Telegram Group & Telegram Channel
​​አልወጣም ከቤቴ ቁ. ፪

ክፍል ፪(2)

ፈዲላም ተነስታ ወደ መኝታ ቤቷ ተመልሳ ገባች። ወዲያው ተኛች

ከምሽቱ 2፡00 ሲሆን የልጇን ደህንነት እንደ ምጥ ምትጠባበቅ እናት በድጋሚ መኝታ ቤቷን እያንኳኳች "ፈዲላ ተነሽ እራት ቀመስ አድርጊና ትተኛለሽ" ትል ጀመር። ፈዲላም ነቅታ ስለነበር "እሺ" አለቻት

ወደ ሻውር ቤት ገብታ ከተጣጠበች በኋላ ወደ ሳሎን ገባች

መሀመድ፡- ልጄ እንደምን አመሸሽ ነይ አጠገቤ

ፈዲላ፡- አባ አለሁ" እያለች አጠገቡ ቁጭ አለች

መሀመድ፡- ጥሩ ዜና አለኝ

ፈዲላ፡- ምንድን?

መሀመድ፡- ስራ አግኝቼልሻለሁ! ከአሁን በኋላ ራስን መጉዳት ቀን መተኛትና በድብርት መዋል የለም ስራ ትሰሪያለሽ አይምሮሽም ይመለሳል

ፈዲላ፡- እሺ" ከማለት ውጪ ሌላ ምንም አማራጭ አልነበራትም

ዘሀራም እራት አቀረበች ከወንድሞችና ከእህቶቿ ጋር እራቷን በላችና ተኛች። በነጋታውም መሀመድ ፈዲላን ቀሰቀሳትና "ዛሬ መስሪያ ቦታሽን አሳይሻለሁ ስራም ትጀምሪያለሽ ቶሎ ቶሎ ተዘጋጂ እንዳይረፍድብን" አላት።

ከተዘገጃጁም በኋላ አብረው ወደ ስራ ቦታ ሄዱ መሀመድም ስለ ፈዲላ በጣም ያስብ ነበርና ከድብርት እንድትወጣ የተለያዩ ሀሳቦችን በማንሳት ያዋራት ያወያያትም ነበር። በመጨረሻም ስለ ሀይማኖት አንድ ጥያቄ ጠየቃት

መሀመድ፡- ልጄ ግን ቁርአን አንብበሽ ታውቂያለሽ?

ፈዲላ፡- አዋ አባ ለምን አላነብም አነባለሁ

መሀመድ፡- እና በሀይማኖትሽ ትክክለኝነት እርግጠኛ ነሽ?

ፈዲላ፡- ይህን መመለስ ምችለው ሁሉም ሀይማኖቶች ውስጥ ያለውን ነገር መርምሬ ነው ስለዚህ አሁን የኢስላምን ትክክለኝነት በእርግጠኝነት አላቅም

መሀመድ፡- ወይ ልጄ እኔ አባትሽ ኡስታዝ ሆኜ አንቺ በኢስላም ሀይማኖት እርግጠኛ አይደለሁም ትያለሽ?
ስለ እስልምና መፅሀፉን አንብበሽ ተፍሲሩን ተረድተሽ ልትደርሺበት ትችያለሽ አንዲትም ስህተት የለውም! ነገር ግን ስለ ክርስትናና ስለ መፅሀፍ ቅዱስ ትክክል አለመሆን እኔ አባትሽ በደንብ አድርጌ አስተምርሻለሁ ኢንሻላህ።

በነገራችን ላይ ተወዳጆች ይህ ስልት ብዙዎች ወደ ክርስትናው አለም እንዳይመጡና ክርስትናና መፅሀፍ ቅዱስ ላይ የተለየ አመለካከት እንዲኖራቸው ከሚደረጉባቸው መነገዶች አንዱ ሲሆን የብዙ ሙስሊሞች ነፍስ መጥፋት ምክንያት ከሆኑት ዋነኛው ነው። ከኡስታዝ መፅሀፍ ቅዱስንንና ክርስትናን መማር"

ፈዲላ፡- እሺ አባ መልካም

መሀመድ፡- ጥሩ ልጄ ከዛን ኢስላም በፈጣሪ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሀይማኖት እንደሆነ ሌሎቹ በጠቅላላ ከንቱ እንደሆኑ ትረጃለሽ

ፈዲላ፡- እሺ

ብዙ ከተጓዙ በኋላ ስራ ቦታ ደረሱ ወደውስጥም ከገቡ በኋላ በአንድ ክርስቲያን ጓደኛው ጋር የምትሰራበትን ቦታ ምን እንደምትሰራና ምትገባበት የምትወጣበትን ሰአት በሙሉ እንዲያብራራላት አደረገ። ፈዲላም ስራውን ስትገምተው የምትወጣበትም የምትገባበትም ሰአት እንዲሁ ምቹ ስለሆነ በሀሳቡ ደስ ተሰኘች

ፍቃዱ(የመሀመድ ጓደኛ)፡- ዛሬዉኑ ስራሽን መጀመር ትችያለሽ እኔ ቀጥሎ ያለው ቢሮ ስለሆንኩ የፈለግሽውን ነገር ልትጠይቂኝ ትችያለሽ

ፈዲላ፡- እሺ አመሰግናለሁ " አለችና ወደ ተጠቆመችበት ቢሮ ገባች አራት ሴቶችም ነበሩ። ሰላምታም ከተቀባበሉ በኋላ የተዘጋጀላት ቦታ ላይ ተቀመጠች።

ማህተምን በመምታት ሌሎች ስሮችንም በመሰራራት እንዲሁ እስከ 10 ሰአት ድረስ ቆየች በዛን ቀን ስራው ትንሽ አይምሮዋን ጠምዶት ስለነበር ስለ ሳሙኤል ብዙ አላሰበችም ነበር።

የሚወጡበት ሰአት በደረሰ ጊዜ ወደ ኋላ ቀረት ያለችውን ሰራተኛዋን ልትግባባት ፈልጋ ነበርና

ፈዲላ፡- ይቅርታ ሁሌ በዚህ ሰአት ነው የምንወጣው?

ኤልሳቤጥ ፡- አዎን እህት በዚህ ሰአት ነው ሁሌ የምንወጣው

ፈዲላ፡- መልካም እንተዋወቅ ፈዲላ እባላለሁ ፈዱ በይኝ ክክክክ

ኤልሳቤጥ ፡- ክክክክ እሺ ፈዱ እኔ ደግሞ ኤልሳቤጥ እባላለሁ

ፈዲላ፡- መልካም ስለተዋወቅኩሽ ደስ ብሎኛል

ኤልሳቤጥ፡- እኔም

ፈዲላ፡- እሺ ንገሪኝ ምን አይነት ሰው ነሽ ምን ትወጃለሽ ምን ትጠያለሽ" እያወሩና እየተግባቡ ወደ ታክሲ መያዣ ደረሱ። ፈዲላም መኪና አልያዘችም ነበርና ታክሲ የግድ መሳፈር ነበረባት።

ከተለያዩም በኋላ ፈዲላ ወደ ቤቷ እንደገባች እጅጉን ተደሰተች ቀኑን መልካም ና ጥሩ በሆነ ሁኔታ ስላሳለፈች እንዲሁም አንዲስ ጓደኛ ስለተዋወቀች ስሜቷ አሪፍ ነበር።

ይህንን ሁኔታ የተመለከተችው የፈዲላ እናት ዘሀራ እጅጉን ደስ አላት ልጄ ተመለሰችልኝ በማለት ፈጠረኝ ብላ ምታስበውን አካለ እጅጉን አመሰገነች። መሀመድም ተጨንቆ ነበርና ይህንን ሁኔታ ሲያይ ይህንኑ አደረገ ።

መሀመድ፡- ፈዲላ ደክሞሻል እንዴ

ፈዲላ፡- አይ አባ ምነው

መሀመድ፡- ስለ ጠዋቱ ውይይት ከዛሬ እንድንጀምር ብዬ ነው ሀይማኖታዊ ጥናት

ፈዲላ፡- አይ አልደከመኝም እሺ ተታጥቤ መጣሁ

መሀመድ፡- እሺ የኔ ልጅ "አለና ወደ ሳሎን ተመልሶ መፅሀፍቶቹን ማዘገጃጀት ጀመረ። እንደጨረሰችም ወደ ሳሎን ዘለቀች መሀመድም "መጣሽ ልጄ ቁጭ በይ" አላት ቁጭም አለች።


መሀመድ፡- እንግዲህ አሁን የምታያቸው መፅሀፍት ባይብልና ቅዱስ ቁርአን ናቸው ሁለቱም የአላህ ቃል ናቸው ነገር ግን ባይብል በአይሁድና በክርስቲያኖች ስለተበረዘ የምንቀበለው ነገር በጣም ትንሹን ነው።

ፈዲላ፡- እሺ አባ ለምን ተበረዘ

መሀመድ፡- እነሱ የሚፈልጉትንና ከኑሯቸው ጋር ሊስማማ ሚችለውን ነገር መጨመር ስለኖረባቸው ነው።

ፈዲላ፡- እሺ

ይቀጥላል...........
@THESECRETKNOWITFIRST



group-telegram.com/THESECRETKNOWITFIRST/324
Create:
Last Update:

​​አልወጣም ከቤቴ ቁ. ፪

ክፍል ፪(2)

ፈዲላም ተነስታ ወደ መኝታ ቤቷ ተመልሳ ገባች። ወዲያው ተኛች

ከምሽቱ 2፡00 ሲሆን የልጇን ደህንነት እንደ ምጥ ምትጠባበቅ እናት በድጋሚ መኝታ ቤቷን እያንኳኳች "ፈዲላ ተነሽ እራት ቀመስ አድርጊና ትተኛለሽ" ትል ጀመር። ፈዲላም ነቅታ ስለነበር "እሺ" አለቻት

ወደ ሻውር ቤት ገብታ ከተጣጠበች በኋላ ወደ ሳሎን ገባች

መሀመድ፡- ልጄ እንደምን አመሸሽ ነይ አጠገቤ

ፈዲላ፡- አባ አለሁ" እያለች አጠገቡ ቁጭ አለች

መሀመድ፡- ጥሩ ዜና አለኝ

ፈዲላ፡- ምንድን?

መሀመድ፡- ስራ አግኝቼልሻለሁ! ከአሁን በኋላ ራስን መጉዳት ቀን መተኛትና በድብርት መዋል የለም ስራ ትሰሪያለሽ አይምሮሽም ይመለሳል

ፈዲላ፡- እሺ" ከማለት ውጪ ሌላ ምንም አማራጭ አልነበራትም

ዘሀራም እራት አቀረበች ከወንድሞችና ከእህቶቿ ጋር እራቷን በላችና ተኛች። በነጋታውም መሀመድ ፈዲላን ቀሰቀሳትና "ዛሬ መስሪያ ቦታሽን አሳይሻለሁ ስራም ትጀምሪያለሽ ቶሎ ቶሎ ተዘጋጂ እንዳይረፍድብን" አላት።

ከተዘገጃጁም በኋላ አብረው ወደ ስራ ቦታ ሄዱ መሀመድም ስለ ፈዲላ በጣም ያስብ ነበርና ከድብርት እንድትወጣ የተለያዩ ሀሳቦችን በማንሳት ያዋራት ያወያያትም ነበር። በመጨረሻም ስለ ሀይማኖት አንድ ጥያቄ ጠየቃት

መሀመድ፡- ልጄ ግን ቁርአን አንብበሽ ታውቂያለሽ?

ፈዲላ፡- አዋ አባ ለምን አላነብም አነባለሁ

መሀመድ፡- እና በሀይማኖትሽ ትክክለኝነት እርግጠኛ ነሽ?

ፈዲላ፡- ይህን መመለስ ምችለው ሁሉም ሀይማኖቶች ውስጥ ያለውን ነገር መርምሬ ነው ስለዚህ አሁን የኢስላምን ትክክለኝነት በእርግጠኝነት አላቅም

መሀመድ፡- ወይ ልጄ እኔ አባትሽ ኡስታዝ ሆኜ አንቺ በኢስላም ሀይማኖት እርግጠኛ አይደለሁም ትያለሽ?
ስለ እስልምና መፅሀፉን አንብበሽ ተፍሲሩን ተረድተሽ ልትደርሺበት ትችያለሽ አንዲትም ስህተት የለውም! ነገር ግን ስለ ክርስትናና ስለ መፅሀፍ ቅዱስ ትክክል አለመሆን እኔ አባትሽ በደንብ አድርጌ አስተምርሻለሁ ኢንሻላህ።

በነገራችን ላይ ተወዳጆች ይህ ስልት ብዙዎች ወደ ክርስትናው አለም እንዳይመጡና ክርስትናና መፅሀፍ ቅዱስ ላይ የተለየ አመለካከት እንዲኖራቸው ከሚደረጉባቸው መነገዶች አንዱ ሲሆን የብዙ ሙስሊሞች ነፍስ መጥፋት ምክንያት ከሆኑት ዋነኛው ነው። ከኡስታዝ መፅሀፍ ቅዱስንንና ክርስትናን መማር"

ፈዲላ፡- እሺ አባ መልካም

መሀመድ፡- ጥሩ ልጄ ከዛን ኢስላም በፈጣሪ ዘንድ ተቀባይነት ያለው ሀይማኖት እንደሆነ ሌሎቹ በጠቅላላ ከንቱ እንደሆኑ ትረጃለሽ

ፈዲላ፡- እሺ

ብዙ ከተጓዙ በኋላ ስራ ቦታ ደረሱ ወደውስጥም ከገቡ በኋላ በአንድ ክርስቲያን ጓደኛው ጋር የምትሰራበትን ቦታ ምን እንደምትሰራና ምትገባበት የምትወጣበትን ሰአት በሙሉ እንዲያብራራላት አደረገ። ፈዲላም ስራውን ስትገምተው የምትወጣበትም የምትገባበትም ሰአት እንዲሁ ምቹ ስለሆነ በሀሳቡ ደስ ተሰኘች

ፍቃዱ(የመሀመድ ጓደኛ)፡- ዛሬዉኑ ስራሽን መጀመር ትችያለሽ እኔ ቀጥሎ ያለው ቢሮ ስለሆንኩ የፈለግሽውን ነገር ልትጠይቂኝ ትችያለሽ

ፈዲላ፡- እሺ አመሰግናለሁ " አለችና ወደ ተጠቆመችበት ቢሮ ገባች አራት ሴቶችም ነበሩ። ሰላምታም ከተቀባበሉ በኋላ የተዘጋጀላት ቦታ ላይ ተቀመጠች።

ማህተምን በመምታት ሌሎች ስሮችንም በመሰራራት እንዲሁ እስከ 10 ሰአት ድረስ ቆየች በዛን ቀን ስራው ትንሽ አይምሮዋን ጠምዶት ስለነበር ስለ ሳሙኤል ብዙ አላሰበችም ነበር።

የሚወጡበት ሰአት በደረሰ ጊዜ ወደ ኋላ ቀረት ያለችውን ሰራተኛዋን ልትግባባት ፈልጋ ነበርና

ፈዲላ፡- ይቅርታ ሁሌ በዚህ ሰአት ነው የምንወጣው?

ኤልሳቤጥ ፡- አዎን እህት በዚህ ሰአት ነው ሁሌ የምንወጣው

ፈዲላ፡- መልካም እንተዋወቅ ፈዲላ እባላለሁ ፈዱ በይኝ ክክክክ

ኤልሳቤጥ ፡- ክክክክ እሺ ፈዱ እኔ ደግሞ ኤልሳቤጥ እባላለሁ

ፈዲላ፡- መልካም ስለተዋወቅኩሽ ደስ ብሎኛል

ኤልሳቤጥ፡- እኔም

ፈዲላ፡- እሺ ንገሪኝ ምን አይነት ሰው ነሽ ምን ትወጃለሽ ምን ትጠያለሽ" እያወሩና እየተግባቡ ወደ ታክሲ መያዣ ደረሱ። ፈዲላም መኪና አልያዘችም ነበርና ታክሲ የግድ መሳፈር ነበረባት።

ከተለያዩም በኋላ ፈዲላ ወደ ቤቷ እንደገባች እጅጉን ተደሰተች ቀኑን መልካም ና ጥሩ በሆነ ሁኔታ ስላሳለፈች እንዲሁም አንዲስ ጓደኛ ስለተዋወቀች ስሜቷ አሪፍ ነበር።

ይህንን ሁኔታ የተመለከተችው የፈዲላ እናት ዘሀራ እጅጉን ደስ አላት ልጄ ተመለሰችልኝ በማለት ፈጠረኝ ብላ ምታስበውን አካለ እጅጉን አመሰገነች። መሀመድም ተጨንቆ ነበርና ይህንን ሁኔታ ሲያይ ይህንኑ አደረገ ።

መሀመድ፡- ፈዲላ ደክሞሻል እንዴ

ፈዲላ፡- አይ አባ ምነው

መሀመድ፡- ስለ ጠዋቱ ውይይት ከዛሬ እንድንጀምር ብዬ ነው ሀይማኖታዊ ጥናት

ፈዲላ፡- አይ አልደከመኝም እሺ ተታጥቤ መጣሁ

መሀመድ፡- እሺ የኔ ልጅ "አለና ወደ ሳሎን ተመልሶ መፅሀፍቶቹን ማዘገጃጀት ጀመረ። እንደጨረሰችም ወደ ሳሎን ዘለቀች መሀመድም "መጣሽ ልጄ ቁጭ በይ" አላት ቁጭም አለች።


መሀመድ፡- እንግዲህ አሁን የምታያቸው መፅሀፍት ባይብልና ቅዱስ ቁርአን ናቸው ሁለቱም የአላህ ቃል ናቸው ነገር ግን ባይብል በአይሁድና በክርስቲያኖች ስለተበረዘ የምንቀበለው ነገር በጣም ትንሹን ነው።

ፈዲላ፡- እሺ አባ ለምን ተበረዘ

መሀመድ፡- እነሱ የሚፈልጉትንና ከኑሯቸው ጋር ሊስማማ ሚችለውን ነገር መጨመር ስለኖረባቸው ነው።

ፈዲላ፡- እሺ

ይቀጥላል...........
@THESECRETKNOWITFIRST

BY THE SECRET KNOW IT FIRST


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/THESECRETKNOWITFIRST/324

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In view of this, the regulator has cautioned investors not to rely on such investment tips / advice received through social media platforms. It has also said investors should exercise utmost caution while taking investment decisions while dealing in the securities market. Investors took profits on Friday while they could ahead of the weekend, explained Tom Essaye, founder of Sevens Report Research. Saturday and Sunday could easily bring unfortunate news on the war front—and traders would rather be able to sell any recent winnings at Friday’s earlier prices than wait for a potentially lower price at Monday’s open. "This time we received the coordinates of enemy vehicles marked 'V' in Kyiv region," it added. Now safely in France with his spouse and three of his children, Kliuchnikov scrolls through Telegram to learn about the devastation happening in his home country. During the operations, Sebi officials seized various records and documents, including 34 mobile phones, six laptops, four desktops, four tablets, two hard drive disks and one pen drive from the custody of these persons.
from it


Telegram THE SECRET KNOW IT FIRST
FROM American