Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል አስራ ሶስት
ትዝታ ከቤት እንደወጣች ብሌን በእፎይታ ሶፋው ላይ ተወረወረች። እዮብ ቢሆን እንደዚች አይነቷን አይደለም ለጓደኝነት ለአይንም ቢሆን ይጠየፋት ነበር ስትል አሰበች። መልካቸው ብቻ ነው ለካ የሚመሳሰለው አለች በልቧ። ምንም ስለአልአዛር የግል ህይወት አያገባኝም! ግን ምን ሲሆን ከእንደዚች አይነቷ ጋር ሆነ? ብሌን ከቅሬታዋ በላይ የሚሰማት ብስጭት መንስኤውን አለማወቋ አሳሰባት። ምን አልባት አልአዛርን እንደ እዮብ ቆጥራው ይሆናል። ወይም የወንድሙ ውለታ ስለሱ እንድትጨነቅ አስገድዷትም ይሆናል። ብቻ ተበሳጭታለች። ማታ አልአዛር እስኪመጣ መታገስ አቃታት።

እንደምንም መሸና አልአዛር ቤት መጣ። እራት ካቀረበች በኃላ "ትዝታ የምትባል ሴት መጥታ ነበር።" እዚ ስታጣህ ሱቅ ይኖራል ብዬ ብነግራትም ነገ መጣለው ብላ ሄደች አለች በዝምታ የተዋጠውን ማዕድ በማደፍረስ። እና ምን አለችሽ? የሚያስቀይም ነገር ተናገረችሽ? ጥያቄውን አከታትሎ ጠየቃት። አይ ምንም አልተናገረችም የናትናኤል እጮኛ ነኝ ብዬ ስነግራት ያመነችኝ ትመስላለች ... ብሌን እናቷን ስትዋሻት ሁሌም ታውቅባት ነበር። ትዝታ ግን አለማወቋ አስደስቷታል።

አልአዛር የብሌን ትዝታን ማየት ረፍት ነሳው። የትዝታ መጥፎ ባህሪያቶች ብቻ ሳይሆን ብሌን ከነጭራሹ ከትዝታ ጋር የነበረውን ነገር ባታውቅበት ይመርጣል። ዛሬ ካለወትሮው ወደ ስራ ለምን እንደሄደ አሰበ "ሽሽት" አለ በሆዱ። እኮ ከምን? መልሶ ራሱን ጠየቀ። ከብሌን? እሱማ አይሆንም በሌላ ያሳበበው ስጋቱ እየተገለጠ ነው።

ጠዋት ይወጣል ማታ ይገባል። በሚገናኙበት ጊዜም ብዙም እንዲያወሩ አይፈልግም። የብሌን ትህትና መልክ አነጋገር ለወንዶች ቀዝቃዛ ወጥመድም ነው። በወጥመዱም ላለመያዝ ይሸሻል ግን ስሜቱ ባላወቀው መንገድ የተሸነፈ ይመስላል ወንድሙን እዮብን የከዳ ቃልኪዳኑን ያጠፈ ስሜት እስኪሰማው ያህል።

መሸሻ ፈለገ ከቤቱ የት ይሂድ? ብሌን ደግሞ እሷን ለአይኑ እንኳን የጠላት መስሏታል። ሊያናግራት አለመፈለጉ አይኖቹን ከእሷ ማሸሹ  ለወንድሙ ሞት ተጠያቂ እሷ የሆነች አድርጎ ያሰበ መሰላት። ትክክል ነው ከኔ ውጪ ለእዮብ ሞት ተጠያቂ ማነው? እዮብን ስታስብ በፀፀት ልትሞት ትደርሳለች። ስለ እሱም ላለመስማት ላለማሰብ ጥረት አድርጋለች ግን ከጭንቅላቷ ሊወጣላት አልቻለም። ቀስ በቀስ ድባቴ ውስጥ መግባት ጀመረች። ቀን ላይ ስለነበራት ህይወት አሁን ስላለችበት ስለወደፊቷ በማሰብ ራሷን ታስጨንቃለች። መሽቶም አልአዛር ሲመጣ ከአንድ ሁለት ቃላት ውጪ ንግግር ስለማይኖራቸው የመሰልቸት የተጠያቂነት ስሜቷ አየለባት።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/129
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል አስራ ሶስት
ትዝታ ከቤት እንደወጣች ብሌን በእፎይታ ሶፋው ላይ ተወረወረች። እዮብ ቢሆን እንደዚች አይነቷን አይደለም ለጓደኝነት ለአይንም ቢሆን ይጠየፋት ነበር ስትል አሰበች። መልካቸው ብቻ ነው ለካ የሚመሳሰለው አለች በልቧ። ምንም ስለአልአዛር የግል ህይወት አያገባኝም! ግን ምን ሲሆን ከእንደዚች አይነቷ ጋር ሆነ? ብሌን ከቅሬታዋ በላይ የሚሰማት ብስጭት መንስኤውን አለማወቋ አሳሰባት። ምን አልባት አልአዛርን እንደ እዮብ ቆጥራው ይሆናል። ወይም የወንድሙ ውለታ ስለሱ እንድትጨነቅ አስገድዷትም ይሆናል። ብቻ ተበሳጭታለች። ማታ አልአዛር እስኪመጣ መታገስ አቃታት።

እንደምንም መሸና አልአዛር ቤት መጣ። እራት ካቀረበች በኃላ "ትዝታ የምትባል ሴት መጥታ ነበር።" እዚ ስታጣህ ሱቅ ይኖራል ብዬ ብነግራትም ነገ መጣለው ብላ ሄደች አለች በዝምታ የተዋጠውን ማዕድ በማደፍረስ። እና ምን አለችሽ? የሚያስቀይም ነገር ተናገረችሽ? ጥያቄውን አከታትሎ ጠየቃት። አይ ምንም አልተናገረችም የናትናኤል እጮኛ ነኝ ብዬ ስነግራት ያመነችኝ ትመስላለች ... ብሌን እናቷን ስትዋሻት ሁሌም ታውቅባት ነበር። ትዝታ ግን አለማወቋ አስደስቷታል።

አልአዛር የብሌን ትዝታን ማየት ረፍት ነሳው። የትዝታ መጥፎ ባህሪያቶች ብቻ ሳይሆን ብሌን ከነጭራሹ ከትዝታ ጋር የነበረውን ነገር ባታውቅበት ይመርጣል። ዛሬ ካለወትሮው ወደ ስራ ለምን እንደሄደ አሰበ "ሽሽት" አለ በሆዱ። እኮ ከምን? መልሶ ራሱን ጠየቀ። ከብሌን? እሱማ አይሆንም በሌላ ያሳበበው ስጋቱ እየተገለጠ ነው።

ጠዋት ይወጣል ማታ ይገባል። በሚገናኙበት ጊዜም ብዙም እንዲያወሩ አይፈልግም። የብሌን ትህትና መልክ አነጋገር ለወንዶች ቀዝቃዛ ወጥመድም ነው። በወጥመዱም ላለመያዝ ይሸሻል ግን ስሜቱ ባላወቀው መንገድ የተሸነፈ ይመስላል ወንድሙን እዮብን የከዳ ቃልኪዳኑን ያጠፈ ስሜት እስኪሰማው ያህል።

መሸሻ ፈለገ ከቤቱ የት ይሂድ? ብሌን ደግሞ እሷን ለአይኑ እንኳን የጠላት መስሏታል። ሊያናግራት አለመፈለጉ አይኖቹን ከእሷ ማሸሹ  ለወንድሙ ሞት ተጠያቂ እሷ የሆነች አድርጎ ያሰበ መሰላት። ትክክል ነው ከኔ ውጪ ለእዮብ ሞት ተጠያቂ ማነው? እዮብን ስታስብ በፀፀት ልትሞት ትደርሳለች። ስለ እሱም ላለመስማት ላለማሰብ ጥረት አድርጋለች ግን ከጭንቅላቷ ሊወጣላት አልቻለም። ቀስ በቀስ ድባቴ ውስጥ መግባት ጀመረች። ቀን ላይ ስለነበራት ህይወት አሁን ስላለችበት ስለወደፊቷ በማሰብ ራሷን ታስጨንቃለች። መሽቶም አልአዛር ሲመጣ ከአንድ ሁለት ቃላት ውጪ ንግግር ስለማይኖራቸው የመሰልቸት የተጠያቂነት ስሜቷ አየለባት።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/129

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Russians and Ukrainians are both prolific users of Telegram. They rely on the app for channels that act as newsfeeds, group chats (both public and private), and one-to-one communication. Since the Russian invasion of Ukraine, Telegram has remained an important lifeline for both Russians and Ukrainians, as a way of staying aware of the latest news and keeping in touch with loved ones. You may recall that, back when Facebook started changing WhatsApp’s terms of service, a number of news outlets reported on, and even recommended, switching to Telegram. Pavel Durov even said that users should delete WhatsApp “unless you are cool with all of your photos and messages becoming public one day.” But Telegram can’t be described as a more-secure version of WhatsApp. I want a secure messaging app, should I use Telegram? In addition, Telegram's architecture limits the ability to slow the spread of false information: the lack of a central public feed, and the fact that comments are easily disabled in channels, reduce the space for public pushback. The Security Service of Ukraine said in a tweet that it was able to effectively target Russian convoys near Kyiv because of messages sent to an official Telegram bot account called "STOP Russian War."
from fr


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American