Telegram Group & Telegram Channel
" ህዝቡ ያለፈው አልበቃ ብሎት የትናንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም በሽብር እና በጦርነት ወሬ ስሜት ወስጥ ይገኛል ! " - የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር 

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ለትግራይ ህዝብ በተለይ ደግሞ ለልሂቃን መልእክት እና ምክር አስተላልፈዋል። 

ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥር 26/2017 ዓ.ም በፅሁፍ ባስተላለፉት ጠንካራ መልእክት እና ምክር ትግራይን እና ህዝብዋን " የጥንታዊ እና ገናና ታሪክ ባለቤት የኢትዮጵያ ዋልታና መከታ " ሲሉ ገልፀዋቸዋል።

" የትግራይ ህዝብ ታሪክ የማያረጅ እና የማይደበዝዝ በደማቅ ቀለም የተፃፈ ነው " ያሉ ሲሆን " ክልሉ ለህዝባቸው እና አገራቸው የሚጠቅሙ በርካታ ሊቃውንት ፣ የሃይማኖት መሪዎች ፣ ፓለቲከኞች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ያፈራ ነው " ሲሉ ፅፈዋል።

የትግራይ ህዝብ የዘመናት ተጋድሎዎች ያወሱ እና ያወደሱት ጠቅላይ ሚንስትሩ " የአገር ፍቅር ስሜት የትግራይ ህዝብ መለያ እና መገለጫ ነው " ብለዋል።

" ቢሆንም መጥፎ አጋጣሚ ሆኖ በተለይ ባለፉት አንድ መቶ ዓመታት ከማእከላይ መንግስቱ ለተደጋጋሚ ጊዜዎች ግጭት ውስጥ በመግባት ትግራይ የጦርነት አውድማ ፤ ህዝቡም ደግሞ የሁሉም ዓይነት ችግሮች ተጋላጭ እና ተጠቂ መሆኑን " ጠቅላይ ሚንስትሩ አውስተው " የሚያጋጥሙ እና የሚፈጠሩ ችግሮች ከውግያ በመለስ የሚፈቱበት አማራጭ አልነበረም ወይ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

" ህዝቡ ያለፈው አልበቃ ብሎት የትናንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም በሽብር እና በጦርነት ወሬ ስሜት ወስጥ ይገኛል ፤ ይህንን ዓይነት አደጋ የሚፈጥር ችግር እንዴት መፍታት እና ማስወገድ እንደሚቻል በግልፅ መነጋገር እንደሚያስፈልግ ለአስተዋይ የሚሰወር አይደለም " ብለዋል።

" ስለሆነም በፓለቲካ ፣ በንግድ ፣ ፀጥታ ፣ አካዳሚ እና ሚድያ እና በሌሎች የስራ ዘርፎች የተሰማራችሁ የትግራይ ልሂቃን ወገኖች የትግራይ ህዝብ እስከ ዛሬ የተሰቃየው የከፈለው ዋጋ ይብቃው ፤ ልዩነትን በመነጋገር እና በውይይት የመፍታት ባህልንና ልምድ ታጠቁ " ሲሉ መክረዋል።

ልሂቃኑ ከፌደራል መንግስት እና ሌሎች ሃይሎች ያላቸው ልዩነት በአገሪቱ ህገ-መንግስት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመግባባት ለመፍታት ዝግጁ እንዲሆኑ ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።

" የፌደራል መንግስት በሁሉም አጀንዳዎች ለመነጋገር ፤ የሃሳብ ልዩነት ደግሞ እንደልዩነት በማክበር ፣ በሚያግባቡ አገራዊ ርእሰ ጉዳዮች በመስማማት ለመስራት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩ የትግራይ ህዝብ እና ልሂቃኑ መገንዘብ አለባችሁ " ብለዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልእክታቸው ማሳረግያ " ሰላም እና ብሩህ መፃኢ ለትግራይ ህዝብ ፣ ግጭት እና ጦርነት ይብቃ ! " የሚል መልካም ምኞታቸው አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopia            



group-telegram.com/tikvahethiopia/94219
Create:
Last Update:

" ህዝቡ ያለፈው አልበቃ ብሎት የትናንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም በሽብር እና በጦርነት ወሬ ስሜት ወስጥ ይገኛል ! " - የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር 

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ለትግራይ ህዝብ በተለይ ደግሞ ለልሂቃን መልእክት እና ምክር አስተላልፈዋል። 

ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥር 26/2017 ዓ.ም በፅሁፍ ባስተላለፉት ጠንካራ መልእክት እና ምክር ትግራይን እና ህዝብዋን " የጥንታዊ እና ገናና ታሪክ ባለቤት የኢትዮጵያ ዋልታና መከታ " ሲሉ ገልፀዋቸዋል።

" የትግራይ ህዝብ ታሪክ የማያረጅ እና የማይደበዝዝ በደማቅ ቀለም የተፃፈ ነው " ያሉ ሲሆን " ክልሉ ለህዝባቸው እና አገራቸው የሚጠቅሙ በርካታ ሊቃውንት ፣ የሃይማኖት መሪዎች ፣ ፓለቲከኞች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ያፈራ ነው " ሲሉ ፅፈዋል።

የትግራይ ህዝብ የዘመናት ተጋድሎዎች ያወሱ እና ያወደሱት ጠቅላይ ሚንስትሩ " የአገር ፍቅር ስሜት የትግራይ ህዝብ መለያ እና መገለጫ ነው " ብለዋል።

" ቢሆንም መጥፎ አጋጣሚ ሆኖ በተለይ ባለፉት አንድ መቶ ዓመታት ከማእከላይ መንግስቱ ለተደጋጋሚ ጊዜዎች ግጭት ውስጥ በመግባት ትግራይ የጦርነት አውድማ ፤ ህዝቡም ደግሞ የሁሉም ዓይነት ችግሮች ተጋላጭ እና ተጠቂ መሆኑን " ጠቅላይ ሚንስትሩ አውስተው " የሚያጋጥሙ እና የሚፈጠሩ ችግሮች ከውግያ በመለስ የሚፈቱበት አማራጭ አልነበረም ወይ ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

" ህዝቡ ያለፈው አልበቃ ብሎት የትናንት ቁስሉ ሳይሽር አሁንም በሽብር እና በጦርነት ወሬ ስሜት ወስጥ ይገኛል ፤ ይህንን ዓይነት አደጋ የሚፈጥር ችግር እንዴት መፍታት እና ማስወገድ እንደሚቻል በግልፅ መነጋገር እንደሚያስፈልግ ለአስተዋይ የሚሰወር አይደለም " ብለዋል።

" ስለሆነም በፓለቲካ ፣ በንግድ ፣ ፀጥታ ፣ አካዳሚ እና ሚድያ እና በሌሎች የስራ ዘርፎች የተሰማራችሁ የትግራይ ልሂቃን ወገኖች የትግራይ ህዝብ እስከ ዛሬ የተሰቃየው የከፈለው ዋጋ ይብቃው ፤ ልዩነትን በመነጋገር እና በውይይት የመፍታት ባህልንና ልምድ ታጠቁ " ሲሉ መክረዋል።

ልሂቃኑ ከፌደራል መንግስት እና ሌሎች ሃይሎች ያላቸው ልዩነት በአገሪቱ ህገ-መንግስት በዴሞክራሲያዊ መንገድ በመግባባት ለመፍታት ዝግጁ እንዲሆኑ ጠቅላይ ሚንስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።

" የፌደራል መንግስት በሁሉም አጀንዳዎች ለመነጋገር ፤ የሃሳብ ልዩነት ደግሞ እንደልዩነት በማክበር ፣ በሚያግባቡ አገራዊ ርእሰ ጉዳዮች በመስማማት ለመስራት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መኖሩ የትግራይ ህዝብ እና ልሂቃኑ መገንዘብ አለባችሁ " ብለዋል።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልእክታቸው ማሳረግያ " ሰላም እና ብሩህ መፃኢ ለትግራይ ህዝብ ፣ ግጭት እና ጦርነት ይብቃ ! " የሚል መልካም ምኞታቸው አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopia            

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94219

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Ukrainian forces successfully attacked Russian vehicles in the capital city of Kyiv thanks to a public tip made through the encrypted messaging app Telegram, Ukraine's top law-enforcement agency said on Tuesday. Stocks dropped on Friday afternoon, as gains made earlier in the day on hopes for diplomatic progress between Russia and Ukraine turned to losses. Technology stocks were hit particularly hard by higher bond yields. Just days after Russia invaded Ukraine, Durov wrote that Telegram was "increasingly becoming a source of unverified information," and he worried about the app being used to "incite ethnic hatred." On February 27th, Durov posted that Channels were becoming a source of unverified information and that the company lacks the ability to check on their veracity. He urged users to be mistrustful of the things shared on Channels, and initially threatened to block the feature in the countries involved for the length of the war, saying that he didn’t want Telegram to be used to aggravate conflict or incite ethnic hatred. He did, however, walk back this plan when it became clear that they had also become a vital communications tool for Ukrainian officials and citizens to help coordinate their resistance and evacuations. Pavel Durov, a billionaire who embraces an all-black wardrobe and is often compared to the character Neo from "the Matrix," funds Telegram through his personal wealth and debt financing. And despite being one of the world's most popular tech companies, Telegram reportedly has only about 30 employees who defer to Durov for most major decisions about the platform.
from jp


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American