Telegram Group & Telegram Channel
#US #Egypt

የዴሞክራት ፓርቲ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ የግብፅን ፍላጎት ለማስከበር ጉቦ ተቀብለው በአሜሪካ ሴኔት ውስጥ የግብፅን አጀንዳ በማራመድና በሌሎች ክሶች ጥፋተኛ ተባሉ። 

በሴናተሩ ላይ የቀረቡትን ክሶች የተመለከተው የኒውዮርክ ፍ/ቤት በመጪው ጥቅምት ወር የቅጣት ውሳኔ ለማሳለፍ ቀጠሮ መያዙ ታውቋል። 

ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በአሜሪካ ሴኔት ውስጥ የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው ሲያገለግሉ በነበሩበት ወቅት፣ ለዓመታት የግብፅን አጀንዳ በሴኔት ውስጥ ሲያራምዱ እንደነበር ለዚህም ከግብፅ መንግሥት ክፍያ ማግኘታቸውን ዓቃቤ ሕግ የሰነድ ማስረጃና የሰው ምስክሮችን በማቅረብ አረጋግጧል።

የሴናተር ሜኔንዴዝ ባለቤት የሆነችው ናዲኔ ሜኔንዴዝ  እ.ኤ.አ. በማርች 2020 ገደማ ባለቤቷ ሴናተር ሜኔንዴዝ ከአንድ የግብፅ ጦር ጄኔራል ጋር እንዲገናኙ ፕሮግራም ማዘጋጀቷንና በፕሮግራሙ ላይም ሴናተሩ ከግብፅ ጄኔራል ጋር ተገናኝተው በወቅቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ በግብፅ፣ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል ይካሄድ ስለነበረው ድርድር መወያየታቸውን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

በወቅቱም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ዋነኛ የትኩረት አጀንዳ ተደርጎ ይወሰድ እንደነበር የምርመራ ሰነዱ ይገልጻል።

ሴናተሩ ከግብፅ ጄኔራል ጋር በተገናኙ በቀጣዩ ወር ውስጥ (በኤፕሪል 2020 ወይም ገደማ)፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ላይ ለሚሳተፉት ለወቅቱ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ፀሐፊና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደብዳቤ መጻፋቸውን ያትታል።

በደብዳቤያቸው መግቢያ ላይም፣ " እኔ ይህንን ደብዳቤ የምጽፈው ግብፅ፣ ኢትዮጵያና ሱዳን በግድቡ ዙሪያ ያደርጉት የነበረው ድርድር መቋረጥ እንዳሳሰበኝ ለመግለጽ ነው " ማለታቸውን ያስረዳል።

በማከልም፣ " የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በግድቡ ድርድር ላይ የሚያደርገውን ተሳትፎ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ እጠይቃለሁ "ማለታቸውን የምርመራ መዝገቡ ይጠቅሳል።

እ.ኤ.አ. በ2021 መገባደጃ ላይ የሴናተር ሜኔንዴዝ ባለቤት የሆነችው ናዲኔ ሜኔንዴዝ አዘውትራ ከምትገናኘው ከግብፅ ጄኔራል ጋር በመነጋገር እሷና ባለቤቷ ሜኔንዴዝ ወደ ግብፅ እንዲጓዙ ፕሮግራም ማመቻቸቷንና ጉዞውም በጥቅምት 2021 መደረጉን ያስረዳል። 

በመጀመሪያ ጉዞው መደበኛ ያልሆነ ወይም ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቁጥጥር ውጭ እንዲካሄድ የታቀደ መሆኑን የሚያለክተው የምርመራ መዝገቡ፣ በኋላ ላይ አንድ የአሜሪካ ሴኔት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ባልደረባ በካይሮ የሚገኘውን የአሜሪካ ኤምባሲ በማነጋገር ጉዞው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እውቅናና ቁጥጥር የሚደረግበት መደበኛ የኮንግረንስ ልዑክ የሥራ ጉብኝት እንዲሆን ማነጋገሩን ይጠቅሳል።

ነገር ግን ይህ ጥያቄ መቅረቡን ያወቀው የግብፅ ባለሥልጣን እንደዚያ ሊሆን እንደማይችል የሚገልጽ መልዕክት ለናዲን ሜኔንዴዝ መላኩንና ናዲን ሜኔንዴዝም ምልዕክቱን ለሴናተር ሜኔንዴዝ መላኳን በዚህም ምክንያት ሴናተሩና ባለቤታቸው ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እውቅና ውጪ እንደተካሄደ በምርመራ መዝገቡ ተጠቅሷል።

ሜኔንዴዝና ባለቤታቸው ወደ ግብፅ ከተጓዙ በኋላም በካይሮ ከበርካታ የግብፅ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተውና በአንድ ከፍተኛ የግብፅ የስለላ መሥሪያ ቤት ባለሥልጣን የግል መኖሪያ ቤት እራት መብላታቸውን ያስረዳል።

በእነዚህ ወቅቶችም ልዩ መለያ ቁጥር የተከተበባቸው ባለ አንድ ወቄት የሚመዝኑ 22 የወርቅ ባሮችን (አሞሌዎችን) ከግብፅ መንግሥት በክፍያ (በጉቦ) መልክ ማግኘታቸውን፣ በዚያ ወቅት የገበያ ዋጋ መሠረት አንዱ ወቄት የወርቅ ባር 1,800 ዶላር እንደነበርና ክስ ከተመሠረተ በኋላ በወጣ የፍርድ ቤት የብርበራ ማዘዣ ሁለት የወርቅ አሞሌዎች በመኖሪያ ቤታቸው መገኘቱን የምርምራ መዝገቡ ያስረዳል።

የአሜሪካ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በክሱ እንደገለጸው፣ ሴናተር ሜኔንዴዝ በተለያዩ ጊዜያት ከግብፅ የስለላ ባለሥልጣናት ጋር መገናኘታቸውን፣ ከእነዚህም መካከል በአሜሪካ የምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ሚስጥራዊ ክትትል በተደረገበት በሞርተን ሬስቶራንት ውስጥ ከግብፅ የስለላ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው እራት በመብላት ለግብፅ መረጃ አሳልፈው መስጠታቸውን እንዲሁም ለግብፅ ምቹ ወታደራዊ የጦር መሣሪያ ድጋፍ ለማስገኘት ማሴራቸውን ይገልጻል።

ሜኔንዴዝ ለግብፅ መንግሥት ራሳቸው ደብዳቤ አዘጋጅተው ከሰጡ በኋላ ይህንኑ ደብዳቤ በመጠቀም በግብፅ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ሌሎች የኮንግረስ አባላት ያላቸውን ሥጋት ለማግባባት እንደተጠቀሙበት የአሜሪካ ፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የክስ ሰነድ ያስረዳል።

በጥቅሉ የአሜሪካ የምርመራ ቢሮ እ.ኤ.አ. በጁን 16 ቀን 2022 ከሜኔንዴዝ ቤት በድምሩ 486,461 ዶላር፣ አንድ ወቄት የሚመዝኑ 11 የወርቅ አሞሌዎችንና አንድ ኪሎ ግራም የሚመዝኑ ሁለት የወርቅ አሞሌዎችን በቁጥጥር ሥር አውሏል።

በአጠቃላይ የኒው ጀርሲው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የውጭ መንግሥት ፍላጎትን ለመፈጸም ሥልጣናቸውን መጠቀም፣ ጉቦ መቀበል፣ ማጭበርበር፣ ፍትሕን ማደናቀፍን ጨምሮ በ16 የወንጀል ድርጊቶች የተከሰሱ ሲሆን፣ ባለፈው ማክሰኞ በሁሉም ክሶች ጥፋተኛ ተብለው ተበይኖባቸዋል።

የቅጣት ውሳኔውን ለማስተላለፍ ለመጪው ጥቅም ወር 2017 ዓ.ም. ቀጠሮ የተያዘ ሲሆን፣ ሴናተሩ በትንሹ ከ20 ዓመት በላይ እስር ሊፈረድባቸው እንደሚችል ሲኤንኤንን ጨምሮ የተለያዩ የአሜሪካ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

Credit - Reporter Newspaper

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/89067
Create:
Last Update:

#US #Egypt

የዴሞክራት ፓርቲ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ የግብፅን ፍላጎት ለማስከበር ጉቦ ተቀብለው በአሜሪካ ሴኔት ውስጥ የግብፅን አጀንዳ በማራመድና በሌሎች ክሶች ጥፋተኛ ተባሉ። 

በሴናተሩ ላይ የቀረቡትን ክሶች የተመለከተው የኒውዮርክ ፍ/ቤት በመጪው ጥቅምት ወር የቅጣት ውሳኔ ለማሳለፍ ቀጠሮ መያዙ ታውቋል። 

ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በአሜሪካ ሴኔት ውስጥ የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው ሲያገለግሉ በነበሩበት ወቅት፣ ለዓመታት የግብፅን አጀንዳ በሴኔት ውስጥ ሲያራምዱ እንደነበር ለዚህም ከግብፅ መንግሥት ክፍያ ማግኘታቸውን ዓቃቤ ሕግ የሰነድ ማስረጃና የሰው ምስክሮችን በማቅረብ አረጋግጧል።

የሴናተር ሜኔንዴዝ ባለቤት የሆነችው ናዲኔ ሜኔንዴዝ  እ.ኤ.አ. በማርች 2020 ገደማ ባለቤቷ ሴናተር ሜኔንዴዝ ከአንድ የግብፅ ጦር ጄኔራል ጋር እንዲገናኙ ፕሮግራም ማዘጋጀቷንና በፕሮግራሙ ላይም ሴናተሩ ከግብፅ ጄኔራል ጋር ተገናኝተው በወቅቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ በግብፅ፣ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል ይካሄድ ስለነበረው ድርድር መወያየታቸውን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

በወቅቱም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ዋነኛ የትኩረት አጀንዳ ተደርጎ ይወሰድ እንደነበር የምርመራ ሰነዱ ይገልጻል።

ሴናተሩ ከግብፅ ጄኔራል ጋር በተገናኙ በቀጣዩ ወር ውስጥ (በኤፕሪል 2020 ወይም ገደማ)፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ላይ ለሚሳተፉት ለወቅቱ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ፀሐፊና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደብዳቤ መጻፋቸውን ያትታል።

በደብዳቤያቸው መግቢያ ላይም፣ " እኔ ይህንን ደብዳቤ የምጽፈው ግብፅ፣ ኢትዮጵያና ሱዳን በግድቡ ዙሪያ ያደርጉት የነበረው ድርድር መቋረጥ እንዳሳሰበኝ ለመግለጽ ነው " ማለታቸውን ያስረዳል።

በማከልም፣ " የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በግድቡ ድርድር ላይ የሚያደርገውን ተሳትፎ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ እጠይቃለሁ "ማለታቸውን የምርመራ መዝገቡ ይጠቅሳል።

እ.ኤ.አ. በ2021 መገባደጃ ላይ የሴናተር ሜኔንዴዝ ባለቤት የሆነችው ናዲኔ ሜኔንዴዝ አዘውትራ ከምትገናኘው ከግብፅ ጄኔራል ጋር በመነጋገር እሷና ባለቤቷ ሜኔንዴዝ ወደ ግብፅ እንዲጓዙ ፕሮግራም ማመቻቸቷንና ጉዞውም በጥቅምት 2021 መደረጉን ያስረዳል። 

በመጀመሪያ ጉዞው መደበኛ ያልሆነ ወይም ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቁጥጥር ውጭ እንዲካሄድ የታቀደ መሆኑን የሚያለክተው የምርመራ መዝገቡ፣ በኋላ ላይ አንድ የአሜሪካ ሴኔት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ባልደረባ በካይሮ የሚገኘውን የአሜሪካ ኤምባሲ በማነጋገር ጉዞው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እውቅናና ቁጥጥር የሚደረግበት መደበኛ የኮንግረንስ ልዑክ የሥራ ጉብኝት እንዲሆን ማነጋገሩን ይጠቅሳል።

ነገር ግን ይህ ጥያቄ መቅረቡን ያወቀው የግብፅ ባለሥልጣን እንደዚያ ሊሆን እንደማይችል የሚገልጽ መልዕክት ለናዲን ሜኔንዴዝ መላኩንና ናዲን ሜኔንዴዝም ምልዕክቱን ለሴናተር ሜኔንዴዝ መላኳን በዚህም ምክንያት ሴናተሩና ባለቤታቸው ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እውቅና ውጪ እንደተካሄደ በምርመራ መዝገቡ ተጠቅሷል።

ሜኔንዴዝና ባለቤታቸው ወደ ግብፅ ከተጓዙ በኋላም በካይሮ ከበርካታ የግብፅ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተውና በአንድ ከፍተኛ የግብፅ የስለላ መሥሪያ ቤት ባለሥልጣን የግል መኖሪያ ቤት እራት መብላታቸውን ያስረዳል።

በእነዚህ ወቅቶችም ልዩ መለያ ቁጥር የተከተበባቸው ባለ አንድ ወቄት የሚመዝኑ 22 የወርቅ ባሮችን (አሞሌዎችን) ከግብፅ መንግሥት በክፍያ (በጉቦ) መልክ ማግኘታቸውን፣ በዚያ ወቅት የገበያ ዋጋ መሠረት አንዱ ወቄት የወርቅ ባር 1,800 ዶላር እንደነበርና ክስ ከተመሠረተ በኋላ በወጣ የፍርድ ቤት የብርበራ ማዘዣ ሁለት የወርቅ አሞሌዎች በመኖሪያ ቤታቸው መገኘቱን የምርምራ መዝገቡ ያስረዳል።

የአሜሪካ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በክሱ እንደገለጸው፣ ሴናተር ሜኔንዴዝ በተለያዩ ጊዜያት ከግብፅ የስለላ ባለሥልጣናት ጋር መገናኘታቸውን፣ ከእነዚህም መካከል በአሜሪካ የምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ሚስጥራዊ ክትትል በተደረገበት በሞርተን ሬስቶራንት ውስጥ ከግብፅ የስለላ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው እራት በመብላት ለግብፅ መረጃ አሳልፈው መስጠታቸውን እንዲሁም ለግብፅ ምቹ ወታደራዊ የጦር መሣሪያ ድጋፍ ለማስገኘት ማሴራቸውን ይገልጻል።

ሜኔንዴዝ ለግብፅ መንግሥት ራሳቸው ደብዳቤ አዘጋጅተው ከሰጡ በኋላ ይህንኑ ደብዳቤ በመጠቀም በግብፅ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ሌሎች የኮንግረስ አባላት ያላቸውን ሥጋት ለማግባባት እንደተጠቀሙበት የአሜሪካ ፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የክስ ሰነድ ያስረዳል።

በጥቅሉ የአሜሪካ የምርመራ ቢሮ እ.ኤ.አ. በጁን 16 ቀን 2022 ከሜኔንዴዝ ቤት በድምሩ 486,461 ዶላር፣ አንድ ወቄት የሚመዝኑ 11 የወርቅ አሞሌዎችንና አንድ ኪሎ ግራም የሚመዝኑ ሁለት የወርቅ አሞሌዎችን በቁጥጥር ሥር አውሏል።

በአጠቃላይ የኒው ጀርሲው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የውጭ መንግሥት ፍላጎትን ለመፈጸም ሥልጣናቸውን መጠቀም፣ ጉቦ መቀበል፣ ማጭበርበር፣ ፍትሕን ማደናቀፍን ጨምሮ በ16 የወንጀል ድርጊቶች የተከሰሱ ሲሆን፣ ባለፈው ማክሰኞ በሁሉም ክሶች ጥፋተኛ ተብለው ተበይኖባቸዋል።

የቅጣት ውሳኔውን ለማስተላለፍ ለመጪው ጥቅም ወር 2017 ዓ.ም. ቀጠሮ የተያዘ ሲሆን፣ ሴናተሩ በትንሹ ከ20 ዓመት በላይ እስር ሊፈረድባቸው እንደሚችል ሲኤንኤንን ጨምሮ የተለያዩ የአሜሪካ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

Credit - Reporter Newspaper

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/89067

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Telegram was co-founded by Pavel and Nikolai Durov, the brothers who had previously created VKontakte. VK is Russia’s equivalent of Facebook, a social network used for public and private messaging, audio and video sharing as well as online gaming. In January, SimpleWeb reported that VK was Russia’s fourth most-visited website, after Yandex, YouTube and Google’s Russian-language homepage. In 2016, Forbes’ Michael Solomon described Pavel Durov (pictured, below) as the “Mark Zuckerberg of Russia.” Elsewhere, version 8.6 of Telegram integrates the in-app camera option into the gallery, while a new navigation bar gives quick access to photos, files, location sharing, and more. Such instructions could actually endanger people — citizens receive air strike warnings via smartphone alerts. Multiple pro-Kremlin media figures circulated the post's false claims, including prominent Russian journalist Vladimir Soloviev and the state-controlled Russian outlet RT, according to the DFR Lab's report. "There are several million Russians who can lift their head up from propaganda and try to look for other sources, and I'd say that most look for it on Telegram," he said.
from kr


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American