Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " በየመዋቅሩ ያሉ ም/ቤቶች ጊዚያቸው ያለፈ እና ህጋዊ መሰረታቸው ያበቃ በመሆኑ መሾምና መሻር አይችሉም " ብሎ የነበረው የትግራይ  ክልልጊዚያዊ  አስተዳደር ምክር ቤቶቹ ህጋዊ መሰረት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ደንብ አፅድቀዋል። የጊዚያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ የወረዳ ምክር ቤቶች የሚያጠናክር እና ህጋዊ መሰረት እንዲኖራቸው የሚያደርግ ነው ያለውን ደንብ ከሰሞኑን አፅድቋል። " የፀደቀው ደንብ…
የትግራይ ጉዳይ ወዴት ?

በትግራይ ክልል ያሉ የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች እንደሆኑ የገለጹ መኮንኖች ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህም ' የተዳከመ ' ያሉት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ተነስቶ በሌላ እንዲዋቀር መወሰናቸውን ገልጸዋል።

" የጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደ አዲስ እንዲዋቀር ውሳኔ አሳልፈናል " ብለዋል።

" በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኃላፊነቱን በአግባቡ አልተወጣም የሌሎች መጠቀሚያ ሆኗል " የሚል  ክስም አቅርበዋል።

" በጊዜያዊ አስተዳደሩ ቁልፍ ሥልጣን የነበራቸው አመራር እና አባላት ከተሰጣቸው ተልዕኮ ውጪ የሕዝብን ጥቅም ወደ ጎን በመተው ክህደት በመፈጸም የውጭ ኃይል መሣሪያ ሆነዋል" ብሏል።

በሕዝብ ጥቅም ላይ ስለደረሰው ጉዳትም ሆነ " የውጭ ኃይል " ያሉት አካል ማንነትን በተመለከተ በግልጽ የተናገሩት ነገር የለም።

የወታደራዊ አመራሮቹ በሰጡት መግለጫ በስፋት ስለ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ድክመት ሲናገሩ የነበረ ሲሆን " የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም እየሞከረ ነው " የሚል ክስም አቅርበዋል።

ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ለተካሄደው (በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን) የህወሓት 14ኛ ጉባኤ እውቅና በመስጠት በጉባኤው ውሳኔ መሠረት የጊዜያዊ አስተዳደር የአመራሮች ለውጥ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

ይህንን ጉባኤ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች እውቅና እንደነፈጉት ይታወሳል።

ወታደራዊ አመራሮቹ " ህወሓት የትግራይን ጊዜያዊ አስተዳደር ለማሻሻል ያሳለፈው ውሳኔ በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲሆን " ያሉ ሲሆን " ሠራዊቱን ወክለው በጊዜያዊ አስተዳደሩ የካቢኔ አባላት የሆኑትን ግለሰቦች በመገምገም እምነት የሚጣልባቸው ያልሆኑትን በሌሎች እንዲተኩ ወስነናል " ብለዋል።

" ጊዜያዊ አስተዳደሩን በሠራዊቱ ላይ የሚካሄደውን የስም ማጥፋት ዘመቻን መከላከል አልቻለም " በሚል ' በክህደት ' ወንጅለውታል።

በአሁኑ ወቅት በትግራይ ውስጥ ያለው ችግር " ፖለቲካዊ መፍትሄ የሚሻ ነው " ያሉት አመራሮቹ " ማንኛውም ነገር ከትግራይ ሠራዊት አቅም በላይ አይደለም ይህንን ሰበብ በማድረግ የሚደረግ ጣልቃ ገብነትን አንቀበልም " ብለዋል።

አመራሮቹ በደብረፅዮን (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ቡድን በግዚያዊ አስተዳደር ያለው 50+1 ድርሻ እንዲረከብ እንደሚፈልጉ ተናግረዋን።

ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ ያሉ ታጣቂዎች በትግራይ ሰላም እና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ስር እንዲሆኑ፥ ከዚህ ውጪ በሆነ ላይ ግን እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።

ዛሬ መግለጫ የሰጡት የትግራይ ኃይሎች ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር እንደሆኑ የገለጹት መኮንኖቹ በግልጽ ለደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ቡድን ያደላ አቋም ይዘዋል ፤ ይህ ደግሞ አሁን ላይ በክልሉ ያለውን ሁኔታ አስፍሪ አድርጎታል የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡ መመልከት ችለናል።

ህወሓት በአቶ ጌታቸው ረዳ እና ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ለሁለት ተከፍሎ ላለፉት ወራት እጅግ በጣም በከረረ የመግለጫ እና የሚዲያ ምልልስ ላይ ሲሆን የታጣቂ ኃይሎች እስካሁን በክልሉ ጉዳይ በይፋ አቋማቸውን ሲገልጹ አልታዩም ፤ የዛሬው ለደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ያደላ የድጋፍ መግለጫ ጉዳዩ ወዴት ያመራ ይሆን ? የሚል ስጋት ደቅኗል።

ትግራይ በርካቶች ያለቁበትን እጅግ አስከፊ የሆነ ጦርነት አስተናግዳ ከህመሟ  ገና ያላገገማች ሲሆን አሁን በክልሉ ያለው መካረር መፍትሄ አለማግኘቱ ብዙዎችን እያሳዘነ ይገኛል።

#BBCTigrigna
#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93996
Create:
Last Update:

የትግራይ ጉዳይ ወዴት ?

በትግራይ ክልል ያሉ የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች እንደሆኑ የገለጹ መኮንኖች ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህም ' የተዳከመ ' ያሉት በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ተነስቶ በሌላ እንዲዋቀር መወሰናቸውን ገልጸዋል።

" የጊዜያዊ አስተዳደሩ እንደ አዲስ እንዲዋቀር ውሳኔ አሳልፈናል " ብለዋል።

" በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት የተቋቋመው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ኃላፊነቱን በአግባቡ አልተወጣም የሌሎች መጠቀሚያ ሆኗል " የሚል  ክስም አቅርበዋል።

" በጊዜያዊ አስተዳደሩ ቁልፍ ሥልጣን የነበራቸው አመራር እና አባላት ከተሰጣቸው ተልዕኮ ውጪ የሕዝብን ጥቅም ወደ ጎን በመተው ክህደት በመፈጸም የውጭ ኃይል መሣሪያ ሆነዋል" ብሏል።

በሕዝብ ጥቅም ላይ ስለደረሰው ጉዳትም ሆነ " የውጭ ኃይል " ያሉት አካል ማንነትን በተመለከተ በግልጽ የተናገሩት ነገር የለም።

የወታደራዊ አመራሮቹ በሰጡት መግለጫ በስፋት ስለ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ድክመት ሲናገሩ የነበረ ሲሆን " የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም እየሞከረ ነው " የሚል ክስም አቅርበዋል።

ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ለተካሄደው (በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ቡድን) የህወሓት 14ኛ ጉባኤ እውቅና በመስጠት በጉባኤው ውሳኔ መሠረት የጊዜያዊ አስተዳደር የአመራሮች ለውጥ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

ይህንን ጉባኤ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች እውቅና እንደነፈጉት ይታወሳል።

ወታደራዊ አመራሮቹ " ህወሓት የትግራይን ጊዜያዊ አስተዳደር ለማሻሻል ያሳለፈው ውሳኔ በአስቸኳይ ተግባራዊ እንዲሆን " ያሉ ሲሆን " ሠራዊቱን ወክለው በጊዜያዊ አስተዳደሩ የካቢኔ አባላት የሆኑትን ግለሰቦች በመገምገም እምነት የሚጣልባቸው ያልሆኑትን በሌሎች እንዲተኩ ወስነናል " ብለዋል።

" ጊዜያዊ አስተዳደሩን በሠራዊቱ ላይ የሚካሄደውን የስም ማጥፋት ዘመቻን መከላከል አልቻለም " በሚል ' በክህደት ' ወንጅለውታል።

በአሁኑ ወቅት በትግራይ ውስጥ ያለው ችግር " ፖለቲካዊ መፍትሄ የሚሻ ነው " ያሉት አመራሮቹ " ማንኛውም ነገር ከትግራይ ሠራዊት አቅም በላይ አይደለም ይህንን ሰበብ በማድረግ የሚደረግ ጣልቃ ገብነትን አንቀበልም " ብለዋል።

አመራሮቹ በደብረፅዮን (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ቡድን በግዚያዊ አስተዳደር ያለው 50+1 ድርሻ እንዲረከብ እንደሚፈልጉ ተናግረዋን።

ከዚህ በተጨማሪ በትግራይ ያሉ ታጣቂዎች በትግራይ ሰላም እና ፀጥታ ሴክሬታሪያት ስር እንዲሆኑ፥ ከዚህ ውጪ በሆነ ላይ ግን እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል።

ዛሬ መግለጫ የሰጡት የትግራይ ኃይሎች ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር እንደሆኑ የገለጹት መኮንኖቹ በግልጽ ለደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ቡድን ያደላ አቋም ይዘዋል ፤ ይህ ደግሞ አሁን ላይ በክልሉ ያለውን ሁኔታ አስፍሪ አድርጎታል የሚሉ አስተያየቶች ሲሰጡ መመልከት ችለናል።

ህወሓት በአቶ ጌታቸው ረዳ እና ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ለሁለት ተከፍሎ ላለፉት ወራት እጅግ በጣም በከረረ የመግለጫ እና የሚዲያ ምልልስ ላይ ሲሆን የታጣቂ ኃይሎች እስካሁን በክልሉ ጉዳይ በይፋ አቋማቸውን ሲገልጹ አልታዩም ፤ የዛሬው ለደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ያደላ የድጋፍ መግለጫ ጉዳዩ ወዴት ያመራ ይሆን ? የሚል ስጋት ደቅኗል።

ትግራይ በርካቶች ያለቁበትን እጅግ አስከፊ የሆነ ጦርነት አስተናግዳ ከህመሟ  ገና ያላገገማች ሲሆን አሁን በክልሉ ያለው መካረር መፍትሄ አለማግኘቱ ብዙዎችን እያሳዘነ ይገኛል።

#BBCTigrigna
#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA







Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93996

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In a statement, the regulator said the search and seizure operation was carried out against seven individuals and one corporate entity at multiple locations in Ahmedabad and Bhavnagar in Gujarat, Neemuch in Madhya Pradesh, Delhi, and Mumbai. The last couple days have exemplified that uncertainty. On Thursday, news emerged that talks in Turkey between the Russia and Ukraine yielded no positive result. But on Friday, Reuters reported that Russian President Vladimir Putin said there had been some “positive shifts” in talks between the two sides. Soloviev also promoted the channel in a post he shared on his own Telegram, which has 580,000 followers. The post recommended his viewers subscribe to "War on Fakes" in a time of fake news. The account, "War on Fakes," was created on February 24, the same day Russian President Vladimir Putin announced a "special military operation" and troops began invading Ukraine. The page is rife with disinformation, according to The Atlantic Council's Digital Forensic Research Lab, which studies digital extremism and published a report examining the channel. "There are several million Russians who can lift their head up from propaganda and try to look for other sources, and I'd say that most look for it on Telegram," he said.
from kr


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American