Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray : በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት የራሱን ምክር ቤት አቋቁሟል። " የሃላቀርነት እና ወንጀል ቡድን " ሲል የገለፀውን በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን የህወሓት ቡድን በፅኑ ለመታገል ቆርጦ እንደተነሳ ገልጿል። በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት እስከ ቀጣዩ 14ኛው የደርጅቱ መደበኛ ጉባኤ የሚቆዩ ሊቀመንበር እና ምክትል ያቀፈ 7 አባላት ባሉት አስተባባሪ ኮሚቴ የሚመራ ም/ቤት…
#TPLF : ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል።

ምርጫ ቦርድ ፤ ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አስታውሷል።

ፖርቲው ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ እንደሚጠበቅም አመልክቷል።

ምንም እንኳን ፓርቲው በስድስት ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ የሚለውን ግዴታ ያለተጨማሪ ማሳሰቢያ መፈፀም እንዳለበት የሚታመን ቢሆንም ቦርዱ ለፓርቲው ነሀሴ 3 ፣ ነሀሴ 20 /2016 ዓ/ም እንዲሁም ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በፃፋቸው ደብዳቤዎች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማከናዎን ጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ማስታወቁን አመልክቷል።

" ፓርቲው በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በመሆኑ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ ይጠበቃል " ያለው ምርጫ ቦርድ " ለዚሁ የጠቅላላ ጉባኤ ዝግጅት የሚያስፈልገውን የቅድመ ጉባኤ ዝግጅት የተመለከቱ ስራዎችን ቦርዱ መከታተል እንዲችል ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ከማድረጉ 21 ቀናት በፊት ጉባኤው የሚደረግበትን ቀን ለቦርድ እንዲያሳውቅ ይጠበቃል " ብሏል።

ይሁንና እስከ ዛሬ ድረስ ፓርቲው ከተመዘገበ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚያስችለውን እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ቦርዱ እንደማያውቅ አመልክቷል።

ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚገባው ወቅት ሊገባደድ ከሁለት ወር ያነሰ ጊዜ የቀረው በመሆኑ ፖርቲው ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በቀረው አጭር ጊዜ የጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ቦርዱ በጥበቅ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም።

በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

ምንም እንኳን ምርጫ ቦርድ እውቅና እንደማይሰጥ ቢያሳውቅም በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ቡድን ጉባኤ አድርጎ አመራሮቹን መርጧል።

አቶ ጌታቸው ረዳን እና ሌሎች ከእሳቸው ጋር የነበሩ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮችን ከቦታቸውን አንስቷል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ቡድንም ለጉባኤው እውቅና የነፈገ ሲሆን ትክክለኛ ቅቡልነት ያለው ጉባኤ እንዲደረግ እየሰራ መሆኑን ማሳወቁ አይዘነጋም።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93283
Create:
Last Update:

#TPLF : ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል።

ምርጫ ቦርድ ፤ ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አስታውሷል።

ፖርቲው ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ እንደሚጠበቅም አመልክቷል።

ምንም እንኳን ፓርቲው በስድስት ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ የሚለውን ግዴታ ያለተጨማሪ ማሳሰቢያ መፈፀም እንዳለበት የሚታመን ቢሆንም ቦርዱ ለፓርቲው ነሀሴ 3 ፣ ነሀሴ 20 /2016 ዓ/ም እንዲሁም ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም በፃፋቸው ደብዳቤዎች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማከናዎን ጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ማስታወቁን አመልክቷል።

" ፓርቲው በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም በመሆኑ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ ይጠበቃል " ያለው ምርጫ ቦርድ " ለዚሁ የጠቅላላ ጉባኤ ዝግጅት የሚያስፈልገውን የቅድመ ጉባኤ ዝግጅት የተመለከቱ ስራዎችን ቦርዱ መከታተል እንዲችል ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ከማድረጉ 21 ቀናት በፊት ጉባኤው የሚደረግበትን ቀን ለቦርድ እንዲያሳውቅ ይጠበቃል " ብሏል።

ይሁንና እስከ ዛሬ ድረስ ፓርቲው ከተመዘገበ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚያስችለውን እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ቦርዱ እንደማያውቅ አመልክቷል።

ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ የሚገባው ወቅት ሊገባደድ ከሁለት ወር ያነሰ ጊዜ የቀረው በመሆኑ ፖርቲው ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በቀረው አጭር ጊዜ የጠቅላለ ጉባኤውን እንዲያደርግ ቦርዱ በጥበቅ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም።

በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

ምንም እንኳን ምርጫ ቦርድ እውቅና እንደማይሰጥ ቢያሳውቅም በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ቡድን ጉባኤ አድርጎ አመራሮቹን መርጧል።

አቶ ጌታቸው ረዳን እና ሌሎች ከእሳቸው ጋር የነበሩ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮችን ከቦታቸውን አንስቷል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ቡድንም ለጉባኤው እውቅና የነፈገ ሲሆን ትክክለኛ ቅቡልነት ያለው ጉባኤ እንዲደረግ እየሰራ መሆኑን ማሳወቁ አይዘነጋም።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93283

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In a message on his Telegram channel recently recounting the episode, Durov wrote: "I lost my company and my home, but would do it again – without hesitation." The SC urges the public to refer to the SC’s I nvestor Alert List before investing. The list contains details of unauthorised websites, investment products, companies and individuals. Members of the public who suspect that they have been approached by unauthorised firms or individuals offering schemes that promise unrealistic returns Given the pro-privacy stance of the platform, it’s taken as a given that it’ll be used for a number of reasons, not all of them good. And Telegram has been attached to a fair few scandals related to terrorism, sexual exploitation and crime. Back in 2015, Vox described Telegram as “ISIS’ app of choice,” saying that the platform’s real use is the ability to use channels to distribute material to large groups at once. Telegram has acted to remove public channels affiliated with terrorism, but Pavel Durov reiterated that he had no business snooping on private conversations. "The result is on this photo: fiery 'greetings' to the invaders," the Security Service of Ukraine wrote alongside a photo showing several military vehicles among plumes of black smoke. As such, the SC would like to remind investors to always exercise caution when evaluating investment opportunities, especially those promising unrealistically high returns with little or no risk. Investors should also never deposit money into someone’s personal bank account if instructed.
from in


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American