Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
“ዶክተር አንዷለም ተተኩሶበት ተመትቶ ተገኘ መኪናው ውስጥ። አንድ ሀኪማችንም ተተኩሶበት መኪናው ሁለት፤ ሦስቴ ተመትቶታል” - ጤና ሳይንስ ኮሌጁ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥበበ ግዮን ግቢ ስፔሻላንስድ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር አንዷለም ዳኘ በተተኮሰባቸው ጥይት መገዳላቸውን ዩኒቨርሲቲውና ኢንተርን ሀኪሞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ለደህንነታቸው…
' በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን ! '

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት በፊት ሥራ ቦታ ላይ አንድ የኮሌጁ ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” - የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር

የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር (ባሕር ዳር) “በጥይት ተገደሉ” በተባሉት በዶክተር አንዷለም ዳኘ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፤ “ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ማኀበሩ ይህን ያለው በኮሌጁ አካላትም ሆነ በኢንተርን ሀኪሞች የግድያና የዘረፋ ሙከራዎች እየተደረጉባቸው መሆናቸውን በመግለጽ ጭምር ነው።

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት  በፊት ሥራ ስራ ቦታ ላይ የነበረ አንድ የህክምና ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” ሲልም አስታውሷል።

ማኀበሩ ስለዶክተር አንዷለም ግድያና ስለስጋቱ ምን አሉ?

“ የዶክተር አንዷለም ዳኘ የቀብር ሥነ ስርዓት በድባንቄ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

ዶክተር አንዷለም ትሁት ሀኪም ነበር። ስለሞተ ሳይሆን እውነታው ይሄው ስለሆነ ነው ይህን የምንለው። ስለሞተ ለመሞጋገስ አይደለም። ከሰውም ሰው ስለነበር እንጂ።

አሟሟቱም ልብ ሰባሪ ነው። ሙያው ሰብ ስፔሻሊስት ነው። አንቱ በሚባልበትና ህዝብን የሚያገለግልበት እድሜ ላይ ነው ያጣነው። እንደ ህክምና ተማሪዎች የእውቀት አባታችንን፤ ወንድማችንን ነው ያጣነው።

ይህን የመሰለ ሰብ ስፔሻሊቲ ሀኪም ማጣት እንደ ሀገርም እንደ ህዝብም በጣም ያማል። መራር ሀዘን ገጥሞናል።

በነገራችን ላይ ተደጋጋሚ ችግሮች አሉ። የሆስፒታሉ ዳይሬክተር ስልክ ተቀምቶ፣ በሽጉጥ ማንገራገር ገጥሞት ነበር፤ በኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ይደረጋል።

በዚሁ የተነሳ ሰብ ስፔሻሊስቶች አገር እየለቀቁ፤ እየሸሹ ነው። ይሄ ባለበት ሁኔታ ጥበቃ፣ ከለላ አለመደረጉ በጣም ያሳዝናል። በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን። የሆስፒታሉ ኃላፊ፣ ኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ተደርጎባቸል።

የኮሌጁ ኃላፊዎችም ከአቅማቸው በላይ የሆነባቸው ይመስለናል። ምንም ከለላ የለም። ግቢ ያሉ ጥበቃዎችም የተጠናከረ አይደለም። ውጪ ላይ ይቅርና ግቢ ውስጥ ራሱ ከፍተኛ ስጋት አለ። አቤት የምንልበት አጥተን ነው እንጂ ” ብሏል።

በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎች መጪውን ጊዜ ለማስተካከል እንዲተጉ፣ ስለመብታቸው ዘብ እንዲቆሙ፣ አንድነት በመፍጠር የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ ማኀበሩ አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94212
Create:
Last Update:

' በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን ! '

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት በፊት ሥራ ቦታ ላይ አንድ የኮሌጁ ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” - የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር

የኢትዮጵያ ህክምና ተማሪዎች ማኀበር (ባሕር ዳር) “በጥይት ተገደሉ” በተባሉት በዶክተር አንዷለም ዳኘ ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጾ፤ “ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ማኀበሩ ይህን ያለው በኮሌጁ አካላትም ሆነ በኢንተርን ሀኪሞች የግድያና የዘረፋ ሙከራዎች እየተደረጉባቸው መሆናቸውን በመግለጽ ጭምር ነው።

“ ኦፊሻል ስላልወጣ እንጂ ከሦስት ሳምንት  በፊት ሥራ ስራ ቦታ ላይ የነበረ አንድ የህክምና ባለሙያ ተገድሏል በሽጉጥ ” ሲልም አስታውሷል።

ማኀበሩ ስለዶክተር አንዷለም ግድያና ስለስጋቱ ምን አሉ?

“ የዶክተር አንዷለም ዳኘ የቀብር ሥነ ስርዓት በድባንቄ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።

ዶክተር አንዷለም ትሁት ሀኪም ነበር። ስለሞተ ሳይሆን እውነታው ይሄው ስለሆነ ነው ይህን የምንለው። ስለሞተ ለመሞጋገስ አይደለም። ከሰውም ሰው ስለነበር እንጂ።

አሟሟቱም ልብ ሰባሪ ነው። ሙያው ሰብ ስፔሻሊስት ነው። አንቱ በሚባልበትና ህዝብን የሚያገለግልበት እድሜ ላይ ነው ያጣነው። እንደ ህክምና ተማሪዎች የእውቀት አባታችንን፤ ወንድማችንን ነው ያጣነው።

ይህን የመሰለ ሰብ ስፔሻሊቲ ሀኪም ማጣት እንደ ሀገርም እንደ ህዝብም በጣም ያማል። መራር ሀዘን ገጥሞናል።

በነገራችን ላይ ተደጋጋሚ ችግሮች አሉ። የሆስፒታሉ ዳይሬክተር ስልክ ተቀምቶ፣ በሽጉጥ ማንገራገር ገጥሞት ነበር፤ በኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ይደረጋል።

በዚሁ የተነሳ ሰብ ስፔሻሊስቶች አገር እየለቀቁ፤ እየሸሹ ነው። ይሄ ባለበት ሁኔታ ጥበቃ፣ ከለላ አለመደረጉ በጣም ያሳዝናል። በጣም ከፍተኛና ልዩ ስጋት አለብን። የሆስፒታሉ ኃላፊ፣ ኢንተርን ሀኪሞችም ሙከራ ተደርጎባቸል።

የኮሌጁ ኃላፊዎችም ከአቅማቸው በላይ የሆነባቸው ይመስለናል። ምንም ከለላ የለም። ግቢ ያሉ ጥበቃዎችም የተጠናከረ አይደለም። ውጪ ላይ ይቅርና ግቢ ውስጥ ራሱ ከፍተኛ ስጋት አለ። አቤት የምንልበት አጥተን ነው እንጂ ” ብሏል።

በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ ተማሪዎች መጪውን ጊዜ ለማስተካከል እንዲተጉ፣ ስለመብታቸው ዘብ እንዲቆሙ፣ አንድነት በመፍጠር የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ ማኀበሩ አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA









Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94212

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

"We're seeing really dramatic moves, and it's all really tied to Ukraine right now, and in a secondary way, in terms of interest rates," Octavio Marenzi, CEO of Opimas, told Yahoo Finance Live on Thursday. "This war in Ukraine is going to give the Fed the ammunition, the cover that it needs, to not raise interest rates too quickly. And I think Jay Powell is a very tepid sort of inflation fighter and he's not going to do as much as he needs to do to get that under control. And this seems like an excuse to kick the can further down the road still and not do too much too soon." "The argument from Telegram is, 'You should trust us because we tell you that we're trustworthy,'" Maréchal said. "It's really in the eye of the beholder whether that's something you want to buy into." Official government accounts have also spread fake fact checks. An official Twitter account for the Russia diplomatic mission in Geneva shared a fake debunking video claiming without evidence that "Western and Ukrainian media are creating thousands of fake news on Russia every day." The video, which has amassed almost 30,000 views, offered a "how-to" spot misinformation. There was another possible development: Reuters also reported that Ukraine said that Belarus could soon join the invasion of Ukraine. However, the AFP, citing a Pentagon official, said the U.S. hasn’t yet seen evidence that Belarusian troops are in Ukraine. As the war in Ukraine rages, the messaging app Telegram has emerged as the go-to place for unfiltered live war updates for both Ukrainian refugees and increasingly isolated Russians alike.
from es


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American