Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#መግለጫ : " የአእላፋት ዝማሬ/The Melody of Myriads " ሰኞ በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ በተመሳሳይ ሰዓት ይካሄዳል። ይህንን አስመልክቶ የተሰጠው መግለጫ ከላይ ተያይዟል። የዘንድሮው የእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads በአዲስ አበባ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል (ቦሌ መድኃኔዓለም) ፤ በድሬዳዋ ደግሞ ለገሀር አደባባይ ብቻ ነው የሚካሄደው። (መግለጫውን ያንብቡ)…
#የአእላፋትዝማሬ #TheMelodyofMyriads

“ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” - የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ (ኢጃት)

ታኅሳስ 29 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረውን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያው ጃንደረባ ትውልድ ያዘጋጀው “ልደትን በባለ ልደቱ ቤት” የተሰኘውን የአእላፍ ዝማሬ በተመለከተ አዘጋጆቹ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥተዋል።

የዝማሬ ጉባዔው በአዲስ አበባ በድሬዳዋ እንደሚከናወን የገለጹት አዘጋጆች፣ “ ላለፉት ስምንት ወራት ለዚህ ታላቅ የዝማሬ ጉባዔ ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል ” ብለዋል።

የጉባዔው ዋነኛ ዓላማ በአልባሌ ቦታ የሚውሉ ወገኖች በዓሉን በቤተክርስቲያን የመላክትን ዝማሬ በመዘመር እንዲያሳልፉ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ቢንያም አሕመድ ፤  “ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” ብለዋል።

“ በሌሎች አካባቢዎች ላይ የተዘጋጁ ዝግጅቶች ካሉም በእዛው በመገኘት እንድታሳልፉ የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ ጥሪ ያቀርባል ” ሲሉ አሳስበዋል።

በመርሃ ግብሩ በቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ ምንም አይነት ሽያጭ እንደማይከናውን አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።

በሌላ በኩል፣ “ አእላፋት ዝማሬ ነጭ ልብስ ልበሱ ” ተብሏል በሚል ነጭ ልብስ በተጋነነ ዋጋ የሚቸበችቡ ሁነቱን የተከተሉ ነጋዴዎች ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ነጭ ልብስ በውድ ወጋ እየተቸበቸበ ነው የሚል አስተያዬት እየተሰጠ ተስተውሏል፣ ለመርሀ ግብሩ ነጭ ልብስ ብቻ ለብሶ መምጣት ግዴታ ነው ? ሲል ለአዘጋጆቹ ጥያቄ አቅርቧል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ብንያም አሕመድ በሰጡት ምላሽም፣ “ ነጭ ልብስ የሌለን ያለንን ልብስ ንጹህ አድርገን እንምጣ። ዓላማችን ልብሱ ለመቁረቢያ እንዲሆን ነው ” ብለዋል።

“ ኦርቶዶክሳዊ ኢኮኖሚ እንዲፈጠር ይፈለጋል ግልጽ ነው። በዚህ ምክንያት ወደ ስራ የሚገቡ፣ ሥራቸውን የሚያስፋፉ፣ የሚለወጡ ኦርቶዶክሳዊያን ቢኖሩ ይሄ የማኀበራችን አንዱ ዓላማ ነው ” ሲሉ ነው የተናገሩት።

“ ስለዚህ ይህን በቀና ዓይን ነው የምናየው ” ያሉት አቶ ብንያም፣ “ በእርግጥ በዚሁ ምክንያት ደግሞ አጋጣሚውን የሚጠቀሙ፣ Accidental Entrprenuers የምንላቸው መጥተው ባለሃብት ለመሆን የሚጥሩ ይኖራሉ ” ሲሉም አክለዋል።

“ ልደቱ የሰዎች የመላክት ዝማሬ ነው። ስለዚህ ይህንን በማሰብ ነጭ ለብሰን እንመጣለን ” ብለው፣ “ ዘወትር ወደ ቤተ ክርስቲያን ስንሄድ የምናደርገው ነው፣ የተለዬ ነገር የለውም ” ነው ያሉት።

ሆኖም ነጭ ልብስ የሌላቸው ያላቸውን ልብስ በአግባቡ ለብሰው በዝማሬ መርሀ ግብሩ መገኘታቸው እንዳይዘነጋ መልዕክት ተላልፏል። 

ዝማሬው ዘማሪያን እየዘመሩ ምዕመናን የሚቀበሉበት ሂደት ሳይሆን ልደቱን በሚያወሱ ዝማሬዎች ሁሉም በጋራ ምስጋና እንዲያቀርብ መሆኑ ተሰምሮበታል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93419
Create:
Last Update:

#የአእላፋትዝማሬ #TheMelodyofMyriads

“ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” - የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ (ኢጃት)

ታኅሳስ 29 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረውን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያው ጃንደረባ ትውልድ ያዘጋጀው “ልደትን በባለ ልደቱ ቤት” የተሰኘውን የአእላፍ ዝማሬ በተመለከተ አዘጋጆቹ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥተዋል።

የዝማሬ ጉባዔው በአዲስ አበባ በድሬዳዋ እንደሚከናወን የገለጹት አዘጋጆች፣ “ ላለፉት ስምንት ወራት ለዚህ ታላቅ የዝማሬ ጉባዔ ከፍተኛ ዝግጅት ሲደረግ ቆይቷል ” ብለዋል።

የጉባዔው ዋነኛ ዓላማ በአልባሌ ቦታ የሚውሉ ወገኖች በዓሉን በቤተክርስቲያን የመላክትን ዝማሬ በመዘመር እንዲያሳልፉ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ቢንያም አሕመድ ፤  “ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” ብለዋል።

“ በሌሎች አካባቢዎች ላይ የተዘጋጁ ዝግጅቶች ካሉም በእዛው በመገኘት እንድታሳልፉ የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ ጥሪ ያቀርባል ” ሲሉ አሳስበዋል።

በመርሃ ግብሩ በቤተክርስቲያን ቅጽር ግቢ ውስጥ ምንም አይነት ሽያጭ እንደማይከናውን አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።

በሌላ በኩል፣ “ አእላፋት ዝማሬ ነጭ ልብስ ልበሱ ” ተብሏል በሚል ነጭ ልብስ በተጋነነ ዋጋ የሚቸበችቡ ሁነቱን የተከተሉ ነጋዴዎች ተስተውለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ነጭ ልብስ በውድ ወጋ እየተቸበቸበ ነው የሚል አስተያዬት እየተሰጠ ተስተውሏል፣ ለመርሀ ግብሩ ነጭ ልብስ ብቻ ለብሶ መምጣት ግዴታ ነው ? ሲል ለአዘጋጆቹ ጥያቄ አቅርቧል።

የኢትዮጵያው ጃንረባ ትውልድ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ብንያም አሕመድ በሰጡት ምላሽም፣ “ ነጭ ልብስ የሌለን ያለንን ልብስ ንጹህ አድርገን እንምጣ። ዓላማችን ልብሱ ለመቁረቢያ እንዲሆን ነው ” ብለዋል።

“ ኦርቶዶክሳዊ ኢኮኖሚ እንዲፈጠር ይፈለጋል ግልጽ ነው። በዚህ ምክንያት ወደ ስራ የሚገቡ፣ ሥራቸውን የሚያስፋፉ፣ የሚለወጡ ኦርቶዶክሳዊያን ቢኖሩ ይሄ የማኀበራችን አንዱ ዓላማ ነው ” ሲሉ ነው የተናገሩት።

“ ስለዚህ ይህን በቀና ዓይን ነው የምናየው ” ያሉት አቶ ብንያም፣ “ በእርግጥ በዚሁ ምክንያት ደግሞ አጋጣሚውን የሚጠቀሙ፣ Accidental Entrprenuers የምንላቸው መጥተው ባለሃብት ለመሆን የሚጥሩ ይኖራሉ ” ሲሉም አክለዋል።

“ ልደቱ የሰዎች የመላክት ዝማሬ ነው። ስለዚህ ይህንን በማሰብ ነጭ ለብሰን እንመጣለን ” ብለው፣ “ ዘወትር ወደ ቤተ ክርስቲያን ስንሄድ የምናደርገው ነው፣ የተለዬ ነገር የለውም ” ነው ያሉት።

ሆኖም ነጭ ልብስ የሌላቸው ያላቸውን ልብስ በአግባቡ ለብሰው በዝማሬ መርሀ ግብሩ መገኘታቸው እንዳይዘነጋ መልዕክት ተላልፏል። 

ዝማሬው ዘማሪያን እየዘመሩ ምዕመናን የሚቀበሉበት ሂደት ሳይሆን ልደቱን በሚያወሱ ዝማሬዎች ሁሉም በጋራ ምስጋና እንዲያቀርብ መሆኑ ተሰምሮበታል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA










Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93419

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In 2018, Russia banned Telegram although it reversed the prohibition two years later. At its heart, Telegram is little more than a messaging app like WhatsApp or Signal. But it also offers open channels that enable a single user, or a group of users, to communicate with large numbers in a method similar to a Twitter account. This has proven to be both a blessing and a curse for Telegram and its users, since these channels can be used for both good and ill. Right now, as Wired reports, the app is a key way for Ukrainians to receive updates from the government during the invasion. Recently, Durav wrote on his Telegram channel that users' right to privacy, in light of the war in Ukraine, is "sacred, now more than ever." The SC urges the public to refer to the SC’s I nvestor Alert List before investing. The list contains details of unauthorised websites, investment products, companies and individuals. Members of the public who suspect that they have been approached by unauthorised firms or individuals offering schemes that promise unrealistic returns The regulator said it has been undertaking several campaigns to educate the investors to be vigilant while taking investment decisions based on stock tips.
from kr


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American