Notice: file_put_contents(): Write of 12575 bytes failed with errno=28 No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94826 -
Telegram Group & Telegram Channel
" በ7 ወራት ውስጥ ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት ተፈጽሟል " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ባለፉት 7 ወራት፣ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ሰርቆት ተፈጽሞበታል።

በአዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት ለአገልግሎት መቋረጥ ምክንያት መሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።


የአገልግሎቱ ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ታዬ ለዶቸቨለ ሬድዮ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

የተቋማቸው ተግባር፣ የኤሌክትሪክ ሀይልን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በጅምላ ገዝቶ ለደንበኞች ማቅረብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሆኖም፣ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሀይል መሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትልቅ ተግዳሮት እየፈጠረ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡

ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውም ጉዳት እንደዚሁ እየከፋ መምጣቱንም አመልክተዋል፡፡

በተያዘው የበጀት አመት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት መፈፀሙን አስታውቋል፡፡

በዋና ከተማ አዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በሀይል ማስተላለፊያ መስመሮች፣ በትራንስፎርመር እና በሀይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል።

እነዚህ በውጭ ምንዛሪ የሚገቡ ሀብቶች በመሆናቸው የሚያስከትለው ጉዳት ትልቅ ነው ብለዋል፡፡

የሰርቆት ድርጊቱ በአገልግሎት ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ እንዳለውም አመልክተዋል፡፡ 

"/በመሰረተልማቶች ላይ በሚደርሰው ጉዳት ምክንያት የሀይል አቅርቦት ሲቋረጥ፣ ተጎጅዎቹ ደንበኞች ብቻ አይደሉም ’ተቋሙም ከፍተኛ ጉዳት ያስተናግዳል " ያሉ ሲሆን " ይህ ድርጊት ከደንበኞች የምናገኘውን ገቢ ያሳጣናል፣ የወደሙትን መሰረተልማቶች መልሰን ለመጠገን የምናወጣው ወጪም ከፍተኛ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡

" የስርቆት ድርጊቱን ከመከላከል አኳያ፣ በአሁኑ ጊዜ መጠነኛ መሻሻል አለ " ያሉ ሲሆን ሆኖም አሳሳቢነቱ በመቀጠሉ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ይህን ችግር ለማስቆምና እነዚህን የሀገር ሀብቶች ከውድመት ለመታደግ ሊተባበሩ ይገባል ብለዋል።

 የኤለኤክትሪክ መሰረተልማቱ እየተሰረቀ ያለው ተቀባዮች ስላሉ ነው፣ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ‘ የሚሉት አቶ መላኩ፣ መንግስትም አጥፊዎችን ለህግ በማቅረቡ በኩል እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

#DW

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94826
Create:
Last Update:

" በ7 ወራት ውስጥ ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት ተፈጽሟል " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ባለፉት 7 ወራት፣ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ሰርቆት ተፈጽሞበታል።

በአዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት ለአገልግሎት መቋረጥ ምክንያት መሆኑ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።


የአገልግሎቱ ኮሚኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ታዬ ለዶቸቨለ ሬድዮ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

የተቋማቸው ተግባር፣ የኤሌክትሪክ ሀይልን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል በጅምላ ገዝቶ ለደንበኞች ማቅረብ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሆኖም፣ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሀይል መሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትልቅ ተግዳሮት እየፈጠረ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡

ችግሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ የሚያደርሰውም ጉዳት እንደዚሁ እየከፋ መምጣቱንም አመልክተዋል፡፡

በተያዘው የበጀት አመት ባለፉት ሰባት ወራት ብቻ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኃይል መሰረተ-ልማት ስርቆት መፈፀሙን አስታውቋል፡፡

በዋና ከተማ አዲስ አበባም ጭምር በጠራራ ፀሀይ፣ በመሰረተልማቶች ላይ የሚፈፀመው ስርቆት፣ በሀይል ማስተላለፊያ መስመሮች፣ በትራንስፎርመር እና በሀይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያያተኮረ መሆኑን ገልፀዋል።

እነዚህ በውጭ ምንዛሪ የሚገቡ ሀብቶች በመሆናቸው የሚያስከትለው ጉዳት ትልቅ ነው ብለዋል፡፡

የሰርቆት ድርጊቱ በአገልግሎት ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ እንዳለውም አመልክተዋል፡፡ 

"/በመሰረተልማቶች ላይ በሚደርሰው ጉዳት ምክንያት የሀይል አቅርቦት ሲቋረጥ፣ ተጎጅዎቹ ደንበኞች ብቻ አይደሉም ’ተቋሙም ከፍተኛ ጉዳት ያስተናግዳል " ያሉ ሲሆን " ይህ ድርጊት ከደንበኞች የምናገኘውን ገቢ ያሳጣናል፣ የወደሙትን መሰረተልማቶች መልሰን ለመጠገን የምናወጣው ወጪም ከፍተኛ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡

" የስርቆት ድርጊቱን ከመከላከል አኳያ፣ በአሁኑ ጊዜ መጠነኛ መሻሻል አለ " ያሉ ሲሆን ሆኖም አሳሳቢነቱ በመቀጠሉ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ይህን ችግር ለማስቆምና እነዚህን የሀገር ሀብቶች ከውድመት ለመታደግ ሊተባበሩ ይገባል ብለዋል።

 የኤለኤክትሪክ መሰረተልማቱ እየተሰረቀ ያለው ተቀባዮች ስላሉ ነው፣ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል ‘ የሚሉት አቶ መላኩ፣ መንግስትም አጥፊዎችን ለህግ በማቅረቡ በኩል እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

#DW

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94826

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The account, "War on Fakes," was created on February 24, the same day Russian President Vladimir Putin announced a "special military operation" and troops began invading Ukraine. The page is rife with disinformation, according to The Atlantic Council's Digital Forensic Research Lab, which studies digital extremism and published a report examining the channel. After fleeing Russia, the brothers founded Telegram as a way to communicate outside the Kremlin's orbit. They now run it from Dubai, and Pavel Durov says it has more than 500 million monthly active users. In February 2014, the Ukrainian people ousted pro-Russian president Viktor Yanukovych, prompting Russia to invade and annex the Crimean peninsula. By the start of April, Pavel Durov had given his notice, with TechCrunch saying at the time that the CEO had resisted pressure to suppress pages criticizing the Russian government. The Securities and Exchange Board of India (Sebi) had carried out a similar exercise in 2017 in a matter related to circulation of messages through WhatsApp. The last couple days have exemplified that uncertainty. On Thursday, news emerged that talks in Turkey between the Russia and Ukraine yielded no positive result. But on Friday, Reuters reported that Russian President Vladimir Putin said there had been some “positive shifts” in talks between the two sides.
from id


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American