Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ዘጠኝ
ደብዳቤውን አንብባ እንደጨረሰች ራሷን ጉልበቶቿ መሀል ወሸቀቻቸው። ለምን ይሄን ሁሉ መስዋዕትነት? ለምን ይህን ያህል ለአንዲት ሴት ራስን አሳልፎ መስጠት? በምላሹ ታፍቅረው አታፍቅረው ሳያውቅ ለምን ራሱን ለእሷ ሰጠ? በህይወት ቢኖርና ይህንን ጥያቄዋን ቢመልስላት በወደደች ነበር ግን እዮብ አይመለስ አሸልቧል።

ተሳሳትክ እዮብ ብትነግረኝ ይሻል ነበር። ከጭንቅላቴ የማይሻር ጠባሳ ተውክብኝ! መቼም ከፊቴ የተዘረረውን ያንተን አካል መዘንጋት አልችልም ፣ከአእምሮዬ ሊጠፋ አይችልም። እዮብ ስህተት ሰርተኻል አዎ በጣም ተሳስተሃል! እጇ ላከ የነበረውን ወረቀት ጨመደደችው። ምን ልታስብ እንደሚገባት ማወቅ አልቻለችም። ብቻ ልትከፍለው የማትችለው የእዮብ ውለታ አለባት።

አፈቅረው ነበር? እራሷን ጠየቀች ልቧ የአዎንታም የአሉታም ምላሽ አልሰጣትም። ለረጅም ሰአት አነባች። አልአዛር ለማባበል አልሞከረም። ምክንያቱም የእሱም እምባ እየፈሰሰ ነበር። አንድ ብቸኛ ወንድሙን እንዳጣ ገብቶታል። በጀግንነት የሞተው የወንድሙ ወኔና ድፍረት ታወሰው። ለእዚች ከፊት ለፊቱ ለተቀመጠችው ሴት የነበረው የፍቅር ጥንካሬ የተለየ ነበር። ምን ያደርጋል? በህይወት ሳለ መፈቀሯን ሳታውቅ ከሞተ በኅላ ለፍቅሯ የከፈለውን መስዋዕትነት የተረዳችው ወጣት ላታገግም ቆስላለች። በምንም መንገድ ሊያፅናናት አይችልም።

ማን ያውቃል? ጊዜ የሚያመጣው አይታወቅም አለ ለራሱ እዮብን ልትዘነጋ የምትችልበት መንገድ ይኖራል።  በተቻለው መጠን ሀዘኗን ልትረሳ የምትችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በሙሉ አቅሙ ቆርጧል። ከመንግስትም የደንነት አባላት ጋር በነበረው የጠበቀ ግንኙነት አንድ የውሸት መታወቂያ ሊያገኝላት ችሏል። የእሷን መምጣት ቀደም ብሎ እየጠበቀች ስለነበር ሁሉንም ነገር አስቀድሞ ዝግጁ አድርጓል።

መታወቂያውን ከኪሱ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠው። 'መአዛ አሸናፊ' ይላል። ምንድን ነው በሚል ሁኔታ ተመለከተችው። አዲሱ ስምሽ ነው ትንሽ ራስሽን መቀየር ይኖርብሻል አለና ትርምስምሱ የወጣውን ረጅም ፀጉሯን አየ። መቆረጥ ሳይኖርበት አይቀርም። በተወሰነ መልኩ የፊትሽን ገፅታ ሊቀይረው ይችላል። ግን ይህን የመሰለ ፀጉር ተቆርጦ ሲወድግ ያሳዝናል ሲል አሰበ።

ብሌን አላመነታችም። በህይወት መኖር እስካለባት ድረስ ራሷን መለወጧ የግድ ነው። ሻወር መውሰድ ፈልጋለች። አልአዛር ጭንቅላቷን ያነበበ ይመስል መታጠብ ከፈለግሽ ሻወር ቤቱን ላሳይሽ እችላለሁ።  ፀጉርሽን የምትቆርጪበት መቀስ በስተቀኝ ባለው ኮመዲኖ ላይ ይገኛል። አላት ጊዜ ሳታጠፋ ልብሷን አወላልቃ ውሀው ውስጥ ተነከረች። ውሀው እንደውጪው ቆሻሻዋ ልቧ ውስጥም ያለውን ሸክም መውሰድ ቢችል ምንኛ በተደሰተች ነበር። ዐይኗን ጨፍና ከላይ የሚወርደውን ውሀ ከጭንቅላቷ ጀምሮ ታች እስኪደርስ ድረስ ታዳምጠዋለች። ከውሀው አንድ መፍትሔ ታገኝ ይመስል አሁንም አሁንም ትነከራለች። ሰውነቷ ቢፀዳም መውጣቱን ጠላችው። በጣም ከምትወዳት  ምስኪን እናቷ ጋር እንደማትገናኝ ተረድታለች። ይሄኔ እማዬ ሞቴን ሰምታ ሀዘን ተቀምጣ ይሆናል ስትል አሰበች። በራ ሄዳ አይዞሽ በህይወት አለውልሽ ልትላት ተመኘች።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/124
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ዘጠኝ
ደብዳቤውን አንብባ እንደጨረሰች ራሷን ጉልበቶቿ መሀል ወሸቀቻቸው። ለምን ይሄን ሁሉ መስዋዕትነት? ለምን ይህን ያህል ለአንዲት ሴት ራስን አሳልፎ መስጠት? በምላሹ ታፍቅረው አታፍቅረው ሳያውቅ ለምን ራሱን ለእሷ ሰጠ? በህይወት ቢኖርና ይህንን ጥያቄዋን ቢመልስላት በወደደች ነበር ግን እዮብ አይመለስ አሸልቧል።

ተሳሳትክ እዮብ ብትነግረኝ ይሻል ነበር። ከጭንቅላቴ የማይሻር ጠባሳ ተውክብኝ! መቼም ከፊቴ የተዘረረውን ያንተን አካል መዘንጋት አልችልም ፣ከአእምሮዬ ሊጠፋ አይችልም። እዮብ ስህተት ሰርተኻል አዎ በጣም ተሳስተሃል! እጇ ላከ የነበረውን ወረቀት ጨመደደችው። ምን ልታስብ እንደሚገባት ማወቅ አልቻለችም። ብቻ ልትከፍለው የማትችለው የእዮብ ውለታ አለባት።

አፈቅረው ነበር? እራሷን ጠየቀች ልቧ የአዎንታም የአሉታም ምላሽ አልሰጣትም። ለረጅም ሰአት አነባች። አልአዛር ለማባበል አልሞከረም። ምክንያቱም የእሱም እምባ እየፈሰሰ ነበር። አንድ ብቸኛ ወንድሙን እንዳጣ ገብቶታል። በጀግንነት የሞተው የወንድሙ ወኔና ድፍረት ታወሰው። ለእዚች ከፊት ለፊቱ ለተቀመጠችው ሴት የነበረው የፍቅር ጥንካሬ የተለየ ነበር። ምን ያደርጋል? በህይወት ሳለ መፈቀሯን ሳታውቅ ከሞተ በኅላ ለፍቅሯ የከፈለውን መስዋዕትነት የተረዳችው ወጣት ላታገግም ቆስላለች። በምንም መንገድ ሊያፅናናት አይችልም።

ማን ያውቃል? ጊዜ የሚያመጣው አይታወቅም አለ ለራሱ እዮብን ልትዘነጋ የምትችልበት መንገድ ይኖራል።  በተቻለው መጠን ሀዘኗን ልትረሳ የምትችልበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በሙሉ አቅሙ ቆርጧል። ከመንግስትም የደንነት አባላት ጋር በነበረው የጠበቀ ግንኙነት አንድ የውሸት መታወቂያ ሊያገኝላት ችሏል። የእሷን መምጣት ቀደም ብሎ እየጠበቀች ስለነበር ሁሉንም ነገር አስቀድሞ ዝግጁ አድርጓል።

መታወቂያውን ከኪሱ አውጥቶ ጠረጴዛው ላይ አስቀመጠው። 'መአዛ አሸናፊ' ይላል። ምንድን ነው በሚል ሁኔታ ተመለከተችው። አዲሱ ስምሽ ነው ትንሽ ራስሽን መቀየር ይኖርብሻል አለና ትርምስምሱ የወጣውን ረጅም ፀጉሯን አየ። መቆረጥ ሳይኖርበት አይቀርም። በተወሰነ መልኩ የፊትሽን ገፅታ ሊቀይረው ይችላል። ግን ይህን የመሰለ ፀጉር ተቆርጦ ሲወድግ ያሳዝናል ሲል አሰበ።

ብሌን አላመነታችም። በህይወት መኖር እስካለባት ድረስ ራሷን መለወጧ የግድ ነው። ሻወር መውሰድ ፈልጋለች። አልአዛር ጭንቅላቷን ያነበበ ይመስል መታጠብ ከፈለግሽ ሻወር ቤቱን ላሳይሽ እችላለሁ።  ፀጉርሽን የምትቆርጪበት መቀስ በስተቀኝ ባለው ኮመዲኖ ላይ ይገኛል። አላት ጊዜ ሳታጠፋ ልብሷን አወላልቃ ውሀው ውስጥ ተነከረች። ውሀው እንደውጪው ቆሻሻዋ ልቧ ውስጥም ያለውን ሸክም መውሰድ ቢችል ምንኛ በተደሰተች ነበር። ዐይኗን ጨፍና ከላይ የሚወርደውን ውሀ ከጭንቅላቷ ጀምሮ ታች እስኪደርስ ድረስ ታዳምጠዋለች። ከውሀው አንድ መፍትሔ ታገኝ ይመስል አሁንም አሁንም ትነከራለች። ሰውነቷ ቢፀዳም መውጣቱን ጠላችው። በጣም ከምትወዳት  ምስኪን እናቷ ጋር እንደማትገናኝ ተረድታለች። ይሄኔ እማዬ ሞቴን ሰምታ ሀዘን ተቀምጣ ይሆናል ስትል አሰበች። በራ ሄዳ አይዞሽ በህይወት አለውልሽ ልትላት ተመኘች።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/124

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In addition, Telegram's architecture limits the ability to slow the spread of false information: the lack of a central public feed, and the fact that comments are easily disabled in channels, reduce the space for public pushback. "Markets were cheering this economic recovery and return to strong economic growth, but the cheers will turn to tears if the inflation outbreak pushes businesses and consumers to the brink of recession," he added. Telegram has gained a reputation as the “secure” communications app in the post-Soviet states, but whenever you make choices about your digital security, it’s important to start by asking yourself, “What exactly am I securing? And who am I securing it from?” These questions should inform your decisions about whether you are using the right tool or platform for your digital security needs. Telegram is certainly not the most secure messaging app on the market right now. Its security model requires users to place a great deal of trust in Telegram’s ability to protect user data. For some users, this may be good enough for now. For others, it may be wiser to move to a different platform for certain kinds of high-risk communications. Telegram users are able to send files of any type up to 2GB each and access them from any device, with no limit on cloud storage, which has made downloading files more popular on the platform. As the war in Ukraine rages, the messaging app Telegram has emerged as the go-to place for unfiltered live war updates for both Ukrainian refugees and increasingly isolated Russians alike.
from it


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American