Telegram Group & Telegram Channel
​​አልወጣም ከቤቴ ቁ. ፪

ክፍል ፪(2)

ፈዲላም ተነስታ ወደ መኝታ ቤቷ ተመልሳ ገባች። ወዲያው ተኛች

ከምሽቱ 2፡00 ሲሆን የልጇን ደህንነት እንደ ምጥ ምትጠባበቅ እናት በድጋሚ መኝታ ቤቷን እያንኳኳች "ፈዲላ ተነሽ እራት ቀመስ አድርጊና ትተኛለሽ" ትል ጀመር። ፈዲላም ነቅታ ስለነበር "እሺ" አለቻት

ወደ ሻውር ቤት ገብታ ከተጣጠበች በኋላ ወደ ሳሎን ገባች

መሀመድ፡- ልጄ እንደምን አመሸሽ ነይ አጠገቤ

ፈዲላ፡- አባ አለሁ" እያለች አጠገቡ ቁጭ አለች

መሀመድ፡- ጥሩ ዜና አለኝ

ፈዲላ፡- ምንድን?

መሀመድ፡- ስራ አግኝቼልሻለሁ! ከአሁን በኋላ ራስን መጉዳት ቀን መተኛትና በድብርት መዋል የለም ስራ ትሰሪያለሽ አይምሮሽም ይመለሳል

ፈዲላ፡- እሺ" ከማለት ውጪ ሌላ ምንም አማራጭ አልነበራትም

ዘሀራም እራት አቀረበች ከወንድሞችና ከእህቶቿ ጋር እራቷን በላችና ተኛች። በነጋታውም መሀመድ ፈዲላን ቀሰቀሳትና "ዛሬ መስሪያ ቦታሽን አሳይሻለሁ ስራም ትጀምሪያለሽ ቶሎ ቶሎ ተዘጋጂ እንዳይረፍድብን" አላት።

ከተዘገጃጁም በኋላ አብረው ወደ ስራ ቦታ ሄዱ መሀመድም ስለ ፈዲላ በጣም ያስብ ነበርና ከድብርት እንድትወጣ የተለያዩ ሀሳቦችን በማንሳት ያዋራት ያወያያትም ነበር። በመጨረሻም ስለ ሀይማኖት አንድ ጥያቄ ጠየቃት

መሀመድ፡- ልጄ ግን ቁርአን አንብበሽ ታውቂያለሽ?

ፈዲላ፡- አዋ አባ ለምን አላነብም አነባለሁ

መሀመድ፡- እና በሀይማኖትሽ ትክክለኝነት እርግጠኛ ነሽ?

ፈዲላ፡- ይህን መመለስ ምችለው ሁሉም ሀይማኖቶች ውስጥ ያለውን ነገር መርምሬ ነው ስለዚህ አሁን የኢስላምን ትክክለኝነት በእርግጠኝነት አላቅም

መሀመድ፡- ወይ ልጄ እኔ አባትሽ ኡስታዝ ሆኜ አንቺ በኢስላም ሀይማኖት እርግጠኛ አይደለሁም ትያለሽ?
ስለ እስልምና መፅሀፉን አንብበሽ ተፍሲሩን ተረድተሽ ልትደርሺበት ትችያለሽ አንዲትም ስህተት የለውም! ነገር ግን ስለ ክርስትናና ስለ መፅሀፍ ቅዱስ ትክክል አለመሆን እኔ አባትሽ በደንብ አድርጌ አስተምርሻለሁ ኢንሻላህ።

በነገራችን ላይ ተወዳጆች ይህ ስልት ብዙዎች ወደ ክርስትናው አለም እንዳይመጡና ክርስትናና መፅሀፍ ቅዱስ ላይ የተለየ አመለካከት እንዲኖራቸው ከሚደረጉባቸው መነገዶች አንዱ ሲሆን የብዙ ሙስሊሞች ነፍስ መጥፋት ምክንያት ከሆኑት ዋነኛው ነው። ከኡስታዝ መፅሀፍ ቅዱስንንና ክርስትናን መማር"

ፈዲላ፡- እሺ አባ መልካም

መሀመድ፡- ጥሩ ልጄ ከዛን ኢስላም በፈጣሪ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሀይማኖት እንደሆነ ሌሎቹ በጠቅላላ ከንቱ እንደሆኑ ትረጃለሽ

ፈዲላ፡- እሺ

ብዙ ከተጓዙ በኋላ ስራ ቦታ ደረሱ ወደውስጥም ከገቡ በኋላ በአንድ ክርስቲያን ጓደኛው ጋር የምትሰራበትን ቦታ ምን እንደምትሰራና ምትገባበት የምትወጣበትን ሰአት በሙሉ እንዲያብራራላት አደረገ። ፈዲላም ስራውን ስትገምተው የምትወጣበትም የምትገባበትም ሰአት እንዲሁ ምቹ ስለሆነ በሀሳቡ ደስ ተሰኘች

ፍቃዱ(የመሀመድ ጓደኛ)፡- ዛሬዉኑ ስራሽን መጀመር ትችያለሽ እኔ ቀጥሎ ያለው ቢሮ ስለሆንኩ የፈለግሽውን ነገር ልትጠይቂኝ ትችያለሽ

ፈዲላ፡- እሺ አመሰግናለሁ " አለችና ወደ ተጠቆመችበት ቢሮ ገባች አራት ሴቶችም ነበሩ። ሰላምታም ከተቀባበሉ በኋላ የተዘጋጀላት ቦታ ላይ ተቀመጠች።

ማህተምን በመምታት ሌሎች ስሮችንም በመሰራራት እንዲሁ እስከ 10 ሰአት ድረስ ቆየች በዛን ቀን ስራው ትንሽ አይምሮዋን ጠምዶት ስለነበር ስለ ሳሙኤል ብዙ አላሰበችም ነበር።

የሚወጡበት ሰአት በደረሰ ጊዜ ወደ ኋላ ቀረት ያለችውን ሰራተኛዋን ልትግባባት ፈልጋ ነበርና

ፈዲላ፡- ይቅርታ ሁሌ በዚህ ሰአት ነው የምንወጣው?

ኤልሳቤጥ ፡- አዎን እህት በዚህ ሰአት ነው ሁሌ የምንወጣው

ፈዲላ፡- መልካም እንተዋወቅ ፈዲላ እባላለሁ ፈዱ በይኝ ክክክክ

ኤልሳቤጥ ፡- ክክክክ እሺ ፈዱ እኔ ደግሞ ኤልሳቤጥ እባላለሁ

ፈዲላ፡- መልካም ስለተዋወቅኩሽ ደስ ብሎኛል

ኤልሳቤጥ፡- እኔም

ፈዲላ፡- እሺ ንገሪኝ ምን አይነት ሰው ነሽ ምን ትወጃለሽ ምን ትጠያለሽ" እያወሩና እየተግባቡ ወደ ታክሲ መያዣ ደረሱ። ፈዲላም መኪና አልያዘችም ነበርና ታክሲ የግድ መሳፈር ነበረባት።

ከተለያዩም በኋላ ፈዲላ ወደ ቤቷ እንደገባች እጅጉን ተደሰተች ቀኑን መልካም ና ጥሩ በሆነ ሁኔታ ስላሳለፈች እንዲሁም አንዲስ ጓደኛ ስለተዋወቀች ስሜቷ አሪፍ ነበር።

ይህንን ሁኔታ የተመለከተችው የፈዲላ እናት ዘሀራ እጅጉን ደስ አላት ልጄ ተመለሰችልኝ በማለት ፈጠረኝ ብላ ምታስበውን አካለ እጅጉን አመሰገነች። መሀመድም ተጨንቆ ነበርና ይህንን ሁኔታ ሲያይ ይህንኑ አደረገ ።

መሀመድ፡- ፈዲላ ደክሞሻል እንዴ

ፈዲላ፡- አይ አባ ምነው

መሀመድ፡- ስለ ጠዋቱ ውይይት ከዛሬ እንድንጀምር ብዬ ነው ሀይማኖታዊ ጥናት

ፈዲላ፡- አይ አልደከመኝም እሺ ተታጥቤ መጣሁ

መሀመድ፡- እሺ የኔ ልጅ "አለና ወደ ሳሎን ተመልሶ መፅሀፍቶቹን ማዘገጃጀት ጀመረ። እንደጨረሰችም ወደ ሳሎን ዘለቀች መሀመድም "መጣሽ ልጄ ቁጭ በይ" አላት ቁጭም አለች።


መሀመድ፡- እንግዲህ አሁን የምታያቸው መፅሀፍት ባይብልና ቅዱስ ቁርአን ናቸው ሁለቱም የአላህ ቃል ናቸው ነገር ግን ባይብል በአይሁድና በክርስቲያኖች ስለተበረዘ የምንቀበለው ነገር በጣም ትንሹን ነው።

ፈዲላ፡- እሺ አባ ለምን ተበረዘ

መሀመድ፡- እነሱ የሚፈልጉትንና ከኑሯቸው ጋር ሊስማማ ሚችለውን ነገር መጨመር ስለኖረባቸው ነው።

ፈዲላ፡- እሺ

ይቀጥላል...........
@THESECRETKNOWITFIRST



group-telegram.com/THESECRETKNOWITFIRST/324
Create:
Last Update:

​​አልወጣም ከቤቴ ቁ. ፪

ክፍል ፪(2)

ፈዲላም ተነስታ ወደ መኝታ ቤቷ ተመልሳ ገባች። ወዲያው ተኛች

ከምሽቱ 2፡00 ሲሆን የልጇን ደህንነት እንደ ምጥ ምትጠባበቅ እናት በድጋሚ መኝታ ቤቷን እያንኳኳች "ፈዲላ ተነሽ እራት ቀመስ አድርጊና ትተኛለሽ" ትል ጀመር። ፈዲላም ነቅታ ስለነበር "እሺ" አለቻት

ወደ ሻውር ቤት ገብታ ከተጣጠበች በኋላ ወደ ሳሎን ገባች

መሀመድ፡- ልጄ እንደምን አመሸሽ ነይ አጠገቤ

ፈዲላ፡- አባ አለሁ" እያለች አጠገቡ ቁጭ አለች

መሀመድ፡- ጥሩ ዜና አለኝ

ፈዲላ፡- ምንድን?

መሀመድ፡- ስራ አግኝቼልሻለሁ! ከአሁን በኋላ ራስን መጉዳት ቀን መተኛትና በድብርት መዋል የለም ስራ ትሰሪያለሽ አይምሮሽም ይመለሳል

ፈዲላ፡- እሺ" ከማለት ውጪ ሌላ ምንም አማራጭ አልነበራትም

ዘሀራም እራት አቀረበች ከወንድሞችና ከእህቶቿ ጋር እራቷን በላችና ተኛች። በነጋታውም መሀመድ ፈዲላን ቀሰቀሳትና "ዛሬ መስሪያ ቦታሽን አሳይሻለሁ ስራም ትጀምሪያለሽ ቶሎ ቶሎ ተዘጋጂ እንዳይረፍድብን" አላት።

ከተዘገጃጁም በኋላ አብረው ወደ ስራ ቦታ ሄዱ መሀመድም ስለ ፈዲላ በጣም ያስብ ነበርና ከድብርት እንድትወጣ የተለያዩ ሀሳቦችን በማንሳት ያዋራት ያወያያትም ነበር። በመጨረሻም ስለ ሀይማኖት አንድ ጥያቄ ጠየቃት

መሀመድ፡- ልጄ ግን ቁርአን አንብበሽ ታውቂያለሽ?

ፈዲላ፡- አዋ አባ ለምን አላነብም አነባለሁ

መሀመድ፡- እና በሀይማኖትሽ ትክክለኝነት እርግጠኛ ነሽ?

ፈዲላ፡- ይህን መመለስ ምችለው ሁሉም ሀይማኖቶች ውስጥ ያለውን ነገር መርምሬ ነው ስለዚህ አሁን የኢስላምን ትክክለኝነት በእርግጠኝነት አላቅም

መሀመድ፡- ወይ ልጄ እኔ አባትሽ ኡስታዝ ሆኜ አንቺ በኢስላም ሀይማኖት እርግጠኛ አይደለሁም ትያለሽ?
ስለ እስልምና መፅሀፉን አንብበሽ ተፍሲሩን ተረድተሽ ልትደርሺበት ትችያለሽ አንዲትም ስህተት የለውም! ነገር ግን ስለ ክርስትናና ስለ መፅሀፍ ቅዱስ ትክክል አለመሆን እኔ አባትሽ በደንብ አድርጌ አስተምርሻለሁ ኢንሻላህ።

በነገራችን ላይ ተወዳጆች ይህ ስልት ብዙዎች ወደ ክርስትናው አለም እንዳይመጡና ክርስትናና መፅሀፍ ቅዱስ ላይ የተለየ አመለካከት እንዲኖራቸው ከሚደረጉባቸው መነገዶች አንዱ ሲሆን የብዙ ሙስሊሞች ነፍስ መጥፋት ምክንያት ከሆኑት ዋነኛው ነው። ከኡስታዝ መፅሀፍ ቅዱስንንና ክርስትናን መማር"

ፈዲላ፡- እሺ አባ መልካም

መሀመድ፡- ጥሩ ልጄ ከዛን ኢስላም በፈጣሪ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሀይማኖት እንደሆነ ሌሎቹ በጠቅላላ ከንቱ እንደሆኑ ትረጃለሽ

ፈዲላ፡- እሺ

ብዙ ከተጓዙ በኋላ ስራ ቦታ ደረሱ ወደውስጥም ከገቡ በኋላ በአንድ ክርስቲያን ጓደኛው ጋር የምትሰራበትን ቦታ ምን እንደምትሰራና ምትገባበት የምትወጣበትን ሰአት በሙሉ እንዲያብራራላት አደረገ። ፈዲላም ስራውን ስትገምተው የምትወጣበትም የምትገባበትም ሰአት እንዲሁ ምቹ ስለሆነ በሀሳቡ ደስ ተሰኘች

ፍቃዱ(የመሀመድ ጓደኛ)፡- ዛሬዉኑ ስራሽን መጀመር ትችያለሽ እኔ ቀጥሎ ያለው ቢሮ ስለሆንኩ የፈለግሽውን ነገር ልትጠይቂኝ ትችያለሽ

ፈዲላ፡- እሺ አመሰግናለሁ " አለችና ወደ ተጠቆመችበት ቢሮ ገባች አራት ሴቶችም ነበሩ። ሰላምታም ከተቀባበሉ በኋላ የተዘጋጀላት ቦታ ላይ ተቀመጠች።

ማህተምን በመምታት ሌሎች ስሮችንም በመሰራራት እንዲሁ እስከ 10 ሰአት ድረስ ቆየች በዛን ቀን ስራው ትንሽ አይምሮዋን ጠምዶት ስለነበር ስለ ሳሙኤል ብዙ አላሰበችም ነበር።

የሚወጡበት ሰአት በደረሰ ጊዜ ወደ ኋላ ቀረት ያለችውን ሰራተኛዋን ልትግባባት ፈልጋ ነበርና

ፈዲላ፡- ይቅርታ ሁሌ በዚህ ሰአት ነው የምንወጣው?

ኤልሳቤጥ ፡- አዎን እህት በዚህ ሰአት ነው ሁሌ የምንወጣው

ፈዲላ፡- መልካም እንተዋወቅ ፈዲላ እባላለሁ ፈዱ በይኝ ክክክክ

ኤልሳቤጥ ፡- ክክክክ እሺ ፈዱ እኔ ደግሞ ኤልሳቤጥ እባላለሁ

ፈዲላ፡- መልካም ስለተዋወቅኩሽ ደስ ብሎኛል

ኤልሳቤጥ፡- እኔም

ፈዲላ፡- እሺ ንገሪኝ ምን አይነት ሰው ነሽ ምን ትወጃለሽ ምን ትጠያለሽ" እያወሩና እየተግባቡ ወደ ታክሲ መያዣ ደረሱ። ፈዲላም መኪና አልያዘችም ነበርና ታክሲ የግድ መሳፈር ነበረባት።

ከተለያዩም በኋላ ፈዲላ ወደ ቤቷ እንደገባች እጅጉን ተደሰተች ቀኑን መልካም ና ጥሩ በሆነ ሁኔታ ስላሳለፈች እንዲሁም አንዲስ ጓደኛ ስለተዋወቀች ስሜቷ አሪፍ ነበር።

ይህንን ሁኔታ የተመለከተችው የፈዲላ እናት ዘሀራ እጅጉን ደስ አላት ልጄ ተመለሰችልኝ በማለት ፈጠረኝ ብላ ምታስበውን አካለ እጅጉን አመሰገነች። መሀመድም ተጨንቆ ነበርና ይህንን ሁኔታ ሲያይ ይህንኑ አደረገ ።

መሀመድ፡- ፈዲላ ደክሞሻል እንዴ

ፈዲላ፡- አይ አባ ምነው

መሀመድ፡- ስለ ጠዋቱ ውይይት ከዛሬ እንድንጀምር ብዬ ነው ሀይማኖታዊ ጥናት

ፈዲላ፡- አይ አልደከመኝም እሺ ተታጥቤ መጣሁ

መሀመድ፡- እሺ የኔ ልጅ "አለና ወደ ሳሎን ተመልሶ መፅሀፍቶቹን ማዘገጃጀት ጀመረ። እንደጨረሰችም ወደ ሳሎን ዘለቀች መሀመድም "መጣሽ ልጄ ቁጭ በይ" አላት ቁጭም አለች።


መሀመድ፡- እንግዲህ አሁን የምታያቸው መፅሀፍት ባይብልና ቅዱስ ቁርአን ናቸው ሁለቱም የአላህ ቃል ናቸው ነገር ግን ባይብል በአይሁድና በክርስቲያኖች ስለተበረዘ የምንቀበለው ነገር በጣም ትንሹን ነው።

ፈዲላ፡- እሺ አባ ለምን ተበረዘ

መሀመድ፡- እነሱ የሚፈልጉትንና ከኑሯቸው ጋር ሊስማማ ሚችለውን ነገር መጨመር ስለኖረባቸው ነው።

ፈዲላ፡- እሺ

ይቀጥላል...........
@THESECRETKNOWITFIRST

BY THE SECRET KNOW IT FIRST


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/THESECRETKNOWITFIRST/324

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Perpetrators of such fraud use various marketing techniques to attract subscribers on their social media channels. Ukrainian President Volodymyr Zelensky said in a video message on Tuesday that Ukrainian forces "destroy the invaders wherever we can." Right now the digital security needs of Russians and Ukrainians are very different, and they lead to very different caveats about how to mitigate the risks associated with using Telegram. For Ukrainians in Ukraine, whose physical safety is at risk because they are in a war zone, digital security is probably not their highest priority. They may value access to news and communication with their loved ones over making sure that all of their communications are encrypted in such a manner that they are indecipherable to Telegram, its employees, or governments with court orders. Telegram, which does little policing of its content, has also became a hub for Russian propaganda and misinformation. Many pro-Kremlin channels have become popular, alongside accounts of journalists and other independent observers. Individual messages can be fully encrypted. But the user has to turn on that function. It's not automatic, as it is on Signal and WhatsApp.
from hk


Telegram THE SECRET KNOW IT FIRST
FROM American