Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-93812-93813-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/93812 -
Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake : ዛሬ ሰኞ ምሽት 5:24 ሲል በሬክተር ስኬል 4.8 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 17 ኪ/ሜ ርቀት ላይ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ አሳውቋል። የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባና ሌሎችም ከተሞች ተሰምቷል። " አሁን ላይ ቀንሷል ቆሟል ፣ ከአሁን በኃላ ምንም ነገር አይፈጠርም " በሚል መዘናጋት ጥንቃቄ እና ትኩረት ማጣት እንዳይመጣ መጠንቀቅ ይገባል። የመሬት…
“ አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ነው እየመነጨ ያለው። ደብረ ብርሃን የተሰማ ነገር የለም” - አታላይ አየለ (ፕ/ር)

ትላንት ከሌሊቱ 10፡46 በደብረ ብርሃን አካባቢ በሬክተር ስኬል 4.9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የጀርመን የጂኦ ሳይንስ ጥናትና ምርምር ማዕከል ድረጽ መረጃ አውጥቷል ፤ ይኸው መረጃም ሲዘገብ ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵዮጵያ በበኩሉ፣ በጉዳዩ ዙሪያ ከዘርፉ ተመራማሪ ማብራሪያ ጠይቋል።

ደብረ ብርሃን አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል መባሉን እውነት ነው ? ብለን የጠየቅናቸው በአዲስ አበባ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ አታላይ አየለ (ፕ/ሮ)፣ " ኧረ ውሸት ነው " ሲሉ መልሰዋል።

" ደብረ ብርሃን አካባቢ የለም። እዛው አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ነው እየመነጨ ያለው። ደብረ ብርሃን የተሰማ ነገር የለም " ነው ያሉት።

" የዘርፉ ተቋማት በሚያወጡት መረጃ፣ ' ከደብረ ብርሃን ይህን ያህል ኪሎ ሜትር፣ ወይ ከመተሃራ ይህንን ያህል ኪሎ ሜትር ' ይላሉ ስም እየጠሩ። ከዛ በመለስ ግን እንደዚህ የሚባል ነገር የለም። ደብረ ብርሃን አሁን ከየት የመጣ መንቀጥቀጥ ነው? " ሲሉ ነው ምላሽ የሰጡት።

ከዚህ ቀደም ከደብረ ሲና በ52 ኪሎ ሜትር ተከሰተ ለተባ የመሬት መንቀጥቀጥ በተለመለተ፣ ከሚከሰትበት የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የቦታ ለውጥ አደረገ ማለት እንዳልሆነ ተመራማሪው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

" በአንዳንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም " ነበር ያሉት።

አዋሽ ፈንታሌ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች ከተሞች ንዝረቱ እየተሰማ እንደሆነ ይታወቃል።

ሌላው በተያያዘ፣ የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ አሁንስ በምን ደረጃ ላይ ነው ያለው ? በሚል ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ለቀረበላቸው ተጨማሪ ምላሽ ሰጥተዋል።

አታላይ አየለ (ፕ/ር) ምን ምላሽ ሰጡ ?

" ምንም የተለዬ ነገር የለም እንደቀጠለ ነው። ከቀን ቀን ትንሽ ለውጥ ያለው ይመስላል። ግን ነገ ይቆማል የሚባል ነገር አይደለም።

ስቲል ይታያል እንቅስቃሴ። የሚረግብ አይመስልም በአጭሩ። 

ዌብ ሳይት ተለጠፈ የሚለው ሳይሆን ለሊት 10 ገደማ ተፈጠረ የተባለው አካባቢ አንድ ነው ሪፓርት የተደረገው ግን ከእኩለ ለሊት ጀምሮ እስካሁን ስንት ተፈጠረ ብትለኝ ከ100ዎች በላይ ሊሆኑ ይችላሉ።

ያ ማለት የሚረግብ አይነት አይደለም
" ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93812
Create:
Last Update:

“ አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ነው እየመነጨ ያለው። ደብረ ብርሃን የተሰማ ነገር የለም” - አታላይ አየለ (ፕ/ር)

ትላንት ከሌሊቱ 10፡46 በደብረ ብርሃን አካባቢ በሬክተር ስኬል 4.9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የጀርመን የጂኦ ሳይንስ ጥናትና ምርምር ማዕከል ድረጽ መረጃ አውጥቷል ፤ ይኸው መረጃም ሲዘገብ ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵዮጵያ በበኩሉ፣ በጉዳዩ ዙሪያ ከዘርፉ ተመራማሪ ማብራሪያ ጠይቋል።

ደብረ ብርሃን አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል መባሉን እውነት ነው ? ብለን የጠየቅናቸው በአዲስ አበባ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ አታላይ አየለ (ፕ/ሮ)፣ " ኧረ ውሸት ነው " ሲሉ መልሰዋል።

" ደብረ ብርሃን አካባቢ የለም። እዛው አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ነው እየመነጨ ያለው። ደብረ ብርሃን የተሰማ ነገር የለም " ነው ያሉት።

" የዘርፉ ተቋማት በሚያወጡት መረጃ፣ ' ከደብረ ብርሃን ይህን ያህል ኪሎ ሜትር፣ ወይ ከመተሃራ ይህንን ያህል ኪሎ ሜትር ' ይላሉ ስም እየጠሩ። ከዛ በመለስ ግን እንደዚህ የሚባል ነገር የለም። ደብረ ብርሃን አሁን ከየት የመጣ መንቀጥቀጥ ነው? " ሲሉ ነው ምላሽ የሰጡት።

ከዚህ ቀደም ከደብረ ሲና በ52 ኪሎ ሜትር ተከሰተ ለተባ የመሬት መንቀጥቀጥ በተለመለተ፣ ከሚከሰትበት የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የቦታ ለውጥ አደረገ ማለት እንዳልሆነ ተመራማሪው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

" በአንዳንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም " ነበር ያሉት።

አዋሽ ፈንታሌ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች ከተሞች ንዝረቱ እየተሰማ እንደሆነ ይታወቃል።

ሌላው በተያያዘ፣ የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ አሁንስ በምን ደረጃ ላይ ነው ያለው ? በሚል ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ለቀረበላቸው ተጨማሪ ምላሽ ሰጥተዋል።

አታላይ አየለ (ፕ/ር) ምን ምላሽ ሰጡ ?

" ምንም የተለዬ ነገር የለም እንደቀጠለ ነው። ከቀን ቀን ትንሽ ለውጥ ያለው ይመስላል። ግን ነገ ይቆማል የሚባል ነገር አይደለም።

ስቲል ይታያል እንቅስቃሴ። የሚረግብ አይመስልም በአጭሩ። 

ዌብ ሳይት ተለጠፈ የሚለው ሳይሆን ለሊት 10 ገደማ ተፈጠረ የተባለው አካባቢ አንድ ነው ሪፓርት የተደረገው ግን ከእኩለ ለሊት ጀምሮ እስካሁን ስንት ተፈጠረ ብትለኝ ከ100ዎች በላይ ሊሆኑ ይችላሉ።

ያ ማለት የሚረግብ አይነት አይደለም
" ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93812

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The Security Service of Ukraine said in a tweet that it was able to effectively target Russian convoys near Kyiv because of messages sent to an official Telegram bot account called "STOP Russian War." The SC urges the public to refer to the SC’s I nvestor Alert List before investing. The list contains details of unauthorised websites, investment products, companies and individuals. Members of the public who suspect that they have been approached by unauthorised firms or individuals offering schemes that promise unrealistic returns In addition, Telegram now supports the use of third-party streaming tools like OBS Studio and XSplit to broadcast live video, allowing users to add overlays and multi-screen layouts for a more professional look. As the war in Ukraine rages, the messaging app Telegram has emerged as the go-to place for unfiltered live war updates for both Ukrainian refugees and increasingly isolated Russians alike. Individual messages can be fully encrypted. But the user has to turn on that function. It's not automatic, as it is on Signal and WhatsApp.
from jp


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American