Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴 " ዩኒቨርሲቲያችን እንደ ሁሉም የሀገራችን ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም ነዉ " - የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ➡️ " ወደ ዩኒቨርሲቲዉ ቅጥር ግቢ እንዳንገባ ተደርገናል በዚህም ምክንያት በሁለት መስጊዶች ተጠልለን እንገኛለን " - ሙስሊም ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት የእስልምና እምነት ተከታይ / ሙስሊም…
#Update

“ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባሳቸው ሳቢያ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከላቸው፣ ከትምህርት፣ ከካፌና ከማደሪያ ውጪ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው አይዘነጋም፡፡

ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል፣ " 44 ሴት ተማሪዎችን ጥቁር ማስክ አድርጋችሁ 'አናስገባም' ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን " ነበር ያሉት።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው ዩኒቨርሲቲው፣ እንደ ሁሉም የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም እንደሆነና ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ እንዳልተከለከለ ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ እንደማይደረግ ገልጾ ነበር።

ተማሪዎቹ ግቢ እንዲገቡ ተፈቀዳላቸው ?

ወደ ግቢ ገባችሁ ወይስ አሁንም ከግቢ ውጪ ናችሁ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ተማሪዎቹ፣ " ለጊዜው ከስምምንት ተደርሷል " ሲሉ መልሰዋል።

" በተወካዮቻችን በኩል ኒቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰን መግባት እንደምንችል ተነገረንና ትላንት ገብተናል " ብለዋል።

በስምምነቱ መሰረት ለብሰው እንዲገቡ ከመነገራቸው ውጪ ሌላ የተባሉት ነገር እንደሌለ አስረድተው፣ " ለጊዜው ግን ግቢ ገብተናል " ነው ያሉት፡፡

በደብዳቤ ጭምር በመጠየቅ ጉዳያቸውን ሲከታተል የቆየውን የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትንም ግቢ እንደይገቡ ተከልክለው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢ ገብተዋል ? ስንል ጠይቀናል፡፡

የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምን አለ ?

" በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል፡፡

በዘላቂነቱ ላይ እንደ አገር የሚያዝ አቅጣጫ ይኖራል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ይሄ ነው ተብሎ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ሲጀመር ክልከለውን በተመለከተም በፅሑፍ የተገለጸ የለም፡፡ አሁን ሲፈቀድም በተመሳሳይ ነው፡፡

አገራችን የብዙ ሃይማኖቶችና ብሔሮች መገኛ ስለሆነች ስርዓቶችም ሃይማኖቶችን፣ ብሔር ብሔረሰቦችን ያማካሉ ቢሆኑ፤ ለአንዱ እድል ሰጥቶ ሌላኛውን ያላገለሉ፣ ሃይማኖት ባሉ ነገሮች ምክንያት በሌሎች ቦታዎችም ሁሉን ያማከለ ሆነው ቢወጡ የተሻለ ነው፡፡

የጥብቅ ደን/ብዙ እፅዋቶችን አንድ ላይ ነው በማልማት የሚታወቀውና እንደ አገርም ቅርስ የተያዘለት ማህበረሰብ ያለበት ዩኒቨርሲቲም ስለሆነ ነገሮች ሲከናወኑ በዚያ ቢታሰቡ እጅግ መልካም ይሆናል
" ብሏል፡፡

የተደረሰውን ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ የዩኒቨርሲቲው አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው ሃሳባቸውን ማካተት አልተሳካም፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94118
Create:
Last Update:

#Update

“ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባሳቸው ሳቢያ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከላቸው፣ ከትምህርት፣ ከካፌና ከማደሪያ ውጪ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው አይዘነጋም፡፡

ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል፣ " 44 ሴት ተማሪዎችን ጥቁር ማስክ አድርጋችሁ 'አናስገባም' ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን " ነበር ያሉት።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው ዩኒቨርሲቲው፣ እንደ ሁሉም የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም እንደሆነና ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ እንዳልተከለከለ ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ እንደማይደረግ ገልጾ ነበር።

ተማሪዎቹ ግቢ እንዲገቡ ተፈቀዳላቸው ?

ወደ ግቢ ገባችሁ ወይስ አሁንም ከግቢ ውጪ ናችሁ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ተማሪዎቹ፣ " ለጊዜው ከስምምንት ተደርሷል " ሲሉ መልሰዋል።

" በተወካዮቻችን በኩል ኒቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰን መግባት እንደምንችል ተነገረንና ትላንት ገብተናል " ብለዋል።

በስምምነቱ መሰረት ለብሰው እንዲገቡ ከመነገራቸው ውጪ ሌላ የተባሉት ነገር እንደሌለ አስረድተው፣ " ለጊዜው ግን ግቢ ገብተናል " ነው ያሉት፡፡

በደብዳቤ ጭምር በመጠየቅ ጉዳያቸውን ሲከታተል የቆየውን የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትንም ግቢ እንደይገቡ ተከልክለው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢ ገብተዋል ? ስንል ጠይቀናል፡፡

የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምን አለ ?

" በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል፡፡

በዘላቂነቱ ላይ እንደ አገር የሚያዝ አቅጣጫ ይኖራል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ይሄ ነው ተብሎ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ሲጀመር ክልከለውን በተመለከተም በፅሑፍ የተገለጸ የለም፡፡ አሁን ሲፈቀድም በተመሳሳይ ነው፡፡

አገራችን የብዙ ሃይማኖቶችና ብሔሮች መገኛ ስለሆነች ስርዓቶችም ሃይማኖቶችን፣ ብሔር ብሔረሰቦችን ያማካሉ ቢሆኑ፤ ለአንዱ እድል ሰጥቶ ሌላኛውን ያላገለሉ፣ ሃይማኖት ባሉ ነገሮች ምክንያት በሌሎች ቦታዎችም ሁሉን ያማከለ ሆነው ቢወጡ የተሻለ ነው፡፡

የጥብቅ ደን/ብዙ እፅዋቶችን አንድ ላይ ነው በማልማት የሚታወቀውና እንደ አገርም ቅርስ የተያዘለት ማህበረሰብ ያለበት ዩኒቨርሲቲም ስለሆነ ነገሮች ሲከናወኑ በዚያ ቢታሰቡ እጅግ መልካም ይሆናል
" ብሏል፡፡

የተደረሰውን ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ የዩኒቨርሲቲው አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው ሃሳባቸውን ማካተት አልተሳካም፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA






Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94118

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The Securities and Exchange Board of India (Sebi) had carried out a similar exercise in 2017 in a matter related to circulation of messages through WhatsApp. Just days after Russia invaded Ukraine, Durov wrote that Telegram was "increasingly becoming a source of unverified information," and he worried about the app being used to "incite ethnic hatred." Given the pro-privacy stance of the platform, it’s taken as a given that it’ll be used for a number of reasons, not all of them good. And Telegram has been attached to a fair few scandals related to terrorism, sexual exploitation and crime. Back in 2015, Vox described Telegram as “ISIS’ app of choice,” saying that the platform’s real use is the ability to use channels to distribute material to large groups at once. Telegram has acted to remove public channels affiliated with terrorism, but Pavel Durov reiterated that he had no business snooping on private conversations. Two days after Russia invaded Ukraine, an account on the Telegram messaging platform posing as President Volodymyr Zelenskiy urged his armed forces to surrender.
from kr


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American