Telegram Group & Telegram Channel
. . . 'ጠናናነቱን' የሚያሳብቁ አይኖቹን እያየው

.....የኔ ፍቅር ታፈቅረኛለህ? እንዲያዘንብልኝ አንዴ የፀሐይዋን መጥለቅ ደግሞ ዘወር ብዬ ካፊያውን እየናፈቅኩ!

........እሱ ዝም... ጭጭ።

ቆይ!! ቃል ማውጣት ስራ ይሆናል? ለእሱማ ጥንብ የሆነበትን ሸክም የሚያራግፍበት ቀሊል የሚጠብቅ ነው የሚመስለው. ... በጣም ይከብደዋል።

....... እ? <የኔ ፍቅር ምን ያህል ታፈቅረኛለህ?> ለወጥ ሳደርግ ይመልስልኝ ይመስል...... የአጠያየቄ አይነት ሁልቆ መሳፍርት የለሁም። ...... ጥያቄ ጎጆዋን እንደቀለሰችብኝ መልስ ደሞ ደጅ ታስጠናኛለች።

.... ማሬ! እስኪ << አፈቅርሻለው >>በለኝ አልኩት እየተልመጠመጥኩ..... ምን አለ አፈንድቶት ቢገላግለኝ የጥያቄ መዝገበ ቃላቴ እኮ ታዘበኝ።

.....ለሽርደዳ ለሽርደዳማ ማንም አይችለውም። ..... ከንፋስ የፈጠነ፣ ከእስትንፋስ የቀረበ ነው። ............ 'በእግረ ደረቅነቴ' ላይ ሲያሽሞጥጥ የሚቀድመው የለም። ምን እሱ ብቻ መዘባበቻ ሲያደርገኝ የአለም ቃላት፣ ዓረፍተነገር፣ አንቀፅ ቀለበት ያሰሩለት ነው የሚመስሉት!!

... ''ለምን አይመልስልኝም?" ቃላት ማውጣት ይከብዳል? ያውም የሰለለ ድምፁን ከእሬት ስልቱ ጋር አዋህዶት ሊያቀርብልኝ

ግን! እኮ ያንን ቃል እወደዋለው እንደተፈታች እንቦሳ ያስፈነድቀኛል።

. . . ፈለግ የወረረውን ጣቱን ፈርሱ ላይ እያንሸራሸረ፣ አልፎ አልፎ እጆቹን ጉሹ በሸሸው አናቱ ላይ ችፍ ያለሁን ላቦቱን እየጠረገ፣ ልማደኛ ጥፍሩን ጭጉኝ በወረሰው ጢሙ ወጋ ወጋ እያደረገ፣ ....እንደ ማስቲካ አላምጦ ጣዕሙ ሲያልቅ ለሚተፋው ቃል ለምንስ እጨነቃለው?

. . . 'ስጋ' የሆነውን 'ቃል' እንኳን የገዛ ወገኖቹ አልተቀበሉትም። "ሰምና ወርቅ" ሲያወጡለት ስንክልክል ብለዋል። ...'የፍጥረትን ሩጫ' የሚያቃጥለው 'ዓረፍተ ነገር' በየጉራንጉሩ እንደ ጭቃ ይለጣጠፉበታል። <አንደበት ዓመፀኛ አለም ነው> ያሻው ፍቅርን ይገድልበታል። የገደለውን ይቀብርበታል። ታዲያ! ለዚ ቃል ነው ደጅ የሚያስጠናኝ? 'የህልም እንጀራ' አሳቅፎ የሚያንከራትተኝ!

.....'ያላበጀውን ፍቅር' በፊደሉ ቢራቀቅበት ምን አለ? ለእሱ ''ማርጃ'' ለእኔ ''የምስራች'' የሆነውን ቢነግረኝ ምን ቸግሮት?

.....<ሀሞቴ ፈሷል> ግን! የመጨረሻ ቃሌን አቀበልኩት

<<የእኔ ውድ በጣም አፈቅርሃለው!>> ጥያቄ አልነበረም። ምላሽም አይሻም!

. . . 'የበጨጨ' አልፎ አልፎ ጥጋ ጥጉን እንደ 'ዳመና' ጥቁር ያጠላበትን ጥርሱን ብልጭ አድርጎ እንደወትሮው በመሰሪ አይኖቹ 'ሴሰኛ' አስተያየቱን መርቆልኝ ..... የአምስት ወር ህፃን ይመስል እየዳኸ በሚንፏቀቁ ቃላቶች

<<አ..ላ...ፈ...ቅ...ርሽም>> አለኝ! ቦምቡን አፈነዳው። ስብርባሪው አልጎዳኝም። እንደሁም በተቃራኒው. . .

.... "ነፍሴ ሃሴት አደረገች". . . "ጮቤ ረገጥኩ". . . "ቦረቅኩ"!
<ውሃ እንደተጠማ ደርቆ መሰነጣጠቅ የጀመረው ተስፋዬ ረሰረሰልኝ> ... ቃሉ ለኔ ኃይል አለው። "ሳይፈቀሩ ማፍቀር ድሌ ነው"። "ምላሽ የሌለው መውደድ የሰባ ፍሪዳ ጮማዬ ነው" ።

አርያም ተስፋዬ (2013)



group-telegram.com/yabsiratesfaye/110
Create:
Last Update:

. . . 'ጠናናነቱን' የሚያሳብቁ አይኖቹን እያየው

.....የኔ ፍቅር ታፈቅረኛለህ? እንዲያዘንብልኝ አንዴ የፀሐይዋን መጥለቅ ደግሞ ዘወር ብዬ ካፊያውን እየናፈቅኩ!

........እሱ ዝም... ጭጭ።

ቆይ!! ቃል ማውጣት ስራ ይሆናል? ለእሱማ ጥንብ የሆነበትን ሸክም የሚያራግፍበት ቀሊል የሚጠብቅ ነው የሚመስለው. ... በጣም ይከብደዋል።

....... እ? <የኔ ፍቅር ምን ያህል ታፈቅረኛለህ?> ለወጥ ሳደርግ ይመልስልኝ ይመስል...... የአጠያየቄ አይነት ሁልቆ መሳፍርት የለሁም። ...... ጥያቄ ጎጆዋን እንደቀለሰችብኝ መልስ ደሞ ደጅ ታስጠናኛለች።

.... ማሬ! እስኪ << አፈቅርሻለው >>በለኝ አልኩት እየተልመጠመጥኩ..... ምን አለ አፈንድቶት ቢገላግለኝ የጥያቄ መዝገበ ቃላቴ እኮ ታዘበኝ።

.....ለሽርደዳ ለሽርደዳማ ማንም አይችለውም። ..... ከንፋስ የፈጠነ፣ ከእስትንፋስ የቀረበ ነው። ............ 'በእግረ ደረቅነቴ' ላይ ሲያሽሞጥጥ የሚቀድመው የለም። ምን እሱ ብቻ መዘባበቻ ሲያደርገኝ የአለም ቃላት፣ ዓረፍተነገር፣ አንቀፅ ቀለበት ያሰሩለት ነው የሚመስሉት!!

... ''ለምን አይመልስልኝም?" ቃላት ማውጣት ይከብዳል? ያውም የሰለለ ድምፁን ከእሬት ስልቱ ጋር አዋህዶት ሊያቀርብልኝ

ግን! እኮ ያንን ቃል እወደዋለው እንደተፈታች እንቦሳ ያስፈነድቀኛል።

. . . ፈለግ የወረረውን ጣቱን ፈርሱ ላይ እያንሸራሸረ፣ አልፎ አልፎ እጆቹን ጉሹ በሸሸው አናቱ ላይ ችፍ ያለሁን ላቦቱን እየጠረገ፣ ልማደኛ ጥፍሩን ጭጉኝ በወረሰው ጢሙ ወጋ ወጋ እያደረገ፣ ....እንደ ማስቲካ አላምጦ ጣዕሙ ሲያልቅ ለሚተፋው ቃል ለምንስ እጨነቃለው?

. . . 'ስጋ' የሆነውን 'ቃል' እንኳን የገዛ ወገኖቹ አልተቀበሉትም። "ሰምና ወርቅ" ሲያወጡለት ስንክልክል ብለዋል። ...'የፍጥረትን ሩጫ' የሚያቃጥለው 'ዓረፍተ ነገር' በየጉራንጉሩ እንደ ጭቃ ይለጣጠፉበታል። <አንደበት ዓመፀኛ አለም ነው> ያሻው ፍቅርን ይገድልበታል። የገደለውን ይቀብርበታል። ታዲያ! ለዚ ቃል ነው ደጅ የሚያስጠናኝ? 'የህልም እንጀራ' አሳቅፎ የሚያንከራትተኝ!

.....'ያላበጀውን ፍቅር' በፊደሉ ቢራቀቅበት ምን አለ? ለእሱ ''ማርጃ'' ለእኔ ''የምስራች'' የሆነውን ቢነግረኝ ምን ቸግሮት?

.....<ሀሞቴ ፈሷል> ግን! የመጨረሻ ቃሌን አቀበልኩት

<<የእኔ ውድ በጣም አፈቅርሃለው!>> ጥያቄ አልነበረም። ምላሽም አይሻም!

. . . 'የበጨጨ' አልፎ አልፎ ጥጋ ጥጉን እንደ 'ዳመና' ጥቁር ያጠላበትን ጥርሱን ብልጭ አድርጎ እንደወትሮው በመሰሪ አይኖቹ 'ሴሰኛ' አስተያየቱን መርቆልኝ ..... የአምስት ወር ህፃን ይመስል እየዳኸ በሚንፏቀቁ ቃላቶች

<<አ..ላ...ፈ...ቅ...ርሽም>> አለኝ! ቦምቡን አፈነዳው። ስብርባሪው አልጎዳኝም። እንደሁም በተቃራኒው. . .

.... "ነፍሴ ሃሴት አደረገች". . . "ጮቤ ረገጥኩ". . . "ቦረቅኩ"!
<ውሃ እንደተጠማ ደርቆ መሰነጣጠቅ የጀመረው ተስፋዬ ረሰረሰልኝ> ... ቃሉ ለኔ ኃይል አለው። "ሳይፈቀሩ ማፍቀር ድሌ ነው"። "ምላሽ የሌለው መውደድ የሰባ ፍሪዳ ጮማዬ ነው" ።

አርያም ተስፋዬ (2013)

BY አርያም - ARYAM

❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/110

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

He said that since his platform does not have the capacity to check all channels, it may restrict some in Russia and Ukraine "for the duration of the conflict," but then reversed course hours later after many users complained that Telegram was an important source of information. "There is a significant risk of insider threat or hacking of Telegram systems that could expose all of these chats to the Russian government," said Eva Galperin with the Electronic Frontier Foundation, which has called for Telegram to improve its privacy practices. That hurt tech stocks. For the past few weeks, the 10-year yield has traded between 1.72% and 2%, as traders moved into the bond for safety when Russia headlines were ugly—and out of it when headlines improved. Now, the yield is touching its pandemic-era high. If the yield breaks above that level, that could signal that it’s on a sustainable path higher. Higher long-dated bond yields make future profits less valuable—and many tech companies are valued on the basis of profits forecast for many years in the future. Either way, Durov says that he withdrew his resignation but that he was ousted from his company anyway. Subsequently, control of the company was reportedly handed to oligarchs Alisher Usmanov and Igor Sechin, both allegedly close associates of Russian leader Vladimir Putin. Although some channels have been removed, the curation process is considered opaque and insufficient by analysts.
from es


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American