Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-92942-92943-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/92943 -
Telegram Group & Telegram Channel
“ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” - የአቶ ክርስቲያን ታደለ ቤተሰብ

ለ1 አመት ከ4 ወራት በእስር ላይ ሆነው ፍትህ እየተጠባበቁ የሚገኙት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አበል አቶ ክርስቲያን ታደለ ከባድ የጤና እከል ስለገጠማቸው በሕይወት እንዲቆዩ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዲጎበኟቸው የቅርብ ቤተሰባቸው አሳሰቡ።

ከፍትህ በፊት በሕይወት መቆየታቸው እንደሚቀድም ገልጸው፣ “ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።

የአቶ ክርስቲያን የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ የጤናው ሁኔታ አሁንም በጣም አሳሰቢ ነው። ሰርጀሪ ተደርጎለት በሰዓታት ልዩነት ነው ወደ ማረሚያ ቤት የተመለሰው። እዛም ሆኖ የደም መፍሰስ አለበት።

ሰኞ እለት ቀጠሮ ስለነበር ሂዶ ነበር የሚፈሰው ደም ምን እንደሆነ ለማወቅ ብለው ደም ወስደዋል። ባለፈው ከአንጀቱ ውስጥ በሰርጀሪ የወጣውንና የተወሰደውን ደም ውጤት ለማወቅ ለነገ ሐሙስ ተቀጥሯል።

ህመም አለው። ‘ከፍተኛ ህመም ነው የሚሰማኝ’ ነው የሚለው። ለጊዜው የሚያስታግስለትን መድኃኒት ነው የሚጠቀመው።

ከዚህ ቀደም አያመውም ነበር። አዋሽ አርባ ከሄደ በኋላ ነው የታመመው። አሁን ሲነግረን አሟቸው ከአዋሽ ወደ አዲስ አበባ አምጥተዋቸው ነበር። የዛኔም ምርመራና በቂ ህክምና አላደረገም። 

የዛኔ አብረዋቸው ከአዋሽ የመጡ አካላት ፕራይቬሲያቸውን በሚጥስ ሁኔታ ‘አብረን ገብተን እንመለከታለን ህክምናውን’ በሚል አለመግባባት ተፈጥሮ ህክምና ሳያገኙ ተመልሱ።

የዛኔ ቢታከም መታጠብ ነበር የሚጠበቅበት ለሰርጀሪም አይደርስም ነበር። ህመሙ በድርቀት የሚመጣ ሲሆን፣  አንጀቱ ውስጥ ሌላ የቋጠረ ነገር ነበር።

እሱንም አሁን ሀኪሞቹ ለማብራራት ቆርጠው ካወጡት በኋላ ለምርመራ ተወስዷል። ነገ ነው ውጤቱ የሚገለጸው።

የፍርድ ሂደቱን በተመለከተ በሚገርም ሁኔታ በጣም ረጅም፣ ረጅም የሆነ ቀጠሮ ነው የሚሰጠው። አሁንም ገና ለጥር 13 ነው ቀጠሮ የተሰጣቸው።
 
እንደ ቤተሰብ ከምንናገረው በላይ እጅግ በጣም ከባድ ነው ያለንበት ሁኔታ። እሱ በነበረበት ወቅት ጥሩ በሚባል ሁኔታ ላይ ነው የነበርነው፣ አሁን ላይ እንደዛ አይደለም።

ፍትህ እንጠብቃለን። ተስፋ አንቆርጥም። ግን አሁን ያለው ሂደት በፍትህ ስርዓቱ ክርስቲያንንም ተስፋ እንዳቆረጠው ነው በተደጋጋሚ የሚነግረን፣ እኛም የምናየው።

የደም መፍሰሱ እንኳ አልቆመለትም በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ነው ያለው። የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ።

በቂ የሆነ ህክምና እንዲያገኝ ያለበትን ሁኔታ ተረድተው የሰብዓዊ መብት አካላት እንዲጎበኙት እንፈልጋለን ”
ሲሉ ተማጽነዋል።

(የአቶ ዮሐንስ ቧ ያለው የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ያቀረቡት እሮሮ በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/92943
Create:
Last Update:

“ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” - የአቶ ክርስቲያን ታደለ ቤተሰብ

ለ1 አመት ከ4 ወራት በእስር ላይ ሆነው ፍትህ እየተጠባበቁ የሚገኙት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አበል አቶ ክርስቲያን ታደለ ከባድ የጤና እከል ስለገጠማቸው በሕይወት እንዲቆዩ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዲጎበኟቸው የቅርብ ቤተሰባቸው አሳሰቡ።

ከፍትህ በፊት በሕይወት መቆየታቸው እንደሚቀድም ገልጸው፣ “ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።

የአቶ ክርስቲያን የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ የጤናው ሁኔታ አሁንም በጣም አሳሰቢ ነው። ሰርጀሪ ተደርጎለት በሰዓታት ልዩነት ነው ወደ ማረሚያ ቤት የተመለሰው። እዛም ሆኖ የደም መፍሰስ አለበት።

ሰኞ እለት ቀጠሮ ስለነበር ሂዶ ነበር የሚፈሰው ደም ምን እንደሆነ ለማወቅ ብለው ደም ወስደዋል። ባለፈው ከአንጀቱ ውስጥ በሰርጀሪ የወጣውንና የተወሰደውን ደም ውጤት ለማወቅ ለነገ ሐሙስ ተቀጥሯል።

ህመም አለው። ‘ከፍተኛ ህመም ነው የሚሰማኝ’ ነው የሚለው። ለጊዜው የሚያስታግስለትን መድኃኒት ነው የሚጠቀመው።

ከዚህ ቀደም አያመውም ነበር። አዋሽ አርባ ከሄደ በኋላ ነው የታመመው። አሁን ሲነግረን አሟቸው ከአዋሽ ወደ አዲስ አበባ አምጥተዋቸው ነበር። የዛኔም ምርመራና በቂ ህክምና አላደረገም። 

የዛኔ አብረዋቸው ከአዋሽ የመጡ አካላት ፕራይቬሲያቸውን በሚጥስ ሁኔታ ‘አብረን ገብተን እንመለከታለን ህክምናውን’ በሚል አለመግባባት ተፈጥሮ ህክምና ሳያገኙ ተመልሱ።

የዛኔ ቢታከም መታጠብ ነበር የሚጠበቅበት ለሰርጀሪም አይደርስም ነበር። ህመሙ በድርቀት የሚመጣ ሲሆን፣  አንጀቱ ውስጥ ሌላ የቋጠረ ነገር ነበር።

እሱንም አሁን ሀኪሞቹ ለማብራራት ቆርጠው ካወጡት በኋላ ለምርመራ ተወስዷል። ነገ ነው ውጤቱ የሚገለጸው።

የፍርድ ሂደቱን በተመለከተ በሚገርም ሁኔታ በጣም ረጅም፣ ረጅም የሆነ ቀጠሮ ነው የሚሰጠው። አሁንም ገና ለጥር 13 ነው ቀጠሮ የተሰጣቸው።
 
እንደ ቤተሰብ ከምንናገረው በላይ እጅግ በጣም ከባድ ነው ያለንበት ሁኔታ። እሱ በነበረበት ወቅት ጥሩ በሚባል ሁኔታ ላይ ነው የነበርነው፣ አሁን ላይ እንደዛ አይደለም።

ፍትህ እንጠብቃለን። ተስፋ አንቆርጥም። ግን አሁን ያለው ሂደት በፍትህ ስርዓቱ ክርስቲያንንም ተስፋ እንዳቆረጠው ነው በተደጋጋሚ የሚነግረን፣ እኛም የምናየው።

የደም መፍሰሱ እንኳ አልቆመለትም በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ነው ያለው። የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ።

በቂ የሆነ ህክምና እንዲያገኝ ያለበትን ሁኔታ ተረድተው የሰብዓዊ መብት አካላት እንዲጎበኙት እንፈልጋለን ”
ሲሉ ተማጽነዋል።

(የአቶ ዮሐንስ ቧ ያለው የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ያቀረቡት እሮሮ በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/92943

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

He floated the idea of restricting the use of Telegram in Ukraine and Russia, a suggestion that was met with fierce opposition from users. Shortly after, Durov backed off the idea. Elsewhere, version 8.6 of Telegram integrates the in-app camera option into the gallery, while a new navigation bar gives quick access to photos, files, location sharing, and more. Stocks dropped on Friday afternoon, as gains made earlier in the day on hopes for diplomatic progress between Russia and Ukraine turned to losses. Technology stocks were hit particularly hard by higher bond yields. As the war in Ukraine rages, the messaging app Telegram has emerged as the go-to place for unfiltered live war updates for both Ukrainian refugees and increasingly isolated Russians alike. Ukrainian forces successfully attacked Russian vehicles in the capital city of Kyiv thanks to a public tip made through the encrypted messaging app Telegram, Ukraine's top law-enforcement agency said on Tuesday.
from fr


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American