Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ዘጠኝ
ደብዳቤውን አንብባ እንደጨረሰች ራሷን ጉልበቶቿ መሀል ወሸቀቻቸው። ለምን ይሄን ሁሉ መስዋዕትነት? ለምን ይህን ያህል ለአንዲት ሴት ራስን አሳልፎ መስጠት? በምላሹ ታፍቅረው አታፍቅረው ሳያውቅ ለምን ራሱን ለእሷ ሰጠ? በህይወት ቢኖርና ይህንን ጥያቄዋን ቢመልስላት በወደደች ነበር ግን እዮብ አይመለስ አሸልቧል።

ተሳሳትክ እዮብ ብትነግረኝ ይሻል ነበር። ከጭንቅላቴ የማይሻር ጠባሳ ተውክብኝ! መቼም ከፊቴ የተዘረረውን ያንተን አካል መዘንጋት አልችልም ፣ከአእምሮዬ ሊጠፋ አይችልም። እዮብ ስህተት ሰርተኻል አዎ በጣም ተሳስተሃል! እጇ ላከ የነበረውን ወረቀት ጨመደደችው። ምን ልታስብ እንደሚገባት ማወቅ አልቻለችም። ብቻ ልትከፍለው የማትችለው የእዮብ ውለታ አለባት።

አፈቅረው ነበር? እራሷን ጠየቀች ልቧ የአዎንታም የአሉታም ምላሽ አልሰጣትም። ለረጅም ሰአት አነባች። አልአዛር ለማባበል አልሞከረም። ምክንያቱም የእሱም እምባ እየፈሰሰ ነበር። አንድ ብቸኛ ወንድሙን እንዳጣ ገብቶታል። በጀግንነት የሞተው የወንድሙ ወኔና ድፍረት ታወሰው። ለእዚች ከፊት ለፊቱ ለተቀመጠችው ሴት የነበረው የፍቅር ጥንካሬ የተለየ ነበር። ምን ያደርጋል? በህይወት ሳለ መፈቀሯን ሳታውቅ ከሞተ በኅላ ለፍቅሯ የከፈለውን መስዋዕትነት የተረዳችው ወጣት ላታገግም ቆስላለች። በምንም መንገድ ሊያፅናናት አይችልም።

ማን ያውቃል? ጊዜ የሚያመጣው አይታወቅም አለ ለራሱ እዮብን ልትዘነጋ የምትችልበት መንገድ ይኖራል።  በተቻለው መጠን ሀዘኗን ልትረሳ የምትችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በሙሉ አቅሙ ቆርጧል። ከመንግስትም የደንነት አባላት ጋር በነበረው የጠበቀ ግንኙነት አንድ የውሸት መታወቂያ ሊያገኝላት ችሏል። የእሷን መምጣት ቀደም ብሎ እየጠበቀች ስለነበር ሁሉንም ነገር አስቀድሞ ዝግጁ አድርጓል።

መታወቂያውን ከኪሱ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠው። 'መአዛ አሸናፊ' ይላል። ምንድን ነው በሚል ሁኔታ ተመለከተችው። አዲሱ ስምሽ ነው ትንሽ ራስሽን መቀየር ይኖርብሻል አለና ትርምስምሱ የወጣውን ረጅም ፀጉሯን አየ። መቆረጥ ሳይኖርበት አይቀርም። በተወሰነ መልኩ የፊትሽን ገፅታ ሊቀይረው ይችላል። ግን ይህን የመሰለ ፀጉር ተቆርጦ ሲወድግ ያሳዝናል ሲል አሰበ።

ብሌን አላመነታችም። በህይወት መኖር እስካለባት ድረስ ራሷን መለወጧ የግድ ነው። ሻወር መውሰድ ፈልጋለች። አልአዛር ጭንቅላቷን ያነበበ ይመስል መታጠብ ከፈለግሽ ሻወር ቤቱን ላሳይሽ እችላለሁ።  ፀጉርሽን የምትቆርጪበት መቀስ በስተቀኝ ባለው ኮመዲኖ ላይ ይገኛል። አላት ጊዜ ሳታጠፋ ልብሷን አወላልቃ ውሀው ውስጥ ተነከረች። ውሀው እንደውጪው ቆሻሻዋ ልቧ ውስጥም ያለውን ሸክም መውሰድ ቢችል ምንኛ በተደሰተች ነበር። ዐይኗን ጨፍና ከላይ የሚወርደውን ውሀ ከጭንቅላቷ ጀምሮ ታች እስኪደርስ ድረስ ታዳምጠዋለች። ከውሀው አንድ መፍትሔ ታገኝ ይመስል አሁንም አሁንም ትነከራለች። ሰውነቷ ቢፀዳም መውጣቱን ጠላችው። በጣም ከምትወዳት  ምስኪን እናቷ ጋር እንደማትገናኝ ተረድታለች። ይሄኔ እማዬ ሞቴን ሰምታ ሀዘን ተቀምጣ ይሆናል ስትል አሰበች። በራ ሄዳ አይዞሽ በህይወት አለውልሽ ልትላት ተመኘች።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/124
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ዘጠኝ
ደብዳቤውን አንብባ እንደጨረሰች ራሷን ጉልበቶቿ መሀል ወሸቀቻቸው። ለምን ይሄን ሁሉ መስዋዕትነት? ለምን ይህን ያህል ለአንዲት ሴት ራስን አሳልፎ መስጠት? በምላሹ ታፍቅረው አታፍቅረው ሳያውቅ ለምን ራሱን ለእሷ ሰጠ? በህይወት ቢኖርና ይህንን ጥያቄዋን ቢመልስላት በወደደች ነበር ግን እዮብ አይመለስ አሸልቧል።

ተሳሳትክ እዮብ ብትነግረኝ ይሻል ነበር። ከጭንቅላቴ የማይሻር ጠባሳ ተውክብኝ! መቼም ከፊቴ የተዘረረውን ያንተን አካል መዘንጋት አልችልም ፣ከአእምሮዬ ሊጠፋ አይችልም። እዮብ ስህተት ሰርተኻል አዎ በጣም ተሳስተሃል! እጇ ላከ የነበረውን ወረቀት ጨመደደችው። ምን ልታስብ እንደሚገባት ማወቅ አልቻለችም። ብቻ ልትከፍለው የማትችለው የእዮብ ውለታ አለባት።

አፈቅረው ነበር? እራሷን ጠየቀች ልቧ የአዎንታም የአሉታም ምላሽ አልሰጣትም። ለረጅም ሰአት አነባች። አልአዛር ለማባበል አልሞከረም። ምክንያቱም የእሱም እምባ እየፈሰሰ ነበር። አንድ ብቸኛ ወንድሙን እንዳጣ ገብቶታል። በጀግንነት የሞተው የወንድሙ ወኔና ድፍረት ታወሰው። ለእዚች ከፊት ለፊቱ ለተቀመጠችው ሴት የነበረው የፍቅር ጥንካሬ የተለየ ነበር። ምን ያደርጋል? በህይወት ሳለ መፈቀሯን ሳታውቅ ከሞተ በኅላ ለፍቅሯ የከፈለውን መስዋዕትነት የተረዳችው ወጣት ላታገግም ቆስላለች። በምንም መንገድ ሊያፅናናት አይችልም።

ማን ያውቃል? ጊዜ የሚያመጣው አይታወቅም አለ ለራሱ እዮብን ልትዘነጋ የምትችልበት መንገድ ይኖራል።  በተቻለው መጠን ሀዘኗን ልትረሳ የምትችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በሙሉ አቅሙ ቆርጧል። ከመንግስትም የደንነት አባላት ጋር በነበረው የጠበቀ ግንኙነት አንድ የውሸት መታወቂያ ሊያገኝላት ችሏል። የእሷን መምጣት ቀደም ብሎ እየጠበቀች ስለነበር ሁሉንም ነገር አስቀድሞ ዝግጁ አድርጓል።

መታወቂያውን ከኪሱ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠው። 'መአዛ አሸናፊ' ይላል። ምንድን ነው በሚል ሁኔታ ተመለከተችው። አዲሱ ስምሽ ነው ትንሽ ራስሽን መቀየር ይኖርብሻል አለና ትርምስምሱ የወጣውን ረጅም ፀጉሯን አየ። መቆረጥ ሳይኖርበት አይቀርም። በተወሰነ መልኩ የፊትሽን ገፅታ ሊቀይረው ይችላል። ግን ይህን የመሰለ ፀጉር ተቆርጦ ሲወድግ ያሳዝናል ሲል አሰበ።

ብሌን አላመነታችም። በህይወት መኖር እስካለባት ድረስ ራሷን መለወጧ የግድ ነው። ሻወር መውሰድ ፈልጋለች። አልአዛር ጭንቅላቷን ያነበበ ይመስል መታጠብ ከፈለግሽ ሻወር ቤቱን ላሳይሽ እችላለሁ።  ፀጉርሽን የምትቆርጪበት መቀስ በስተቀኝ ባለው ኮመዲኖ ላይ ይገኛል። አላት ጊዜ ሳታጠፋ ልብሷን አወላልቃ ውሀው ውስጥ ተነከረች። ውሀው እንደውጪው ቆሻሻዋ ልቧ ውስጥም ያለውን ሸክም መውሰድ ቢችል ምንኛ በተደሰተች ነበር። ዐይኗን ጨፍና ከላይ የሚወርደውን ውሀ ከጭንቅላቷ ጀምሮ ታች እስኪደርስ ድረስ ታዳምጠዋለች። ከውሀው አንድ መፍትሔ ታገኝ ይመስል አሁንም አሁንም ትነከራለች። ሰውነቷ ቢፀዳም መውጣቱን ጠላችው። በጣም ከምትወዳት  ምስኪን እናቷ ጋር እንደማትገናኝ ተረድታለች። ይሄኔ እማዬ ሞቴን ሰምታ ሀዘን ተቀምጣ ይሆናል ስትል አሰበች። በራ ሄዳ አይዞሽ በህይወት አለውልሽ ልትላት ተመኘች።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/124

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In addition, Telegram now supports the use of third-party streaming tools like OBS Studio and XSplit to broadcast live video, allowing users to add overlays and multi-screen layouts for a more professional look. "We as Ukrainians believe that the truth is on our side, whether it's truth that you're proclaiming about the war and everything else, why would you want to hide it?," he said. "Someone posing as a Ukrainian citizen just joins the chat and starts spreading misinformation, or gathers data, like the location of shelters," Tsekhanovska said, noting how false messages have urged Ukrainians to turn off their phones at a specific time of night, citing cybersafety. Markets continued to grapple with the economic and corporate earnings implications relating to the Russia-Ukraine conflict. “We have a ton of uncertainty right now,” said Stephanie Link, chief investment strategist and portfolio manager at Hightower Advisors. “We’re dealing with a war, we’re dealing with inflation. We don’t know what it means to earnings.” At this point, however, Durov had already been working on Telegram with his brother, and further planned a mobile-first social network with an explicit focus on anti-censorship. Later in April, he told TechCrunch that he had left Russia and had “no plans to go back,” saying that the nation was currently “incompatible with internet business at the moment.” He added later that he was looking for a country that matched his libertarian ideals to base his next startup.
from fr


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American