Telegram Group & Telegram Channel
. . . 'ጠናናነቱን' የሚያሳብቁ አይኖቹን እያየው

.....የኔ ፍቅር ታፈቅረኛለህ? እንዲያዘንብልኝ አንዴ የፀሐይዋን መጥለቅ ደግሞ ዘወር ብዬ ካፊያውን እየናፈቅኩ!

........እሱ ዝም... ጭጭ።

ቆይ!! ቃል ማውጣት ስራ ይሆናል? ለእሱማ ጥንብ የሆነበትን ሸክም የሚያራግፍበት ቀሊል የሚጠብቅ ነው የሚመስለው. ... በጣም ይከብደዋል።

....... እ? <የኔ ፍቅር ምን ያህል ታፈቅረኛለህ?> ለወጥ ሳደርግ ይመልስልኝ ይመስል...... የአጠያየቄ አይነት ሁልቆ መሳፍርት የለሁም። ...... ጥያቄ ጎጆዋን እንደቀለሰችብኝ መልስ ደሞ ደጅ ታስጠናኛለች።

.... ማሬ! እስኪ << አፈቅርሻለው >>በለኝ አልኩት እየተልመጠመጥኩ..... ምን አለ አፈንድቶት ቢገላግለኝ የጥያቄ መዝገበ ቃላቴ እኮ ታዘበኝ።

.....ለሽርደዳ ለሽርደዳማ ማንም አይችለውም። ..... ከንፋስ የፈጠነ፣ ከእስትንፋስ የቀረበ ነው። ............ 'በእግረ ደረቅነቴ' ላይ ሲያሽሞጥጥ የሚቀድመው የለም። ምን እሱ ብቻ መዘባበቻ ሲያደርገኝ የአለም ቃላት፣ ዓረፍተነገር፣ አንቀፅ ቀለበት ያሰሩለት ነው የሚመስሉት!!

... ''ለምን አይመልስልኝም?" ቃላት ማውጣት ይከብዳል? ያውም የሰለለ ድምፁን ከእሬት ስልቱ ጋር አዋህዶት ሊያቀርብልኝ

ግን! እኮ ያንን ቃል እወደዋለው እንደተፈታች እንቦሳ ያስፈነድቀኛል።

. . . ፈለግ የወረረውን ጣቱን ፈርሱ ላይ እያንሸራሸረ፣ አልፎ አልፎ እጆቹን ጉሹ በሸሸው አናቱ ላይ ችፍ ያለሁን ላቦቱን እየጠረገ፣ ልማደኛ ጥፍሩን ጭጉኝ በወረሰው ጢሙ ወጋ ወጋ እያደረገ፣ ....እንደ ማስቲካ አላምጦ ጣዕሙ ሲያልቅ ለሚተፋው ቃል ለምንስ እጨነቃለው?

. . . 'ስጋ' የሆነውን 'ቃል' እንኳን የገዛ ወገኖቹ አልተቀበሉትም። "ሰምና ወርቅ" ሲያወጡለት ስንክልክል ብለዋል። ...'የፍጥረትን ሩጫ' የሚያቃጥለው 'ዓረፍተ ነገር' በየጉራንጉሩ እንደ ጭቃ ይለጣጠፉበታል። <አንደበት ዓመፀኛ አለም ነው> ያሻው ፍቅርን ይገድልበታል። የገደለውን ይቀብርበታል። ታዲያ! ለዚ ቃል ነው ደጅ የሚያስጠናኝ? 'የህልም እንጀራ' አሳቅፎ የሚያንከራትተኝ!

.....'ያላበጀውን ፍቅር' በፊደሉ ቢራቀቅበት ምን አለ? ለእሱ ''ማርጃ'' ለእኔ ''የምስራች'' የሆነውን ቢነግረኝ ምን ቸግሮት?

.....<ሀሞቴ ፈሷል> ግን! የመጨረሻ ቃሌን አቀበልኩት

<<የእኔ ውድ በጣም አፈቅርሃለው!>> ጥያቄ አልነበረም። ምላሽም አይሻም!

. . . 'የበጨጨ' አልፎ አልፎ ጥጋ ጥጉን እንደ 'ዳመና' ጥቁር ያጠላበትን ጥርሱን ብልጭ አድርጎ እንደወትሮው በመሰሪ አይኖቹ 'ሴሰኛ' አስተያየቱን መርቆልኝ ..... የአምስት ወር ህፃን ይመስል እየዳኸ በሚንፏቀቁ ቃላቶች

<<አ..ላ...ፈ...ቅ...ርሽም>> አለኝ! ቦምቡን አፈነዳው። ስብርባሪው አልጎዳኝም። እንደሁም በተቃራኒው. . .

.... "ነፍሴ ሃሴት አደረገች". . . "ጮቤ ረገጥኩ". . . "ቦረቅኩ"!
<ውሃ እንደተጠማ ደርቆ መሰነጣጠቅ የጀመረው ተስፋዬ ረሰረሰልኝ> ... ቃሉ ለኔ ኃይል አለው። "ሳይፈቀሩ ማፍቀር ድሌ ነው"። "ምላሽ የሌለው መውደድ የሰባ ፍሪዳ ጮማዬ ነው" ።

አርያም ተስፋዬ (2013)



group-telegram.com/yabsiratesfaye/110
Create:
Last Update:

. . . 'ጠናናነቱን' የሚያሳብቁ አይኖቹን እያየው

.....የኔ ፍቅር ታፈቅረኛለህ? እንዲያዘንብልኝ አንዴ የፀሐይዋን መጥለቅ ደግሞ ዘወር ብዬ ካፊያውን እየናፈቅኩ!

........እሱ ዝም... ጭጭ።

ቆይ!! ቃል ማውጣት ስራ ይሆናል? ለእሱማ ጥንብ የሆነበትን ሸክም የሚያራግፍበት ቀሊል የሚጠብቅ ነው የሚመስለው. ... በጣም ይከብደዋል።

....... እ? <የኔ ፍቅር ምን ያህል ታፈቅረኛለህ?> ለወጥ ሳደርግ ይመልስልኝ ይመስል...... የአጠያየቄ አይነት ሁልቆ መሳፍርት የለሁም። ...... ጥያቄ ጎጆዋን እንደቀለሰችብኝ መልስ ደሞ ደጅ ታስጠናኛለች።

.... ማሬ! እስኪ << አፈቅርሻለው >>በለኝ አልኩት እየተልመጠመጥኩ..... ምን አለ አፈንድቶት ቢገላግለኝ የጥያቄ መዝገበ ቃላቴ እኮ ታዘበኝ።

.....ለሽርደዳ ለሽርደዳማ ማንም አይችለውም። ..... ከንፋስ የፈጠነ፣ ከእስትንፋስ የቀረበ ነው። ............ 'በእግረ ደረቅነቴ' ላይ ሲያሽሞጥጥ የሚቀድመው የለም። ምን እሱ ብቻ መዘባበቻ ሲያደርገኝ የአለም ቃላት፣ ዓረፍተነገር፣ አንቀፅ ቀለበት ያሰሩለት ነው የሚመስሉት!!

... ''ለምን አይመልስልኝም?" ቃላት ማውጣት ይከብዳል? ያውም የሰለለ ድምፁን ከእሬት ስልቱ ጋር አዋህዶት ሊያቀርብልኝ

ግን! እኮ ያንን ቃል እወደዋለው እንደተፈታች እንቦሳ ያስፈነድቀኛል።

. . . ፈለግ የወረረውን ጣቱን ፈርሱ ላይ እያንሸራሸረ፣ አልፎ አልፎ እጆቹን ጉሹ በሸሸው አናቱ ላይ ችፍ ያለሁን ላቦቱን እየጠረገ፣ ልማደኛ ጥፍሩን ጭጉኝ በወረሰው ጢሙ ወጋ ወጋ እያደረገ፣ ....እንደ ማስቲካ አላምጦ ጣዕሙ ሲያልቅ ለሚተፋው ቃል ለምንስ እጨነቃለው?

. . . 'ስጋ' የሆነውን 'ቃል' እንኳን የገዛ ወገኖቹ አልተቀበሉትም። "ሰምና ወርቅ" ሲያወጡለት ስንክልክል ብለዋል። ...'የፍጥረትን ሩጫ' የሚያቃጥለው 'ዓረፍተ ነገር' በየጉራንጉሩ እንደ ጭቃ ይለጣጠፉበታል። <አንደበት ዓመፀኛ አለም ነው> ያሻው ፍቅርን ይገድልበታል። የገደለውን ይቀብርበታል። ታዲያ! ለዚ ቃል ነው ደጅ የሚያስጠናኝ? 'የህልም እንጀራ' አሳቅፎ የሚያንከራትተኝ!

.....'ያላበጀውን ፍቅር' በፊደሉ ቢራቀቅበት ምን አለ? ለእሱ ''ማርጃ'' ለእኔ ''የምስራች'' የሆነውን ቢነግረኝ ምን ቸግሮት?

.....<ሀሞቴ ፈሷል> ግን! የመጨረሻ ቃሌን አቀበልኩት

<<የእኔ ውድ በጣም አፈቅርሃለው!>> ጥያቄ አልነበረም። ምላሽም አይሻም!

. . . 'የበጨጨ' አልፎ አልፎ ጥጋ ጥጉን እንደ 'ዳመና' ጥቁር ያጠላበትን ጥርሱን ብልጭ አድርጎ እንደወትሮው በመሰሪ አይኖቹ 'ሴሰኛ' አስተያየቱን መርቆልኝ ..... የአምስት ወር ህፃን ይመስል እየዳኸ በሚንፏቀቁ ቃላቶች

<<አ..ላ...ፈ...ቅ...ርሽም>> አለኝ! ቦምቡን አፈነዳው። ስብርባሪው አልጎዳኝም። እንደሁም በተቃራኒው. . .

.... "ነፍሴ ሃሴት አደረገች". . . "ጮቤ ረገጥኩ". . . "ቦረቅኩ"!
<ውሃ እንደተጠማ ደርቆ መሰነጣጠቅ የጀመረው ተስፋዬ ረሰረሰልኝ> ... ቃሉ ለኔ ኃይል አለው። "ሳይፈቀሩ ማፍቀር ድሌ ነው"። "ምላሽ የሌለው መውደድ የሰባ ፍሪዳ ጮማዬ ነው" ።

አርያም ተስፋዬ (2013)

BY አርያም - ARYAM

❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/110

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram was founded in 2013 by two Russian brothers, Nikolai and Pavel Durov. This ability to mix the public and the private, as well as the ability to use bots to engage with users has proved to be problematic. In early 2021, a database selling phone numbers pulled from Facebook was selling numbers for $20 per lookup. Similarly, security researchers found a network of deepfake bots on the platform that were generating images of people submitted by users to create non-consensual imagery, some of which involved children. Two days after Russia invaded Ukraine, an account on the Telegram messaging platform posing as President Volodymyr Zelenskiy urged his armed forces to surrender. This provided opportunity to their linked entities to offload their shares at higher prices and make significant profits at the cost of unsuspecting retail investors. After fleeing Russia, the brothers founded Telegram as a way to communicate outside the Kremlin's orbit. They now run it from Dubai, and Pavel Durov says it has more than 500 million monthly active users.
from de


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American