Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቄዶንያ “ ህንፃው ለማጠናቀቅ ገንዘብ ተቸግረናል። ለማጠናቀቅ ወደ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልገናል ” - መቄዶንያ መቄዶንያ የአረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል በሚያስገነባው ሆስፒታል ጭምር ያለው ህንፃ ለማጠናቀቅ የገንዘብ እጥረት ስለገጠመው እርዳታ እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበ። ከየካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ “ በሰይፉ ኢቢኤስ የዩቱብ ቻነል ” ድጋፍ ማድረጊያ መርሀ ግብር ስለሚጀመር…
“ ለአእምሮ ህሙማን ብቻ በየወሩ እስከ 5 ሚሊዮን ብር መድኃኒት እንገዛለን። የህክምና ባለሙዎች እጥረት አለብን ” - የመቄዶኒያ ህክምና ክፍል

የመቄዶንያ አረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መረጃ ማዕከል ህክምና ክፍል የመድኃኒት መወደድና የስፔሻሊት ሀኪሞች እጥረት እንደፈተነው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

የማዕከሉ የህክምና ክፍል አስተባባሪ አቶ ዮናስ ሙሉጌታ በሰጡን ቃል፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ እውቀት ያለው በእውቀቱ፣ ጳጳሳቱ በጸሎታቸው እርዳታ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የማዕከሉ ህክምና ክፍል በዝርዝር ምን አለ?

በመቄዶንያ ካሉት 8,000 ሰዎች ወደ 2000 የሚሆኑት የአእምሮ ህሙማን ናቸው። የአእምሮ ህሙማኑ መድኃኒቶች ደግሞ ብዙ ጊዜ አገር ውስጥ አይገኙም።

ቢኖሩም ውስን ፋብሪካዎች ናቸው የሚያመርቷቸው ጥሬ እቃ ከውጪ አገር እያስመጡ። የተወሰኑ መድኃኒቶችም በቀጥታ ከውጪ አገር ነው የሚመጡት። 

ከገበያ የሚጠፉ መድኃኒቶችም አሉ ከምንዛሪ እጥረት ጋር በተያያዘ። መድኃኒቶቹ መጥፋታቸው ህሙማኑ ህመሙ እንዲያርሽባቸው ይዳርጋቸዋል። ወደ ጤንነታቸው ለመመለስም ጊዜ ይወዳል።

አዲስ አበባ፣ ሰንዳፋ፣ ፃድቃኔ፣ ሶማሌ ክልል ጎዴ፣ አማራ ክልል ደሴ፣ ሀረር፣ ድሴዳዋ በብዛት የአእምሮ ህሙማን የሚገኙባቸው ቦታዎች ናቸው። 

በመቄዶንያ ደግሞ የአእምሮ ህሙማንና አረጋዊያን ብቻ ሳይሆኑ ያሉት የደም ግፊት፣ ስኳር፣ አስም፣ ካንሰር፣ የኩላሊት (ዲያሌሲስ የሚያደርጉ) ህሙማንም አሉ። 

የአእምሮ ህሙማን መድኃኒቶች በጣም ውድ ናቸው። የምንገዛው ከኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ነው። ለአእምሮ ህሙማን ብቻ በየወሩ እስከ 5 ሚሊዮን ብር እንገዛለን። የህክምና ባለሙያዎች እጥረት አለብን”
ብሏል።

“ካለው ቁጥር አንጻር የባለሙያዎች ቁጥር በቂ አይደለም። ሳይካትሪ እንኳ ወደ 18 ነው የሚሆኑት። ግን ስፔሻሊስቶች ያስፈልጉናል። ባለሙያዎች በበጎ ፈቃደኝነት እንዲያገለግሉ እንፈልጋለን” ሲልም ጥሪ አቅርቧል።

“በወር ለአንድ እንኳ ሰዓት የህክምና አገልግሎት ቢሰጡ ለህሙማኑ ቀላል አይደለም” ያሉት የህክምና ክፍሉ፣ “የአእምሮ ስፔሻሊቲ፣ የዓይን፣ የጥርስ፣ የፊዚዮትራፒ፣ የሳይኮሎጁ ባለሙያዎች እጥረት አለብን” ብለዋል።

በሙያቸው ወደ ውጪ አገር ሂደው በትላልቅ የህክምና ተቋማት፣ ፋብሪካዎች የሚሰሩ ወገኖች መድኃኒት ቢልኩላቸው መቄዶንያ በህጋዊ መንገድ ፕሮሰስ አድርጎ መቀበል እንደሚችል፣ ድጋፉ ቢገኝ ህሙማን ሳያቋርጡ ህክምናቸውን መከታተል እንደሚችሉ ተመልክቷል።

#ማስታወሻ : የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በSiefu Show Tube ላይ ድጋፍ ለማድረግ ይዘጋጁ።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94281
Create:
Last Update:

“ ለአእምሮ ህሙማን ብቻ በየወሩ እስከ 5 ሚሊዮን ብር መድኃኒት እንገዛለን። የህክምና ባለሙዎች እጥረት አለብን ” - የመቄዶኒያ ህክምና ክፍል

የመቄዶንያ አረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማን መረጃ ማዕከል ህክምና ክፍል የመድኃኒት መወደድና የስፔሻሊት ሀኪሞች እጥረት እንደፈተነው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

የማዕከሉ የህክምና ክፍል አስተባባሪ አቶ ዮናስ ሙሉጌታ በሰጡን ቃል፤ ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ እውቀት ያለው በእውቀቱ፣ ጳጳሳቱ በጸሎታቸው እርዳታ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

የማዕከሉ ህክምና ክፍል በዝርዝር ምን አለ?

በመቄዶንያ ካሉት 8,000 ሰዎች ወደ 2000 የሚሆኑት የአእምሮ ህሙማን ናቸው። የአእምሮ ህሙማኑ መድኃኒቶች ደግሞ ብዙ ጊዜ አገር ውስጥ አይገኙም።

ቢኖሩም ውስን ፋብሪካዎች ናቸው የሚያመርቷቸው ጥሬ እቃ ከውጪ አገር እያስመጡ። የተወሰኑ መድኃኒቶችም በቀጥታ ከውጪ አገር ነው የሚመጡት። 

ከገበያ የሚጠፉ መድኃኒቶችም አሉ ከምንዛሪ እጥረት ጋር በተያያዘ። መድኃኒቶቹ መጥፋታቸው ህሙማኑ ህመሙ እንዲያርሽባቸው ይዳርጋቸዋል። ወደ ጤንነታቸው ለመመለስም ጊዜ ይወዳል።

አዲስ አበባ፣ ሰንዳፋ፣ ፃድቃኔ፣ ሶማሌ ክልል ጎዴ፣ አማራ ክልል ደሴ፣ ሀረር፣ ድሴዳዋ በብዛት የአእምሮ ህሙማን የሚገኙባቸው ቦታዎች ናቸው። 

በመቄዶንያ ደግሞ የአእምሮ ህሙማንና አረጋዊያን ብቻ ሳይሆኑ ያሉት የደም ግፊት፣ ስኳር፣ አስም፣ ካንሰር፣ የኩላሊት (ዲያሌሲስ የሚያደርጉ) ህሙማንም አሉ። 

የአእምሮ ህሙማን መድኃኒቶች በጣም ውድ ናቸው። የምንገዛው ከኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦት አገልግሎት ነው። ለአእምሮ ህሙማን ብቻ በየወሩ እስከ 5 ሚሊዮን ብር እንገዛለን። የህክምና ባለሙያዎች እጥረት አለብን”
ብሏል።

“ካለው ቁጥር አንጻር የባለሙያዎች ቁጥር በቂ አይደለም። ሳይካትሪ እንኳ ወደ 18 ነው የሚሆኑት። ግን ስፔሻሊስቶች ያስፈልጉናል። ባለሙያዎች በበጎ ፈቃደኝነት እንዲያገለግሉ እንፈልጋለን” ሲልም ጥሪ አቅርቧል።

“በወር ለአንድ እንኳ ሰዓት የህክምና አገልግሎት ቢሰጡ ለህሙማኑ ቀላል አይደለም” ያሉት የህክምና ክፍሉ፣ “የአእምሮ ስፔሻሊቲ፣ የዓይን፣ የጥርስ፣ የፊዚዮትራፒ፣ የሳይኮሎጁ ባለሙያዎች እጥረት አለብን” ብለዋል።

በሙያቸው ወደ ውጪ አገር ሂደው በትላልቅ የህክምና ተቋማት፣ ፋብሪካዎች የሚሰሩ ወገኖች መድኃኒት ቢልኩላቸው መቄዶንያ በህጋዊ መንገድ ፕሮሰስ አድርጎ መቀበል እንደሚችል፣ ድጋፉ ቢገኝ ህሙማን ሳያቋርጡ ህክምናቸውን መከታተል እንደሚችሉ ተመልክቷል።

#ማስታወሻ : የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ/ም በSiefu Show Tube ላይ ድጋፍ ለማድረግ ይዘጋጁ።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94281

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

So, uh, whenever I hear about Telegram, it’s always in relation to something bad. What gives? Two days after Russia invaded Ukraine, an account on the Telegram messaging platform posing as President Volodymyr Zelenskiy urged his armed forces to surrender. On December 23rd, 2020, Pavel Durov posted to his channel that the company would need to start generating revenue. In early 2021, he added that any advertising on the platform would not use user data for targeting, and that it would be focused on “large one-to-many channels.” He pledged that ads would be “non-intrusive” and that most users would simply not notice any change. The gold standard of encryption, known as end-to-end encryption, where only the sender and person who receives the message are able to see it, is available on Telegram only when the Secret Chat function is enabled. Voice and video calls are also completely encrypted. Oh no. There’s a certain degree of myth-making around what exactly went on, so take everything that follows lightly. Telegram was originally launched as a side project by the Durov brothers, with Nikolai handling the coding and Pavel as CEO, while both were at VK.
from hk


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American