Telegram Group & Telegram Channel
“ ገዢው ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም ” - አዲሱ  የመኢአድ ተሿሚ ፕሬዜዳንት

መላው ኢትዮጵያ አንድነት ደርጅት (መኢአድ) በቅርቡ ፓርቲውን ለስድስት ዓመታት በመሩት አቶ ማሙሸት አማረ ምትክ አቶ አብርሃም ጌጡን ፕሬዜዳንት አድርጎ ሾሟል።

አንዲሱ የፓርቲው ፕሬዜዳንትም ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገዢውን ፓርቲ በብርቱ ተችተዋል።

" ጠባብ " የሚል ትችት የሚሰነዘርበት የኢትዮጵያ የፓለቲካ ምህዳርን ለመቋቋም ምን ያህል ተዘጋጅተዋል ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ተሿሚው ብርቱ ትችት ያነገበ ምላሽ ሰጥተዋል።

አዲሱ የመኢዓድ ተሿሚ ፕሬዚዳንት አቶ አብርሃም ጌጡ ምን አሉ ?

“ እንደ ተመራጭ መሪ በድንገት አይደለም የመጣሁት፡፡ ለ26 አካካቢ ዓመታት ፖልቲካሊ አክቲቭ ሆኘ ረጅም ትግል እያደረኩ ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር የመኢአድ አባላትም ከፍተኛውን ድምጽ ሰጥተውኛል፡፡

በኢትዮጵያ ፖለቲካ መጻዒው እጣ ፋንታችን ስናየው እውነት ለመናገር የአሁኑን ገዢ ፓርቲ ፓርቲ ነው ብለን ለመናገርም ይከብዳል፡፡ ገዢ ፓርቲ የሚባለው ሁሉንም እኩል የሚገዛ ነውና፡፡ መልቲ ፓርቲ ሲስተም የተገነባባቸው ዓለማት የሚመሩት በዴሞክራሲ ህግ ነው፡፡

የዴሞክራሲ ስርዓት የሚያድግ የነበረው ደግሞ በዚያች አገር በሚኖረው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ የኛ አገር የፖለቲካ ሂደትና ባህሪ ምን ነበር ? አሁንስ ምን እየሆንን ነው? ብለን ስናስብ ገዢ ፓርቲ አለ ማለት አይቻልም፡፡ 

ገዢ ፓርቲ የፖለቲካ ስፔሱ ነጻ ሆኖ የፓለቲካ አክተሮች ሜዳው ላይ ወርደው፣ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ ሰጥተው መራጩም ተመራጩም ተሳትፎ ወደ ስልጣን የሚመጣበት መሆን አለበት፡፡

የመረጠውንም ያልመረጠውንም እኩል ማስተዳደር፣ ኃላፊነቱን፣ ግዴታውን ሲወጣ ገዢ ፓርቲ ይባላል፡፡ ከዚህ አንፃር ገዢውን ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም፡፡ ፓርቲ በውስጡ ብዙ ነገሮችን መያዝ አለበት።

የፓለቲካ ፓርቲ ማለት የራሱ ፕሮግራም፣ ርዕዮተዓለም፣ አደረጃጀት ያለው ነው፡፡ አሁን ስልጣን ላይ ያለው የፖለቲካ ኃይል ፋንዳሜንታል የሆኑ ነገሮች በውስጡ የሉትም፡

ዝም ብሎ የተደራጀ፣ የሕዝብ፣ ብሶትና ትግል በአጋጣሚ አስፈንጥሮ ወስዶ ቤተ መንግስት ያስቀመጠው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ ህዝቡ ከነበረበት የለውጥ ፍላጎት ተነስቶ መርጦታል፡፡ 

ከተመረጠ በኋላ ግን አገሪቱ ወዴት እየሄደች ነው? ምንድን ነው የሆነችው? ሰርቫይዝ ማድረግ የምትችልብት መሰረታዊ አገራዊ ምሰሶዎች አሉ ወይ? ተብሎ ሲታሰብ በጣም አደጋ ነው፡፡ 

ድሮ ኢትዮጵያ መስቀልኛ ጥያቄ ገብታለች እንል ነበር። መስቀልኛ ጥያቄ የሚባለው በመስቀልኛ ቦታ ተቁሞ ግራ ቀኝ ሲታይ ነውና አሁን ግን መቆምም አይቻለም፡፡ መቆሚያ፣ መንቀሳቀሻ መሬት የለም።

የጸጥታና ሰላምን የሚያስከብር ኃይል በሌለበት ቀጣይ የአገሪቱ የፖለቲካ እጣፋንታ ምን ይሆናል? ለሚለው ጥያቄ ፈጣሪ እጁን ዘርግቶ ኢትዮጵያን ካልጠበቃት አሁን ባለው ተጨባጪ ሁኔታ ከባድ አደጋ ላይ ናት።

ይህን ብለን ግን በዝምታ ቁጭ እንልም፡፡ መኢዓድ ፓርቲ ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም በቀጣይ አሸናፊ ሆኖ ሊወጣ ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም የአንድንት ኃይሎች የሚባሉትን አሰብስብን የፖለቲካ ትግል ያደርጋል።

መንግስት የህዝብን ድምጽና ሰቆቃ አዳምጦ የፖለቲካ መፍትሄ ሊሰጥ ተቋቋመ ተቋም መሆን አለበትና አብሶሉት ሞናርኪዎች ሲያደርጉት እንደነበረው እንዲያደርግ አንፈቅድለትም፡፡ ለዚህም ብርቱ ትግል እናደርጋለን፡፡
 
ሰው ሚያሳድዱ፣ የሚያግቱ፣ በመሳሪያ የሚጨፈጭፉ አካላት ስልጣንን መከታ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ግን በየትኛውም መስኮት ሂደው መደበቅ አይችሉም፡፡ ይህን እንነግራቸዋለን። የፖለቲካ ጥበቡ ለህዝብ መፍትሄ መፈለግ ነውና እሱን እናሳያለን ” ብለዋል።


በቀጣዩ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ያላቸውን ዝግጅትና ፓለቲካዊ አስቻይ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ጠይቀናቸው በሰጡን ምላሽ፣ “ የመጀመሪያ ስራችን በምርጫና ሥራ ወደ ስልጣን መምጣት ነው ” ሲሉ መልሰዋል።

“ ይህን ለማድረግ ጠንክረን እንሰራለን። ህዝቡ በቲፎዞ ካርድ መብቱን ሰጥቶ እንደአሁኑ ቤቱ እንዲፈርስ፣ ህልውናውን እንዲያጣ አናደርግም። ኢትዮጵያ በከፍተኛ ችግር እንዳለች የሚጠባ ህጻን የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡ ይህንን አስተካክለን ጥሩ ተመራጮች ሆነን ለመቅረብ ዝግጅት እያደረግን ነው ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94387
Create:
Last Update:

“ ገዢው ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም ” - አዲሱ  የመኢአድ ተሿሚ ፕሬዜዳንት

መላው ኢትዮጵያ አንድነት ደርጅት (መኢአድ) በቅርቡ ፓርቲውን ለስድስት ዓመታት በመሩት አቶ ማሙሸት አማረ ምትክ አቶ አብርሃም ጌጡን ፕሬዜዳንት አድርጎ ሾሟል።

አንዲሱ የፓርቲው ፕሬዜዳንትም ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገዢውን ፓርቲ በብርቱ ተችተዋል።

" ጠባብ " የሚል ትችት የሚሰነዘርበት የኢትዮጵያ የፓለቲካ ምህዳርን ለመቋቋም ምን ያህል ተዘጋጅተዋል ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው ተሿሚው ብርቱ ትችት ያነገበ ምላሽ ሰጥተዋል።

አዲሱ የመኢዓድ ተሿሚ ፕሬዚዳንት አቶ አብርሃም ጌጡ ምን አሉ ?

“ እንደ ተመራጭ መሪ በድንገት አይደለም የመጣሁት፡፡ ለ26 አካካቢ ዓመታት ፖልቲካሊ አክቲቭ ሆኘ ረጅም ትግል እያደረኩ ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር የመኢአድ አባላትም ከፍተኛውን ድምጽ ሰጥተውኛል፡፡

በኢትዮጵያ ፖለቲካ መጻዒው እጣ ፋንታችን ስናየው እውነት ለመናገር የአሁኑን ገዢ ፓርቲ ፓርቲ ነው ብለን ለመናገርም ይከብዳል፡፡ ገዢ ፓርቲ የሚባለው ሁሉንም እኩል የሚገዛ ነውና፡፡ መልቲ ፓርቲ ሲስተም የተገነባባቸው ዓለማት የሚመሩት በዴሞክራሲ ህግ ነው፡፡

የዴሞክራሲ ስርዓት የሚያድግ የነበረው ደግሞ በዚያች አገር በሚኖረው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ የኛ አገር የፖለቲካ ሂደትና ባህሪ ምን ነበር ? አሁንስ ምን እየሆንን ነው? ብለን ስናስብ ገዢ ፓርቲ አለ ማለት አይቻልም፡፡ 

ገዢ ፓርቲ የፖለቲካ ስፔሱ ነጻ ሆኖ የፓለቲካ አክተሮች ሜዳው ላይ ወርደው፣ አማራጭ ሃሳባቸውን ለህዝብ ሰጥተው መራጩም ተመራጩም ተሳትፎ ወደ ስልጣን የሚመጣበት መሆን አለበት፡፡

የመረጠውንም ያልመረጠውንም እኩል ማስተዳደር፣ ኃላፊነቱን፣ ግዴታውን ሲወጣ ገዢ ፓርቲ ይባላል፡፡ ከዚህ አንፃር ገዢውን ብልጽግና እንደ ፓርቲም አንቆጥረውም፡፡ ፓርቲ በውስጡ ብዙ ነገሮችን መያዝ አለበት።

የፓለቲካ ፓርቲ ማለት የራሱ ፕሮግራም፣ ርዕዮተዓለም፣ አደረጃጀት ያለው ነው፡፡ አሁን ስልጣን ላይ ያለው የፖለቲካ ኃይል ፋንዳሜንታል የሆኑ ነገሮች በውስጡ የሉትም፡

ዝም ብሎ የተደራጀ፣ የሕዝብ፣ ብሶትና ትግል በአጋጣሚ አስፈንጥሮ ወስዶ ቤተ መንግስት ያስቀመጠው የፖለቲካ ኃይል ነው፡፡ ህዝቡ ከነበረበት የለውጥ ፍላጎት ተነስቶ መርጦታል፡፡ 

ከተመረጠ በኋላ ግን አገሪቱ ወዴት እየሄደች ነው? ምንድን ነው የሆነችው? ሰርቫይዝ ማድረግ የምትችልብት መሰረታዊ አገራዊ ምሰሶዎች አሉ ወይ? ተብሎ ሲታሰብ በጣም አደጋ ነው፡፡ 

ድሮ ኢትዮጵያ መስቀልኛ ጥያቄ ገብታለች እንል ነበር። መስቀልኛ ጥያቄ የሚባለው በመስቀልኛ ቦታ ተቁሞ ግራ ቀኝ ሲታይ ነውና አሁን ግን መቆምም አይቻለም፡፡ መቆሚያ፣ መንቀሳቀሻ መሬት የለም።

የጸጥታና ሰላምን የሚያስከብር ኃይል በሌለበት ቀጣይ የአገሪቱ የፖለቲካ እጣፋንታ ምን ይሆናል? ለሚለው ጥያቄ ፈጣሪ እጁን ዘርግቶ ኢትዮጵያን ካልጠበቃት አሁን ባለው ተጨባጪ ሁኔታ ከባድ አደጋ ላይ ናት።

ይህን ብለን ግን በዝምታ ቁጭ እንልም፡፡ መኢዓድ ፓርቲ ኢትዮጵያዊነትን በማስቀደም በቀጣይ አሸናፊ ሆኖ ሊወጣ ብቻ ሳይሆን ሌሎችንም የአንድንት ኃይሎች የሚባሉትን አሰብስብን የፖለቲካ ትግል ያደርጋል።

መንግስት የህዝብን ድምጽና ሰቆቃ አዳምጦ የፖለቲካ መፍትሄ ሊሰጥ ተቋቋመ ተቋም መሆን አለበትና አብሶሉት ሞናርኪዎች ሲያደርጉት እንደነበረው እንዲያደርግ አንፈቅድለትም፡፡ ለዚህም ብርቱ ትግል እናደርጋለን፡፡
 
ሰው ሚያሳድዱ፣ የሚያግቱ፣ በመሳሪያ የሚጨፈጭፉ አካላት ስልጣንን መከታ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ግን በየትኛውም መስኮት ሂደው መደበቅ አይችሉም፡፡ ይህን እንነግራቸዋለን። የፖለቲካ ጥበቡ ለህዝብ መፍትሄ መፈለግ ነውና እሱን እናሳያለን ” ብለዋል።


በቀጣዩ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ያላቸውን ዝግጅትና ፓለቲካዊ አስቻይ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ ጠይቀናቸው በሰጡን ምላሽ፣ “ የመጀመሪያ ስራችን በምርጫና ሥራ ወደ ስልጣን መምጣት ነው ” ሲሉ መልሰዋል።

“ ይህን ለማድረግ ጠንክረን እንሰራለን። ህዝቡ በቲፎዞ ካርድ መብቱን ሰጥቶ እንደአሁኑ ቤቱ እንዲፈርስ፣ ህልውናውን እንዲያጣ አናደርግም። ኢትዮጵያ በከፍተኛ ችግር እንዳለች የሚጠባ ህጻን የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡ ይህንን አስተካክለን ጥሩ ተመራጮች ሆነን ለመቅረብ ዝግጅት እያደረግን ነው ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94387

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In addition, Telegram's architecture limits the ability to slow the spread of false information: the lack of a central public feed, and the fact that comments are easily disabled in channels, reduce the space for public pushback. This provided opportunity to their linked entities to offload their shares at higher prices and make significant profits at the cost of unsuspecting retail investors. These administrators had built substantial positions in these scrips prior to the circulation of recommendations and offloaded their positions subsequent to rise in price of these scrips, making significant profits at the expense of unsuspecting investors, Sebi noted. The Russian invasion of Ukraine has been a driving force in markets for the past few weeks. On Telegram’s website, it says that Pavel Durov “supports Telegram financially and ideologically while Nikolai (Duvov)’s input is technological.” Currently, the Telegram team is based in Dubai, having moved around from Berlin, London and Singapore after departing Russia. Meanwhile, the company which owns Telegram is registered in the British Virgin Islands.
from in


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American