Telegram Group & Telegram Channel
#መቄዶንያ❤️

🔵 “ የጎዳና ኑሮ ከባድ ነው፣ የ85 ዓመት እናቶች ተደፍረው የመጡበት አጋጣሚዎች አሉ። ጎዳና ላይ ሰዎች በብርድ ምክንያት ይሞታሉ” - የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ

🔴 “ ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ወደ ቀልባችን እንመለስ። ሰውን በመግደል፣ በማፈናቀል የምናገኘው ጥቅም የለም። ሰውን በመርዳት ግን ጥቅም ይገኛል ” - ቀሲስ ታጋይ ታደለ

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ከመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኀበር ጋር በመተባበር ለመጀመሪያ ጊዜ በመቄዶንያን ቅጥር ግቢ ውስጥ አረጋዊያን በተገኙበት ዛሬ የጸሎት መርሀ ግብር አዘጋጅቶ ነበር።

ጸሎቱን የሰባቱም የሃይማኖት ተቋማት አባቶች ሁሉም በዬእምነታቸው መርሀ ግብሩን በጸሎት አስጀምረው፣ የጸሎት መርሀ ግብሩ ተከናውኗል።

የጸሎት ፕሮግራሙ ዓላማ አረጋዊያንን ጋር ተኩኖ ቢጸለይ ፈጣሪ ሰላሙን፣ ፍቅሩን እንደሚሰጥ በማሰብ እንዲሁም የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በሚደረገው ለመቄዶንያ ርዳታ የማሰባሰብ መርሃ ግብር ሁሉም ኢትዮጵያውያን ርብርብ ያደርጉ ጥሪ ለማቅረብ ነው።

የመቄዶንያ መስራች የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ ምን አሉ?

“ እንደሚታወቀው መቄዶኒያ የዘር፣ የሃይማኖት፣ የጾታ ልዩነት ሳያደርግ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ነው የሚረዳው።

ሁሉም የእምነት ተከታዮች በመቄዶንያ አሉ። መቄዶንያ ውስጥ ፕሮቴስታንቶች፣ ሙስሊሞች፣ ኦሮቶዶክሶች፣ ካቶሊኮች አሉ።

እንዲያውም የሚጠበቅብን ምግብ፣ ልብስ መጠለያ ማሟላት ነው። ነገር ግን ከሚጠበቅበት በላይ ድርጅቱ መንፈሳዊ ፍላጎቶችንም ጭምር እያሟላ ይገኛል።

ዛሬ ስለመጣችሁ በጣም ደስ ብሎናል ምክንያቱም ሁሉም የሃይማኖት ተከታዮች እዚህ ስላሉ እናንተን ሲያዩ በጣም ደስ ይላቸዋል። ወደፊትም በሚመቻችሁ ጊዜ እንደዚሁ እየመጣችሁ ብትጎበኙን በጣም ደስ ይለናል።
 
በአሁኑ ወቅት በጣም በርካታ ሰዎች እየረዳን እንገኛለን። 5 ወለል ያለው ህንጻ እየገነባን እንገኛለን። በክልሎችም እንደዚሁ በተለያዩ ቦታዎች ግንባታዎች እየተፋጠኑ ይገኛሉ።

ደሴ፣ ድሬዳዋ፣ ጋምቤላ፣ ኮንሶ፣ ሞያሌ፣ ያቤሎ፣ ጅማ፣ አምቦ፣ ዓዲግራት፣ ዓድዋና ሌሎችም ቦታዎች መቄዶንያ አለ። በተለይ ደግሞ እኛ የምንረዳቸው የአልጋ ቁራኛ፣ የጎዳና ነዋሪ የሆኑ ሰዎችን ነው። 

የጎዳና ኑሮ በጣም ከባድ ነው፣ የሚገርማችሁ የ85 ዓመት እናቶች ተደፍረው እዚህ የመጡበት አጋጣሚዎች አሉ። ጎዳና ላይ ሰዎች በብርድ ምክንያት ይሞታሉ። ብርድ የመታቸው ሰዎች ወደ ህክምና የሚወስዳቸው የለም ”
ብለዋል።

በመሆኑም የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በሚደረገው ዓለም አቀፍ ገቢ የማሰባሰብ መርሀ ግብር፣ ሁሉም አካላት ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉ በ8,000 አረጋዊያን ስም ጥሪ አቅርበዋል።

በመርሀ ግብሩ የተገኙት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው፣ መርሀ ግብሩ የተዘጋጀው ከአረጋዊያኑ ጋር ቢጸለይ ፈጣሪ ጸሎት ይሰማን ተብሎ ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል።

ቀሲስ ታጋይ ምን አሉ ?

“ ዛሬ በመቄዶንያ የተገኘነው ሁለት ጉዳዮችን መሠረት አድርገን ነው። አንደኛው ጸሎት ለማድረግ ነው። 

በአገር ሰላም ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የድርሻቸውን እንዲወጡ በማሰብ ጸሎት ማድረግና የሰላም ጥሪ የቀረበላቸው ወገኖች ወደ ሰላም እንዲመለሱ አስቸኳይ ሁኔታ ለመፍጠር የተደረገ ነው።

ሁለተኛው በመቄዶንያ የተገኘንበት ምክንያት በመቄዶንያ ከ8,000 የሚልቁ ለችግር የተጋለጡ፣ ጎዳና ላይ የወደቁ ኢትዮጵያዊያን ምዕመናን፣ ሙስሊሞች ክርስቲያኖች በኀብረት አሉ።

ስለዚህ ከእነርሱ ጋር ሆነን ብንጸልይ፣ ወደ ፈጣሪ ብናነባ ፈጣሪ ምህረት፣ ቸርነት ያደርግልናል በሚል እሳቤና መቄዶንያም መደገፍ ስላለበት ድጋፍ እንዲደረግለት በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ ለማቅረብ ነው።

ስለዚህ ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ወደ ቀልባችን እንመለስ። ሰውን በመግደል፣ በማፈናቀል የምናገኘው ጥቅም የለም። ሰውን በመርዳት ግን ጥቅም ይገኛል። ሰላምን በማረጋገጥ ግን ጥቅም ይገኛል ”
ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/92539
Create:
Last Update:

#መቄዶንያ❤️

🔵 “ የጎዳና ኑሮ ከባድ ነው፣ የ85 ዓመት እናቶች ተደፍረው የመጡበት አጋጣሚዎች አሉ። ጎዳና ላይ ሰዎች በብርድ ምክንያት ይሞታሉ” - የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ

🔴 “ ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ወደ ቀልባችን እንመለስ። ሰውን በመግደል፣ በማፈናቀል የምናገኘው ጥቅም የለም። ሰውን በመርዳት ግን ጥቅም ይገኛል ” - ቀሲስ ታጋይ ታደለ

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ከመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማኀበር ጋር በመተባበር ለመጀመሪያ ጊዜ በመቄዶንያን ቅጥር ግቢ ውስጥ አረጋዊያን በተገኙበት ዛሬ የጸሎት መርሀ ግብር አዘጋጅቶ ነበር።

ጸሎቱን የሰባቱም የሃይማኖት ተቋማት አባቶች ሁሉም በዬእምነታቸው መርሀ ግብሩን በጸሎት አስጀምረው፣ የጸሎት መርሀ ግብሩ ተከናውኗል።

የጸሎት ፕሮግራሙ ዓላማ አረጋዊያንን ጋር ተኩኖ ቢጸለይ ፈጣሪ ሰላሙን፣ ፍቅሩን እንደሚሰጥ በማሰብ እንዲሁም የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በሚደረገው ለመቄዶንያ ርዳታ የማሰባሰብ መርሃ ግብር ሁሉም ኢትዮጵያውያን ርብርብ ያደርጉ ጥሪ ለማቅረብ ነው።

የመቄዶንያ መስራች የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ ምን አሉ?

“ እንደሚታወቀው መቄዶኒያ የዘር፣ የሃይማኖት፣ የጾታ ልዩነት ሳያደርግ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ነው የሚረዳው።

ሁሉም የእምነት ተከታዮች በመቄዶንያ አሉ። መቄዶንያ ውስጥ ፕሮቴስታንቶች፣ ሙስሊሞች፣ ኦሮቶዶክሶች፣ ካቶሊኮች አሉ።

እንዲያውም የሚጠበቅብን ምግብ፣ ልብስ መጠለያ ማሟላት ነው። ነገር ግን ከሚጠበቅበት በላይ ድርጅቱ መንፈሳዊ ፍላጎቶችንም ጭምር እያሟላ ይገኛል።

ዛሬ ስለመጣችሁ በጣም ደስ ብሎናል ምክንያቱም ሁሉም የሃይማኖት ተከታዮች እዚህ ስላሉ እናንተን ሲያዩ በጣም ደስ ይላቸዋል። ወደፊትም በሚመቻችሁ ጊዜ እንደዚሁ እየመጣችሁ ብትጎበኙን በጣም ደስ ይለናል።
 
በአሁኑ ወቅት በጣም በርካታ ሰዎች እየረዳን እንገኛለን። 5 ወለል ያለው ህንጻ እየገነባን እንገኛለን። በክልሎችም እንደዚሁ በተለያዩ ቦታዎች ግንባታዎች እየተፋጠኑ ይገኛሉ።

ደሴ፣ ድሬዳዋ፣ ጋምቤላ፣ ኮንሶ፣ ሞያሌ፣ ያቤሎ፣ ጅማ፣ አምቦ፣ ዓዲግራት፣ ዓድዋና ሌሎችም ቦታዎች መቄዶንያ አለ። በተለይ ደግሞ እኛ የምንረዳቸው የአልጋ ቁራኛ፣ የጎዳና ነዋሪ የሆኑ ሰዎችን ነው። 

የጎዳና ኑሮ በጣም ከባድ ነው፣ የሚገርማችሁ የ85 ዓመት እናቶች ተደፍረው እዚህ የመጡበት አጋጣሚዎች አሉ። ጎዳና ላይ ሰዎች በብርድ ምክንያት ይሞታሉ። ብርድ የመታቸው ሰዎች ወደ ህክምና የሚወስዳቸው የለም ”
ብለዋል።

በመሆኑም የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በሚደረገው ዓለም አቀፍ ገቢ የማሰባሰብ መርሀ ግብር፣ ሁሉም አካላት ከወዲሁ ዝግጅት እንዲያደርጉ በ8,000 አረጋዊያን ስም ጥሪ አቅርበዋል።

በመርሀ ግብሩ የተገኙት የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ የበላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው፣ መርሀ ግብሩ የተዘጋጀው ከአረጋዊያኑ ጋር ቢጸለይ ፈጣሪ ጸሎት ይሰማን ተብሎ ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል።

ቀሲስ ታጋይ ምን አሉ ?

“ ዛሬ በመቄዶንያ የተገኘነው ሁለት ጉዳዮችን መሠረት አድርገን ነው። አንደኛው ጸሎት ለማድረግ ነው። 

በአገር ሰላም ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን የድርሻቸውን እንዲወጡ በማሰብ ጸሎት ማድረግና የሰላም ጥሪ የቀረበላቸው ወገኖች ወደ ሰላም እንዲመለሱ አስቸኳይ ሁኔታ ለመፍጠር የተደረገ ነው።

ሁለተኛው በመቄዶንያ የተገኘንበት ምክንያት በመቄዶንያ ከ8,000 የሚልቁ ለችግር የተጋለጡ፣ ጎዳና ላይ የወደቁ ኢትዮጵያዊያን ምዕመናን፣ ሙስሊሞች ክርስቲያኖች በኀብረት አሉ።

ስለዚህ ከእነርሱ ጋር ሆነን ብንጸልይ፣ ወደ ፈጣሪ ብናነባ ፈጣሪ ምህረት፣ ቸርነት ያደርግልናል በሚል እሳቤና መቄዶንያም መደገፍ ስላለበት ድጋፍ እንዲደረግለት በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ ለማቅረብ ነው።

ስለዚህ ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ወደ ቀልባችን እንመለስ። ሰውን በመግደል፣ በማፈናቀል የምናገኘው ጥቅም የለም። ሰውን በመርዳት ግን ጥቅም ይገኛል። ሰላምን በማረጋገጥ ግን ጥቅም ይገኛል ”
ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA











Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/92539

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Perpetrators of such fraud use various marketing techniques to attract subscribers on their social media channels. The Dow Jones Industrial Average fell 230 points, or 0.7%. Meanwhile, the S&P 500 and the Nasdaq Composite dropped 1.3% and 2.2%, respectively. All three indexes began the day with gains before selling off. Update March 8, 2022: EFF has clarified that Channels and Groups are not fully encrypted, end-to-end, updated our post to link to Telegram’s FAQ for Cloud and Secret chats, updated to clarify that auto-delete is available for group and channel admins, and added some additional links. At the start of 2018, the company attempted to launch an Initial Coin Offering (ICO) which would enable it to enable payments (and earn the cash that comes from doing so). The initial signals were promising, especially given Telegram’s user base is already fairly crypto-savvy. It raised an initial tranche of cash – worth more than a billion dollars – to help develop the coin before opening sales to the public. Unfortunately, third-party sales of coins bought in those initial fundraising rounds raised the ire of the SEC, which brought the hammer down on the whole operation. In 2020, officials ordered Telegram to pay a fine of $18.5 million and hand back much of the cash that it had raised. "The result is on this photo: fiery 'greetings' to the invaders," the Security Service of Ukraine wrote alongside a photo showing several military vehicles among plumes of black smoke.
from es


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American