፍ ፣
- በሴቶችና ሕፃናት እንዲሁም በሕብረት ስራ ጽ/ቤቶች የሚሰሩ ሠራተኞች ናቸው።

" በወቅቱ በአግባቡ ማስታወቂያ ወጥቶ ተመዝግበንና ተወዳድረን ማለፋችን ተረጋግጦ የቋሚነት ደብዳቤ ተሰጥቶን ላለፉት አምስትና ስድስት ዓመታት ደሞዝ ሲከፈለን በቆየንባቸው መደቦች ላይ እየሰራን ባለንበት በአዲሱ የደሞዝ ማሻሻያ አለመካተታችን ለዘርፈ ብዙ ችግሮች ዳርጎናል " ብለዋል።

" ለወረዳዉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት እና ለክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ቅሬታችንን በአካልና በፅሁፍ ብናቀርብም ተገቢዉ ምላሽ አልተሰጠንም ጉዳዩን ለኢትዮጵያ እምባ ጠባቂ ተቋም ለማቅረብ መረጃ እያደራጀን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ፤ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰዉ ሃብት ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃይሉ አቢኖ ፥ " በወረዳዉ በ2012 ዓ/ም የነበረው አግባብነት በሌለው ቅጥር በአንድ መደብ ሶስትና አራት ሰዎችን በተደራራቢነት የመቅጠር ሁኔታዎች አሁን ለተፈጠረው ችግር ዋነኛ ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ገልጸዋል።

ከዞኑና የክልሉ ፐብልክ ሰርቪስ ጋር በመናበብ መፍትሔ እያፈላለጉ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

በወቅቱ ይህን ተግባር የፈፀሙ አመራሮች እና የሰዉ ሃብት ልማት ኃላፊዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የሚናገሩት ኃላፊዉ በወረዳዉ በዚህ መልክ ተጠቀጥረዉ በአዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ያልካተቱና በቀጣይ መፍትሔ የሚፈለግላቸዉ 470 በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ዉስጥ የተለዩ ሰራተኞች ስለመኖራቸዉ አክለዋል።

የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ፐብልክ ሰርቪስና የሰዉ ሃይል ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ በዛብህ ባርሶ በበኩላቸው በ2011 እና 2012 በአከባቢው ሕገወጥ ቅጥሮች መፈፀማቸውን ገልጸዋል።

በወረዳዉ አጣሪ ቡድን ተቋቁሞ በአዲሱ ደሞዝ ያልተካተቱንና በወረዳው ቅጥር ያልተፈፀመባቸዉ ክፍት መደቦችን የመለየት ስራ መከናወኑን አንስተዉ በሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ ብቻ 407 ክፍት መደቦች መኖራቸዉን ለማወቅ መቻሉን ገልፀዋል።

የክልሉ የበላይ አመራሮች በሚያስቀምጡት አቅጣጫ መሰረት እነዚህን ሠራተኞች በነዚህ ክፍት መደቦች የመደልደልና ሌሎችም ሕጋዊ አመራጮች በመፈለግ በአጭር ጊዜ ዉስጥ እልባት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስከመጨረሻ ተከታትሎ መረጃውን ይልካል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94381

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The news also helped traders look past another report showing decades-high inflation and shake off some of the volatility from recent sessions. The Bureau of Labor Statistics' February Consumer Price Index (CPI) this week showed another surge in prices even before Russia escalated its attacks in Ukraine. The headline CPI — soaring 7.9% over last year — underscored the sticky inflationary pressures reverberating across the U.S. economy, with everything from groceries to rents and airline fares getting more expensive for everyday consumers. Elsewhere, version 8.6 of Telegram integrates the in-app camera option into the gallery, while a new navigation bar gives quick access to photos, files, location sharing, and more. NEWS In addition, Telegram now supports the use of third-party streaming tools like OBS Studio and XSplit to broadcast live video, allowing users to add overlays and multi-screen layouts for a more professional look. Overall, extreme levels of fear in the market seems to have morphed into something more resembling concern. For example, the Cboe Volatility Index fell from its 2022 peak of 36, which it hit Monday, to around 30 on Friday, a sign of easing tensions. Meanwhile, while the price of WTI crude oil slipped from Sunday’s multiyear high $130 of barrel to $109 a pop. Markets have been expecting heavy restrictions on Russian oil, some of which the U.S. has already imposed, and that would reduce the global supply and bring about even more burdensome inflation.
from de


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American