Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94163-94164-94164-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94163 -
Telegram Group & Telegram Channel
🔈#የአርሶአደሮችድምጽ

🔴 “ አምና 3,600 ብር ስንገዛው የነበረውን ማዳበሪያ ዘንድሮ በ8,400 ብር ለመዛት ተገደናል ” - አርሶ አደሮች

➡️ “ ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል ” - የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ

የሲዳማ ክልል አርሶ አደሮች ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በቆሎ የቀረበላቸው በውድ ዋጋ በመሆኑ ለመግዛት መቸገራቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ አምና የአንድ ኩንታል ማዳበሪያ (ዳፕ) ዋጋ 3,600 ብር ነበር። ዘንድሮ ግን 8,400 ገብቷል። አምና 1,800 ብር የነበረው ምርጥ ዘር በቆሎ የአንድ ፕሎት ዋጋ ዘንድሮ 4,600 ብር ገብቷል። ይህ ለበቆሎ ብቻ የሚከፈል ነው።

በቆሎ ስንወስድ ለብልጽግና ቤት ግንባታ 1,500 ብር፣ ለማኀተም 1,000 ብር፣ ለግብር እስከ 3,000 ብር፣ ለብልጽግና ፓርቲ መዋጮ 300፣ ለቀይ መስቀል 200 ብር ወረዳው በግዴታ የሚያስከፍለን ወጪዎችም አሉ።

በአጠቃላይ ለአንድ ፕሎት ምርጥ ዘር በቆሎ አንድ አርሶ አደር ከ10,000 ሺሕ ብር በላይ እንዲያወጣ ተገዷል።

ስለዚህ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለይ በቆሎን በስፋት በማምረት የሚትታወቀው የሻመና አርሶ አደሮች ዘንድሮ በቆሎ ማምረት ይቸገራሉ"
ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ አርሶ አደሮች ላቀረቡት ቅሬታ ምላሽ እንዲድሰጥ የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮን ጠይቋል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ ምን መለሱ ?

“ ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል። እኛ የጨመርነው ነገር የለም የትራንስፓርት ብቻ ነው። ስለዚህ ያለ ዋጋ ነው፤ ያሳወቅነው ዋጋ።

ሌሎች ጋ አሁን ላይ ስርጭት ስላልጀመረ እንጅ ተመሳሳይ ነው። እነርሱ ቀድመው ስለሚገቡ በሚል እንጅ ፎርማሊ አሳውቀናል እኛ በደብዳቤ። አገራዊ ነው።

አምና ላይ ወደ 4,000 ገደማ ነበር። አሁን ላይ ከ7,500 - 8,000 ብር ይሄዳል እስከ ትራንስፓርት ታሳቢ ተድርጎ
ማለት ነው።

የበቆሎም አዎ በመሳሳይ ነው ይጨምራል። ፕሮዳክሽን ኮስት በየጊዜው ይጨምራል። ባለበት አይሆንም

ስለዚህ ለምሳሌ የአንድ ትራክተር ዋጋ፣ የነዳጅ ዋጋ ታሳቢ አድርጎ በየአመቱ ይጨምራል። መጨመር ያለ ነው። ከሌላ ጋ ካልሆነ በስተቀር ከኛ ጋ ኦፊሻሊ ታይቶ ዋጋ እንደ ሀገር ወጥቶለት በዚያ የምናቀርበው ስለሆነ ችግር ያለው አይደለም።

ለምሳሌ በትራክተር ለሚያርስ ነዳጅ፣ የጉልበት.. ካችአምናና አምና የነበረ ተመሳሳይ አይደለም። ያምና እና የዚህ ዓመት ተመሳሳይ አይሆንም። በዚያ ምክንያት የተወሰኑ መጨመሮች አሉ።

ማዳበሪያ ከአገር ውጪ የሚመጣ ስለሆነ እኛ መተመን አልችልም። መንግስት ሳብሲድ አድርጓል። እንደመንግስት እንዲያውም ከድጎማ በፊት 12 ሺህ ብር ነው የሚሆነው የአንድ ኩንታል ማዳበሪያ ዋጋ። 

በድጎማው ቀንሶ ነው ወደዛም የወረደው። 4,000 ከአንድ ኩንታል ድጎማ ነው ”
ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM



group-telegram.com/tikvahethiopia/94163
Create:
Last Update:

🔈#የአርሶአደሮችድምጽ

🔴 “ አምና 3,600 ብር ስንገዛው የነበረውን ማዳበሪያ ዘንድሮ በ8,400 ብር ለመዛት ተገደናል ” - አርሶ አደሮች

➡️ “ ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል ” - የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ

የሲዳማ ክልል አርሶ አደሮች ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በቆሎ የቀረበላቸው በውድ ዋጋ በመሆኑ ለመግዛት መቸገራቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ አምና የአንድ ኩንታል ማዳበሪያ (ዳፕ) ዋጋ 3,600 ብር ነበር። ዘንድሮ ግን 8,400 ገብቷል። አምና 1,800 ብር የነበረው ምርጥ ዘር በቆሎ የአንድ ፕሎት ዋጋ ዘንድሮ 4,600 ብር ገብቷል። ይህ ለበቆሎ ብቻ የሚከፈል ነው።

በቆሎ ስንወስድ ለብልጽግና ቤት ግንባታ 1,500 ብር፣ ለማኀተም 1,000 ብር፣ ለግብር እስከ 3,000 ብር፣ ለብልጽግና ፓርቲ መዋጮ 300፣ ለቀይ መስቀል 200 ብር ወረዳው በግዴታ የሚያስከፍለን ወጪዎችም አሉ።

በአጠቃላይ ለአንድ ፕሎት ምርጥ ዘር በቆሎ አንድ አርሶ አደር ከ10,000 ሺሕ ብር በላይ እንዲያወጣ ተገዷል።

ስለዚህ የሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ በተለይ በቆሎን በስፋት በማምረት የሚትታወቀው የሻመና አርሶ አደሮች ዘንድሮ በቆሎ ማምረት ይቸገራሉ"
ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ አርሶ አደሮች ላቀረቡት ቅሬታ ምላሽ እንዲድሰጥ የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮን ጠይቋል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ ምን መለሱ ?

“ ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል። እኛ የጨመርነው ነገር የለም የትራንስፓርት ብቻ ነው። ስለዚህ ያለ ዋጋ ነው፤ ያሳወቅነው ዋጋ።

ሌሎች ጋ አሁን ላይ ስርጭት ስላልጀመረ እንጅ ተመሳሳይ ነው። እነርሱ ቀድመው ስለሚገቡ በሚል እንጅ ፎርማሊ አሳውቀናል እኛ በደብዳቤ። አገራዊ ነው።

አምና ላይ ወደ 4,000 ገደማ ነበር። አሁን ላይ ከ7,500 - 8,000 ብር ይሄዳል እስከ ትራንስፓርት ታሳቢ ተድርጎ
ማለት ነው።

የበቆሎም አዎ በመሳሳይ ነው ይጨምራል። ፕሮዳክሽን ኮስት በየጊዜው ይጨምራል። ባለበት አይሆንም

ስለዚህ ለምሳሌ የአንድ ትራክተር ዋጋ፣ የነዳጅ ዋጋ ታሳቢ አድርጎ በየአመቱ ይጨምራል። መጨመር ያለ ነው። ከሌላ ጋ ካልሆነ በስተቀር ከኛ ጋ ኦፊሻሊ ታይቶ ዋጋ እንደ ሀገር ወጥቶለት በዚያ የምናቀርበው ስለሆነ ችግር ያለው አይደለም።

ለምሳሌ በትራክተር ለሚያርስ ነዳጅ፣ የጉልበት.. ካችአምናና አምና የነበረ ተመሳሳይ አይደለም። ያምና እና የዚህ ዓመት ተመሳሳይ አይሆንም። በዚያ ምክንያት የተወሰኑ መጨመሮች አሉ።

ማዳበሪያ ከአገር ውጪ የሚመጣ ስለሆነ እኛ መተመን አልችልም። መንግስት ሳብሲድ አድርጓል። እንደመንግስት እንዲያውም ከድጎማ በፊት 12 ሺህ ብር ነው የሚሆነው የአንድ ኩንታል ማዳበሪያ ዋጋ። 

በድጎማው ቀንሶ ነው ወደዛም የወረደው። 4,000 ከአንድ ኩንታል ድጎማ ነው ”
ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94163

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In the past, it was noticed that through bulk SMSes, investors were induced to invest in or purchase the stocks of certain listed companies. Also in the latest update is the ability for users to create a unique @username from the Settings page, providing others with an easy way to contact them via Search or their t.me/username link without sharing their phone number. Markets continued to grapple with the economic and corporate earnings implications relating to the Russia-Ukraine conflict. “We have a ton of uncertainty right now,” said Stephanie Link, chief investment strategist and portfolio manager at Hightower Advisors. “We’re dealing with a war, we’re dealing with inflation. We don’t know what it means to earnings.” Sebi said data, emails and other documents are being retrieved from the seized devices and detailed investigation is in progress. Telegram boasts 500 million users, who share information individually and in groups in relative security. But Telegram's use as a one-way broadcast channel — which followers can join but not reply to — means content from inauthentic accounts can easily reach large, captive and eager audiences.
from it


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American