Telegram Group & Telegram Channel
" ነበሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን ይቀጥላል " -   የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስ ፓስፖርት ዛሬ ይፋ ሆኗል።

ፓስፖርቱ የግለሰቡን ባዮግራፊክ መረጃ ብቻ ሳይሆን የጣት ዐሻራ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ አለው ተብሏል።

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚመረተው ይህ ፓስፖርት፤ የቪዛ ገጾቹ የኢትዮጵያን መልክ የያዙ መሆናቸው ተጠቅሷል።

ይህም ከዚህ ቀደም በውጭ ሀገር አምራች ድርጅት እጅ የነበረውን ዲዛይን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት እንዲሸፈን አድርጓል ተብሏል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በአዲስ የዘርጋው የኢ-ፓስፖርት ሲስተም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና በጃፓኑ ቶፓን ሴኩሪቲ ኢትዮጵያ አ.ማ. አማካይነት የተሰራ ነው።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፤ ነበሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚቀጥል ሲሆን የዕድሳት ጊዜው ሲደርስ በኢ-ፓስፖርት ይተካል ተብሏል።

አገልግሎት መ/ቤቱ ፤ " 14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈትም አገልግሎቱን ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቋል " ያለ ሲሆን " ከአንድ ነጥብ 5 ሚልየን በላይ ኢ-ፓስፖርት ታትሞ ተዘጋጅቷል " ሲል ገልጿል።

አዲሱ የኢ-ፓስፖርት በነበረው ዋጋ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እንደሚሆን የተነገረ ሲሆን  ደንበኞች ባሉበት ፓስፖርታቸውን በፍጥነት ማግኘት እንዲችሉ ያደርጋል ተብሏል።

"  አዲሱን ኢ-ፓስፖርት በሁለት ወር ከ10 ቀን ማግኘት ይቻላል " ሲል አገልግሎቱ አሳውቋል።

የፓስፖርቱ አገልግሎት ጊዜ 10 ዓመት ሲሆን የዜጎችን ጊዜ፣ ገንዘብ እና ጉልበት ይቆጥባል ተብሏል።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊ ዳዊት ፥ " አዲሱ ኢ-ፓስፖርት እስከአሁን ኢትዮጵያ ካላት ፓስፖርት በአይነቱና በደረጃው እጅግ ከፍ ባለ ጥረት የተዘጋጀ የጉዞ ሰነድ ነው " ብለዋል።


#EPA #ICS

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94631
Create:
Last Update:

" ነበሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን ይቀጥላል " -   የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስ ፓስፖርት ዛሬ ይፋ ሆኗል።

ፓስፖርቱ የግለሰቡን ባዮግራፊክ መረጃ ብቻ ሳይሆን የጣት ዐሻራ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ አለው ተብሏል።

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚመረተው ይህ ፓስፖርት፤ የቪዛ ገጾቹ የኢትዮጵያን መልክ የያዙ መሆናቸው ተጠቅሷል።

ይህም ከዚህ ቀደም በውጭ ሀገር አምራች ድርጅት እጅ የነበረውን ዲዛይን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት እንዲሸፈን አድርጓል ተብሏል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በአዲስ የዘርጋው የኢ-ፓስፖርት ሲስተም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና በጃፓኑ ቶፓን ሴኩሪቲ ኢትዮጵያ አ.ማ. አማካይነት የተሰራ ነው።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፤ ነበሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚቀጥል ሲሆን የዕድሳት ጊዜው ሲደርስ በኢ-ፓስፖርት ይተካል ተብሏል።

አገልግሎት መ/ቤቱ ፤ " 14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈትም አገልግሎቱን ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቋል " ያለ ሲሆን " ከአንድ ነጥብ 5 ሚልየን በላይ ኢ-ፓስፖርት ታትሞ ተዘጋጅቷል " ሲል ገልጿል።

አዲሱ የኢ-ፓስፖርት በነበረው ዋጋ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እንደሚሆን የተነገረ ሲሆን  ደንበኞች ባሉበት ፓስፖርታቸውን በፍጥነት ማግኘት እንዲችሉ ያደርጋል ተብሏል።

"  አዲሱን ኢ-ፓስፖርት በሁለት ወር ከ10 ቀን ማግኘት ይቻላል " ሲል አገልግሎቱ አሳውቋል።

የፓስፖርቱ አገልግሎት ጊዜ 10 ዓመት ሲሆን የዜጎችን ጊዜ፣ ገንዘብ እና ጉልበት ይቆጥባል ተብሏል።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊ ዳዊት ፥ " አዲሱ ኢ-ፓስፖርት እስከአሁን ኢትዮጵያ ካላት ፓስፖርት በአይነቱና በደረጃው እጅግ ከፍ ባለ ጥረት የተዘጋጀ የጉዞ ሰነድ ነው " ብለዋል።


#EPA #ICS

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA










Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94631

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Again, in contrast to Facebook, Google and Twitter, Telegram's founder Pavel Durov runs his company in relative secrecy from Dubai. Since its launch in 2013, Telegram has grown from a simple messaging app to a broadcast network. Its user base isn’t as vast as WhatsApp’s, and its broadcast platform is a fraction the size of Twitter, but it’s nonetheless showing its use. While Telegram has been embroiled in controversy for much of its life, it has become a vital source of communication during the invasion of Ukraine. But, if all of this is new to you, let us explain, dear friends, what on Earth a Telegram is meant to be, and why you should, or should not, need to care. Either way, Durov says that he withdrew his resignation but that he was ousted from his company anyway. Subsequently, control of the company was reportedly handed to oligarchs Alisher Usmanov and Igor Sechin, both allegedly close associates of Russian leader Vladimir Putin. Groups are also not fully encrypted, end-to-end. This includes private groups. Private groups cannot be seen by other Telegram users, but Telegram itself can see the groups and all of the communications that you have in them. All of the same risks and warnings about channels can be applied to groups. In addition, Telegram now supports the use of third-party streaming tools like OBS Studio and XSplit to broadcast live video, allowing users to add overlays and multi-screen layouts for a more professional look.
from de


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American