Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94087-94088-94089-94090-94091-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94090 -
Telegram Group & Telegram Channel
" ተመዝግበንና ክፍያም ከፍለናቸው ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ ባለንበት ዩኒቨርሲቲዉ አላስተምራችሁም ብሎናል " - የሪሚዲያል ተማሪዎች

➡️ " ዉሳኔዉ የትምህርት ሚንስቴ እንጂ የዩኒቨርሲቲው አይደለም " - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ

" የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከሁለት ወራት ፊት በሣምንቱ የዕረፍት ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ባወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት የምዝገባ እና የመማሪያ ክፍያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ እያለን ዩኒቨርሲቲው ሌሎች አማራጮችን መጠቀሚያ ጊዜ ባለፈብን በዚህ ወቅት አላስተምራችሁም ብሎናል " ሲሉ ተማሪዎሽ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

ቅሬታቸዉን ካደረሱን ተማሪዎች መካከል በመደበኛው የትምህርት ሚንስቴር ምደባ ጅግጅጋ ፣ሰላሌ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተመደብዉ እያለ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) በእረፍት ቀናት በክፍያ ለማስተማር ማስታወቂያ ማዉጣቱን ተከትሎ ከቤተሰብ ላለመራቅና በአንዳንድ አከባቢዎች ካለዉ የፀጥታ ችግር የተነሳ ከፍለዉ ለመማር በመወሰን የምዝገባና የትምህርት ክፍያ አጠናቀው የትምህርት መጀመርን ሲጠባበቁ እንደነበር ገልፀዉ ዩኒቨርሲቲዉ " ኃላፊነት በጎደለው መልኩ 'ትምህርት ሚንስቴር በግል ከፍሎ መማርን ስላልፈቀደ ማስተማር የማንችል በመሆኑ ክፍያችሁን መዉሰድ ትችላላችሁ ' ብሎ የለጠፈዉ ማስታወቂያ እጅግ አሳዝኖናል " ብለዋል።

በተመደብንባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች መሄድ በማንችልበትና ሌሎችም በግል ኮሌጆች ከፍለን የመማሪያ ጊዜዉ ካለፈብን በኋላ የተወሰነዉ ይህ ዉሳኔ ከጊዜ እና ገንዘብ ጉልበት ብክነት ባሻገር በስነልቦናም ጉዳት አድርሶብናል ብለዋል።

ተማሪዎቹ ቅሬታቸዉን ለዩኒቨርሲቲዉና በግልባጭ ለትምህርት ሚንስቴርም ማቅረባቸውን ገልፀዉ የሚመለከተዉ አካል አስፈላጊውን መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌን አግኝቶ በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግሯል።

ዶክተር ቅሬታዉ እንደደረሳቸዉና ዩኒቨርሲቲዉ ከዚህ ቀደም እንደሚያደርገዉ ሁሉ " በሣምንቱ መጨረሻ ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለመስጠት ማስታወቂያ ማዉጣቱንና 400 የሚሆኑ ተማሪዎች ተመዝግበው ክፍያ ላጠናቀቁ ተማሪዎች ትምህርት የመጀመር ሂደት ላይ እያለን ትምህርት ሚንስቴር በሰጠዉ ትዕዛዝ መሰረት ማስተማር ስለማንችል ማስታወቂያ ለጥፈናል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዩኒቨርቲዉ ለማስተማር ካለዉ ፍላጎት የተነሳ ተማሪዎችን መዝግቦ ወደ መማር ማስተማር ሂደት በመግባት ሂደት ላይ እንደነበር ያስታወሱት ፕሬዘረዳንቱ የተማሪዎችንና የወላጆችን ቅሬታ ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ትምህርት ሚንስቴር በማቅረብ ሂደት ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

" በሚንስትር መስሪያ ቤቱ ምላሽ ላይ ተመስርተን ' አስተምሩ ' የሚባል ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች የሚገኙ ከሆነ ለተማሪዎቹ ጥሪ እናቀርባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።

ጉዳዩን ተከታትለን ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94090
Create:
Last Update:

" ተመዝግበንና ክፍያም ከፍለናቸው ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ ባለንበት ዩኒቨርሲቲዉ አላስተምራችሁም ብሎናል " - የሪሚዲያል ተማሪዎች

➡️ " ዉሳኔዉ የትምህርት ሚንስቴ እንጂ የዩኒቨርሲቲው አይደለም " - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ

" የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከሁለት ወራት ፊት በሣምንቱ የዕረፍት ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ባወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት የምዝገባ እና የመማሪያ ክፍያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ እያለን ዩኒቨርሲቲው ሌሎች አማራጮችን መጠቀሚያ ጊዜ ባለፈብን በዚህ ወቅት አላስተምራችሁም ብሎናል " ሲሉ ተማሪዎሽ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

ቅሬታቸዉን ካደረሱን ተማሪዎች መካከል በመደበኛው የትምህርት ሚንስቴር ምደባ ጅግጅጋ ፣ሰላሌ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተመደብዉ እያለ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) በእረፍት ቀናት በክፍያ ለማስተማር ማስታወቂያ ማዉጣቱን ተከትሎ ከቤተሰብ ላለመራቅና በአንዳንድ አከባቢዎች ካለዉ የፀጥታ ችግር የተነሳ ከፍለዉ ለመማር በመወሰን የምዝገባና የትምህርት ክፍያ አጠናቀው የትምህርት መጀመርን ሲጠባበቁ እንደነበር ገልፀዉ ዩኒቨርሲቲዉ " ኃላፊነት በጎደለው መልኩ 'ትምህርት ሚንስቴር በግል ከፍሎ መማርን ስላልፈቀደ ማስተማር የማንችል በመሆኑ ክፍያችሁን መዉሰድ ትችላላችሁ ' ብሎ የለጠፈዉ ማስታወቂያ እጅግ አሳዝኖናል " ብለዋል።

በተመደብንባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች መሄድ በማንችልበትና ሌሎችም በግል ኮሌጆች ከፍለን የመማሪያ ጊዜዉ ካለፈብን በኋላ የተወሰነዉ ይህ ዉሳኔ ከጊዜ እና ገንዘብ ጉልበት ብክነት ባሻገር በስነልቦናም ጉዳት አድርሶብናል ብለዋል።

ተማሪዎቹ ቅሬታቸዉን ለዩኒቨርሲቲዉና በግልባጭ ለትምህርት ሚንስቴርም ማቅረባቸውን ገልፀዉ የሚመለከተዉ አካል አስፈላጊውን መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌን አግኝቶ በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግሯል።

ዶክተር ቅሬታዉ እንደደረሳቸዉና ዩኒቨርሲቲዉ ከዚህ ቀደም እንደሚያደርገዉ ሁሉ " በሣምንቱ መጨረሻ ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለመስጠት ማስታወቂያ ማዉጣቱንና 400 የሚሆኑ ተማሪዎች ተመዝግበው ክፍያ ላጠናቀቁ ተማሪዎች ትምህርት የመጀመር ሂደት ላይ እያለን ትምህርት ሚንስቴር በሰጠዉ ትዕዛዝ መሰረት ማስተማር ስለማንችል ማስታወቂያ ለጥፈናል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዩኒቨርቲዉ ለማስተማር ካለዉ ፍላጎት የተነሳ ተማሪዎችን መዝግቦ ወደ መማር ማስተማር ሂደት በመግባት ሂደት ላይ እንደነበር ያስታወሱት ፕሬዘረዳንቱ የተማሪዎችንና የወላጆችን ቅሬታ ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ትምህርት ሚንስቴር በማቅረብ ሂደት ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

" በሚንስትር መስሪያ ቤቱ ምላሽ ላይ ተመስርተን ' አስተምሩ ' የሚባል ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች የሚገኙ ከሆነ ለተማሪዎቹ ጥሪ እናቀርባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።

ጉዳዩን ተከታትለን ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94090

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Two days after Russia invaded Ukraine, an account on the Telegram messaging platform posing as President Volodymyr Zelenskiy urged his armed forces to surrender. Additionally, investors are often instructed to deposit monies into personal bank accounts of individuals who claim to represent a legitimate entity, and/or into an unrelated corporate account. To lend credence and to lure unsuspecting victims, perpetrators usually claim that their entity and/or the investment schemes are approved by financial authorities. In December 2021, Sebi officials had conducted a search and seizure operation at the premises of certain persons carrying out similar manipulative activities through Telegram channels. "The inflation fire was already hot and now with war-driven inflation added to the mix, it will grow even hotter, setting off a scramble by the world’s central banks to pull back their stimulus earlier than expected," Chris Rupkey, chief economist at FWDBONDS, wrote in an email. "A spike in inflation rates has preceded economic recessions historically and this time prices have soared to levels that once again pose a threat to growth." The regulator took order for the search and seizure operation from Judge Purushottam B Jadhav, Sebi Special Judge / Additional Sessions Judge.
from hk


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American