Telegram Group & Telegram Channel
. . . 'ጠናናነቱን' የሚያሳብቁ አይኖቹን እያየው

.....የኔ ፍቅር ታፈቅረኛለህ? እንዲያዘንብልኝ አንዴ የፀሐይዋን መጥለቅ ደግሞ ዘወር ብዬ ካፊያውን እየናፈቅኩ!

........እሱ ዝም... ጭጭ።

ቆይ!! ቃል ማውጣት ስራ ይሆናል? ለእሱማ ጥንብ የሆነበትን ሸክም የሚያራግፍበት ቀሊል የሚጠብቅ ነው የሚመስለው. ... በጣም ይከብደዋል።

....... እ? <የኔ ፍቅር ምን ያህል ታፈቅረኛለህ?> ለወጥ ሳደርግ ይመልስልኝ ይመስል...... የአጠያየቄ አይነት ሁልቆ መሳፍርት የለሁም። ...... ጥያቄ ጎጆዋን እንደቀለሰችብኝ መልስ ደሞ ደጅ ታስጠናኛለች።

.... ማሬ! እስኪ << አፈቅርሻለው >>በለኝ አልኩት እየተልመጠመጥኩ..... ምን አለ አፈንድቶት ቢገላግለኝ የጥያቄ መዝገበ ቃላቴ እኮ ታዘበኝ።

.....ለሽርደዳ ለሽርደዳማ ማንም አይችለውም። ..... ከንፋስ የፈጠነ፣ ከእስትንፋስ የቀረበ ነው። ............ 'በእግረ ደረቅነቴ' ላይ ሲያሽሞጥጥ የሚቀድመው የለም። ምን እሱ ብቻ መዘባበቻ ሲያደርገኝ የአለም ቃላት፣ ዓረፍተነገር፣ አንቀፅ ቀለበት ያሰሩለት ነው የሚመስሉት!!

... ''ለምን አይመልስልኝም?" ቃላት ማውጣት ይከብዳል? ያውም የሰለለ ድምፁን ከእሬት ስልቱ ጋር አዋህዶት ሊያቀርብልኝ

ግን! እኮ ያንን ቃል እወደዋለው እንደተፈታች እንቦሳ ያስፈነድቀኛል።

. . . ፈለግ የወረረውን ጣቱን ፈርሱ ላይ እያንሸራሸረ፣ አልፎ አልፎ እጆቹን ጉሹ በሸሸው አናቱ ላይ ችፍ ያለሁን ላቦቱን እየጠረገ፣ ልማደኛ ጥፍሩን ጭጉኝ በወረሰው ጢሙ ወጋ ወጋ እያደረገ፣ ....እንደ ማስቲካ አላምጦ ጣዕሙ ሲያልቅ ለሚተፋው ቃል ለምንስ እጨነቃለው?

. . . 'ስጋ' የሆነውን 'ቃል' እንኳን የገዛ ወገኖቹ አልተቀበሉትም። "ሰምና ወርቅ" ሲያወጡለት ስንክልክል ብለዋል። ...'የፍጥረትን ሩጫ' የሚያቃጥለው 'ዓረፍተ ነገር' በየጉራንጉሩ እንደ ጭቃ ይለጣጠፉበታል። <አንደበት ዓመፀኛ አለም ነው> ያሻው ፍቅርን ይገድልበታል። የገደለውን ይቀብርበታል። ታዲያ! ለዚ ቃል ነው ደጅ የሚያስጠናኝ? 'የህልም እንጀራ' አሳቅፎ የሚያንከራትተኝ!

.....'ያላበጀውን ፍቅር' በፊደሉ ቢራቀቅበት ምን አለ? ለእሱ ''ማርጃ'' ለእኔ ''የምስራች'' የሆነውን ቢነግረኝ ምን ቸግሮት?

.....<ሀሞቴ ፈሷል> ግን! የመጨረሻ ቃሌን አቀበልኩት

<<የእኔ ውድ በጣም አፈቅርሃለው!>> ጥያቄ አልነበረም። ምላሽም አይሻም!

. . . 'የበጨጨ' አልፎ አልፎ ጥጋ ጥጉን እንደ 'ዳመና' ጥቁር ያጠላበትን ጥርሱን ብልጭ አድርጎ እንደወትሮው በመሰሪ አይኖቹ 'ሴሰኛ' አስተያየቱን መርቆልኝ ..... የአምስት ወር ህፃን ይመስል እየዳኸ በሚንፏቀቁ ቃላቶች

<<አ..ላ...ፈ...ቅ...ርሽም>> አለኝ! ቦምቡን አፈነዳው። ስብርባሪው አልጎዳኝም። እንደሁም በተቃራኒው. . .

.... "ነፍሴ ሃሴት አደረገች". . . "ጮቤ ረገጥኩ". . . "ቦረቅኩ"!
<ውሃ እንደተጠማ ደርቆ መሰነጣጠቅ የጀመረው ተስፋዬ ረሰረሰልኝ> ... ቃሉ ለኔ ኃይል አለው። "ሳይፈቀሩ ማፍቀር ድሌ ነው"። "ምላሽ የሌለው መውደድ የሰባ ፍሪዳ ጮማዬ ነው" ።

አርያም ተስፋዬ (2013)



group-telegram.com/yabsiratesfaye/110
Create:
Last Update:

. . . 'ጠናናነቱን' የሚያሳብቁ አይኖቹን እያየው

.....የኔ ፍቅር ታፈቅረኛለህ? እንዲያዘንብልኝ አንዴ የፀሐይዋን መጥለቅ ደግሞ ዘወር ብዬ ካፊያውን እየናፈቅኩ!

........እሱ ዝም... ጭጭ።

ቆይ!! ቃል ማውጣት ስራ ይሆናል? ለእሱማ ጥንብ የሆነበትን ሸክም የሚያራግፍበት ቀሊል የሚጠብቅ ነው የሚመስለው. ... በጣም ይከብደዋል።

....... እ? <የኔ ፍቅር ምን ያህል ታፈቅረኛለህ?> ለወጥ ሳደርግ ይመልስልኝ ይመስል...... የአጠያየቄ አይነት ሁልቆ መሳፍርት የለሁም። ...... ጥያቄ ጎጆዋን እንደቀለሰችብኝ መልስ ደሞ ደጅ ታስጠናኛለች።

.... ማሬ! እስኪ << አፈቅርሻለው >>በለኝ አልኩት እየተልመጠመጥኩ..... ምን አለ አፈንድቶት ቢገላግለኝ የጥያቄ መዝገበ ቃላቴ እኮ ታዘበኝ።

.....ለሽርደዳ ለሽርደዳማ ማንም አይችለውም። ..... ከንፋስ የፈጠነ፣ ከእስትንፋስ የቀረበ ነው። ............ 'በእግረ ደረቅነቴ' ላይ ሲያሽሞጥጥ የሚቀድመው የለም። ምን እሱ ብቻ መዘባበቻ ሲያደርገኝ የአለም ቃላት፣ ዓረፍተነገር፣ አንቀፅ ቀለበት ያሰሩለት ነው የሚመስሉት!!

... ''ለምን አይመልስልኝም?" ቃላት ማውጣት ይከብዳል? ያውም የሰለለ ድምፁን ከእሬት ስልቱ ጋር አዋህዶት ሊያቀርብልኝ

ግን! እኮ ያንን ቃል እወደዋለው እንደተፈታች እንቦሳ ያስፈነድቀኛል።

. . . ፈለግ የወረረውን ጣቱን ፈርሱ ላይ እያንሸራሸረ፣ አልፎ አልፎ እጆቹን ጉሹ በሸሸው አናቱ ላይ ችፍ ያለሁን ላቦቱን እየጠረገ፣ ልማደኛ ጥፍሩን ጭጉኝ በወረሰው ጢሙ ወጋ ወጋ እያደረገ፣ ....እንደ ማስቲካ አላምጦ ጣዕሙ ሲያልቅ ለሚተፋው ቃል ለምንስ እጨነቃለው?

. . . 'ስጋ' የሆነውን 'ቃል' እንኳን የገዛ ወገኖቹ አልተቀበሉትም። "ሰምና ወርቅ" ሲያወጡለት ስንክልክል ብለዋል። ...'የፍጥረትን ሩጫ' የሚያቃጥለው 'ዓረፍተ ነገር' በየጉራንጉሩ እንደ ጭቃ ይለጣጠፉበታል። <አንደበት ዓመፀኛ አለም ነው> ያሻው ፍቅርን ይገድልበታል። የገደለውን ይቀብርበታል። ታዲያ! ለዚ ቃል ነው ደጅ የሚያስጠናኝ? 'የህልም እንጀራ' አሳቅፎ የሚያንከራትተኝ!

.....'ያላበጀውን ፍቅር' በፊደሉ ቢራቀቅበት ምን አለ? ለእሱ ''ማርጃ'' ለእኔ ''የምስራች'' የሆነውን ቢነግረኝ ምን ቸግሮት?

.....<ሀሞቴ ፈሷል> ግን! የመጨረሻ ቃሌን አቀበልኩት

<<የእኔ ውድ በጣም አፈቅርሃለው!>> ጥያቄ አልነበረም። ምላሽም አይሻም!

. . . 'የበጨጨ' አልፎ አልፎ ጥጋ ጥጉን እንደ 'ዳመና' ጥቁር ያጠላበትን ጥርሱን ብልጭ አድርጎ እንደወትሮው በመሰሪ አይኖቹ 'ሴሰኛ' አስተያየቱን መርቆልኝ ..... የአምስት ወር ህፃን ይመስል እየዳኸ በሚንፏቀቁ ቃላቶች

<<አ..ላ...ፈ...ቅ...ርሽም>> አለኝ! ቦምቡን አፈነዳው። ስብርባሪው አልጎዳኝም። እንደሁም በተቃራኒው. . .

.... "ነፍሴ ሃሴት አደረገች". . . "ጮቤ ረገጥኩ". . . "ቦረቅኩ"!
<ውሃ እንደተጠማ ደርቆ መሰነጣጠቅ የጀመረው ተስፋዬ ረሰረሰልኝ> ... ቃሉ ለኔ ኃይል አለው። "ሳይፈቀሩ ማፍቀር ድሌ ነው"። "ምላሽ የሌለው መውደድ የሰባ ፍሪዳ ጮማዬ ነው" ።

አርያም ተስፋዬ (2013)

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/110

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The SC urges the public to refer to the SC’s I nvestor Alert List before investing. The list contains details of unauthorised websites, investment products, companies and individuals. Members of the public who suspect that they have been approached by unauthorised firms or individuals offering schemes that promise unrealistic returns Official government accounts have also spread fake fact checks. An official Twitter account for the Russia diplomatic mission in Geneva shared a fake debunking video claiming without evidence that "Western and Ukrainian media are creating thousands of fake news on Russia every day." The video, which has amassed almost 30,000 views, offered a "how-to" spot misinformation. The fake Zelenskiy account reached 20,000 followers on Telegram before it was shut down, a remedial action that experts say is all too rare. Telegram has become more interventionist over time, and has steadily increased its efforts to shut down these accounts. But this has also meant that the company has also engaged with lawmakers more generally, although it maintains that it doesn’t do so willingly. For instance, in September 2021, Telegram reportedly blocked a chat bot in support of (Putin critic) Alexei Navalny during Russia’s most recent parliamentary elections. Pavel Durov was quoted at the time saying that the company was obliged to follow a “legitimate” law of the land. He added that as Apple and Google both follow the law, to violate it would give both platforms a reason to boot the messenger from its stores. Stocks dropped on Friday afternoon, as gains made earlier in the day on hopes for diplomatic progress between Russia and Ukraine turned to losses. Technology stocks were hit particularly hard by higher bond yields.
from in


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American