Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቐለ መቐለ ከተማ ውስጥ በጭካኔ የተገደለች እንስት አስከሬንዋ ከ2 ቀን በኋላ መገኘቱን ፓሊስ አስታውቋል። የጭካኔ ተግባሩ የት ፣ መቼ ፣ እንዴት ተፈፀመ ? የጭካኔ ተግባሩ በትግራይ ፣ መቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ዓዲሓ ተብሎ በሚጠራው ልዩ ሰፈር በሚገኝ የአንድ ሆቴል ክፍል ነው የተፈፀመው። ሓበን የማነ የ19 ዓመት ወጣት ስትሆን በሆቴል ክፍል #በቢላዋ ተገድላ መገኘትዋና ጥቅምት 20 /2017…
#መቐለ

" ተጠርጣሪው ተይዞ ለክልሉ ፖሊስ ተላለልፎ ተሰጥቷል " - ፖሊስ

የ19 ዓመትዋን ወጣት በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ በፓሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል።

የመቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጸው ፥ ጥቅምት 19 /2017 ዓ.ም ሓበን የማነ የተባለች ፍቅረኛውን በተከራዩት የሆቴል ክፍል በጬቤ በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ ከቀናት ፍለጋ በኃላ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።

በአሰቃቂ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ዳዊት ዘርኡ ተወልደ የተባለው ግለሰብ አሰቃቂ ተግባሩን ፈፅሞ በመሰወሩ ሲፈለግ ቆይቷል።

የሟች ቤተሰብ ጨምሮ በርካታ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች በከባድ ግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ግለሰብ ከትግራይ ክልል ወጥቶ በአማራ ክልል በኩል ሊያመልጥ ሲል በደሴ ከተማ መያዙን ፅፈዋል።

የመረጃው ትክክለኝነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያረጋገጡት የሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሲስ አዛዥ ሞገስ ወርቁ ፥ ተጠርጣሪው በዛሬው ቀን ጥቅምት  27/2017 ዓ.ም ለክልሉ ፓሊስ ተላለልፎ መሰጠቱን ገልፀዋል።

ግለሰቡ ደሴ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ ለፖሊስ ጥቆማ በመድረሱ ነው ሊያዝ የቻለው።

ከክልል ፖሊስ በተገኘው መረጃ ደግሞ ግለሰቡ በአላማጣ አድርጎ ነው ወደ ደሴ የተጓዘው። ወደዛ የሄደውም በረዳት ሹፌርነት ነው።

አንድ ለሊትም በደሴ ከተማ ካሳለፈ በኃላ ሰውነቱ ላይ ያለውን ንቅሳት የሚሸፍን ልብስ ገዝቶ ወደ ያዘው መኝታ ክፍል ሲገባ በደረሰ ጥቆማ ሊያዝ ችሏል። ከዛም መቐለ ፖሊስ አባላቱን በመላክ ተጠርጣሪው ወደ መቐለ እንዲመጣ አድርጓል።

የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም የደሴ ህዝብ ላደረገው ትብብር ምስጋና አቅርቧል።

በከባድ የግድያ ተግባር የተጠረጠረው ግለሰብ አስመልክቶ በማህበራዊ የትስስር ገፆች የተሰራጨው አጭር ቪድዮ እንደሚያመለክተው ፥ ተጠርጣሪው ፍቅረኛውን በጬቤ ከገደላት በኋላ ተፀፅቶ ራሱ ለመግደል ሞኩሮ ሳይሳካለት መቅረቱ በአንደበቱ ይገልፃል።

የሟች ወጣት ሓበን የማነ አባት አቶ የማነ ንጉስ ልጃቸው በጭካኔ በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ በአጭር ጊዜ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ለተባበሩ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

የፎቶ ባለቤት ፦ የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን

@tikvahethiopia 



group-telegram.com/tikvahethiopia/91950
Create:
Last Update:

#መቐለ

" ተጠርጣሪው ተይዞ ለክልሉ ፖሊስ ተላለልፎ ተሰጥቷል " - ፖሊስ

የ19 ዓመትዋን ወጣት በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ በፓሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል።

የመቐለ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጸው ፥ ጥቅምት 19 /2017 ዓ.ም ሓበን የማነ የተባለች ፍቅረኛውን በተከራዩት የሆቴል ክፍል በጬቤ በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ ከቀናት ፍለጋ በኃላ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።

በአሰቃቂ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ዳዊት ዘርኡ ተወልደ የተባለው ግለሰብ አሰቃቂ ተግባሩን ፈፅሞ በመሰወሩ ሲፈለግ ቆይቷል።

የሟች ቤተሰብ ጨምሮ በርካታ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች በከባድ ግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ግለሰብ ከትግራይ ክልል ወጥቶ በአማራ ክልል በኩል ሊያመልጥ ሲል በደሴ ከተማ መያዙን ፅፈዋል።

የመረጃው ትክክለኝነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያረጋገጡት የሓወልቲ ክፍለ ከተማ ፓሲስ አዛዥ ሞገስ ወርቁ ፥ ተጠርጣሪው በዛሬው ቀን ጥቅምት  27/2017 ዓ.ም ለክልሉ ፓሊስ ተላለልፎ መሰጠቱን ገልፀዋል።

ግለሰቡ ደሴ ውስጥ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ ለፖሊስ ጥቆማ በመድረሱ ነው ሊያዝ የቻለው።

ከክልል ፖሊስ በተገኘው መረጃ ደግሞ ግለሰቡ በአላማጣ አድርጎ ነው ወደ ደሴ የተጓዘው። ወደዛ የሄደውም በረዳት ሹፌርነት ነው።

አንድ ለሊትም በደሴ ከተማ ካሳለፈ በኃላ ሰውነቱ ላይ ያለውን ንቅሳት የሚሸፍን ልብስ ገዝቶ ወደ ያዘው መኝታ ክፍል ሲገባ በደረሰ ጥቆማ ሊያዝ ችሏል። ከዛም መቐለ ፖሊስ አባላቱን በመላክ ተጠርጣሪው ወደ መቐለ እንዲመጣ አድርጓል።

የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እንዲሁም የደሴ ህዝብ ላደረገው ትብብር ምስጋና አቅርቧል።

በከባድ የግድያ ተግባር የተጠረጠረው ግለሰብ አስመልክቶ በማህበራዊ የትስስር ገፆች የተሰራጨው አጭር ቪድዮ እንደሚያመለክተው ፥ ተጠርጣሪው ፍቅረኛውን በጬቤ ከገደላት በኋላ ተፀፅቶ ራሱ ለመግደል ሞኩሮ ሳይሳካለት መቅረቱ በአንደበቱ ይገልፃል።

የሟች ወጣት ሓበን የማነ አባት አቶ የማነ ንጉስ ልጃቸው በጭካኔ በመግደል የተጠረጠረው ግለሰብ በአጭር ጊዜ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ለተባበሩ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

የፎቶ ባለቤት ፦ የትግራይ ፖሊስ ኮሚሽን

@tikvahethiopia 

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/91950

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Unlike Silicon Valley giants such as Facebook and Twitter, which run very public anti-disinformation programs, Brooking said: "Telegram is famously lax or absent in its content moderation policy." Either way, Durov says that he withdrew his resignation but that he was ousted from his company anyway. Subsequently, control of the company was reportedly handed to oligarchs Alisher Usmanov and Igor Sechin, both allegedly close associates of Russian leader Vladimir Putin. Recently, Durav wrote on his Telegram channel that users' right to privacy, in light of the war in Ukraine, is "sacred, now more than ever." Just days after Russia invaded Ukraine, Durov wrote that Telegram was "increasingly becoming a source of unverified information," and he worried about the app being used to "incite ethnic hatred." "This time we received the coordinates of enemy vehicles marked 'V' in Kyiv region," it added.
from id


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American