Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ሰባት

እጁን ዘርግቶ የተራቆተ እግሯን ሸፈነላት። ምን ነካኝ? አለ ራሱን ቆጣ ብሎ። የተገተረበትን ቦታ ለቆ ወደ መኝታ ቤቱ አመራና አልጋው ላይ ተወረወረ። ጎጃምን ለቆ ሲወጣ የሚያስታውሰው ነገር የለም። በዛን ጊዜ በጣም ልጅ ነበረ። ነገሮች ተረስተውታል። አንድ የማይረሳው ነገር ግን አለ። ታናሽ ወንድሙ እዮብ። በሁለት አመት ውስጥ አከታትላ የወለደቻቸው እናታቸው የ አራት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች እናት ናት። የእድሜ ልዩነታቸው ብዙም ስላይደለ እዮብና አልአዛር መንታ ይመስላሉ።

አባታቸው በእናታቸው ላይ የሚያደርሰውን ግፍ ማየት የሚችልበት ጥንካሬ ስላጣ አንድ ቀን ወንድሙ እዮብን ብቻ ተሰናብቶ ጎጃምን ለቀቀ። ለቀቀ የሚለው ቃል አልአዛር እዚህ ቦታ ለመድረስ ያየው መከራና ጊዜ ባይገልፀውም እንዲሁ ለቀቀ ይባል። የወሰደበት ጊዜ ረጅም ነው ምን አልባትም የእድሜውን እኩሌታ ያህላል።

እዮብ ወደእዚህ አገር ሲመጣ አልአዛር ትንሽ ሱቅ ከፍቶ በመነገድ ላይ ነበር። የስጋ ነገር ሆነና እንደገና ለመገናኘት ዝምድናቸውንም ለማደስ ጊዜ አልፈጀባቸውም። እዮብ አዲስ አበባ ሲመጣ እናታቸው ሆነ አባታቸው ወንድም እህቶቻቸው በወረርሽኝ አልቀው ነበር። ብቻውን የቀረው አንድ እዮብም የተመደበበት ወደነበረው ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ በጎጃም የቀረው አንድም ቤተሰብ የለም። ሁሉም አልቀዋል። ለዚህም ተጠያቂው በምንቸገረኝነት ከዳር ሆኖ ሲመለከት የነበረው መንግስት ለመሆኑ ደምድሟል።

ልቡ በቀልን እንዳረገዘ ዩኒቨርስቲውን ተቀላቀለ። ከአንድ ወር በኃላም በልጅነቱ የተለየውን ወንድሙን አገኘና የብቸኝነቱን ስቃይ መቋቋም ቻለ። የእዮብና የአልአዛር ገበያ ግንኙነት በሚስጥር እንዲሆን ሀሳብ ያቀረበው እዮብ ነበር። አልአዛር ከአገሩ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን ስም ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። "አንተነህ" ምን አይነት አስቀያሚ ስም ነው ሲል አሰበ። ገና አዲስ አበባ እንደገባ ወደ አልአዛር ቀየረ። ወንድማማቾቹ በእረፍት ቀናቸው በድብቅ ተገናኝተው ይወያያሉ። በመካከላቸው የነበረው ፍቅር ጠንካራ ነው። አልአዛር ወሩንና ቀኑን ባያስታውሰውም ብቻ የሆነ ቀን ወንድሙ እዮብ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ወደ እሱ ሲሮጥ ተመለከተ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጉቶ ስለነበር የእዮብ ትንፋሽ መለስ እስኪል ራሱ አልጠበቀም። ምን እንደሆነ ለማወቅ በጥያቄ ያጣድፈው ጀመር።

ፍቅር ይዞኛል! አለው ከእሱ መፍትሔ ያገኝ ይመስል። ታዲያ ምን ችግር አለው? አለ አልአዛር በፍቅር መያዝ እንዲህ ወንድሙን ያስጨነቀበት ምክንያት አልገባሁም። ባክህ አድምጠኝ አለ እዮብ የወንድሙ ቸልታ ቅር አሰኝቶት። የተማሪዎች ህብረት አባል ነኝ። ልጅቷም እንዲሁ አለ እዮብ ከወንድሙ የደበቀውን ሚስጥር ማጋለጡ እያስፈራው።

አልአዛር ስጋቱ እውን ሆኖ ሲያየው የሚያደርገውን አሳጣው። ድሮውኑ የወንድሙን ቆራጥነት ያውቀዋል። የህብረቱ አባል መሆን ማለት ራስን በሸምቀቆ ወደተዘጋጀ ገመድ ማስገባት ማለት ነው። የእዮብን ግትር ውሳኔ ማስቀረት ፍፁም እንደማይቻለው ስለተገነዘበ በሀዘን አንገቱን አቀርቅሮ ዝምታን መረጠ።

አሊ አንድ ነገር በል እንጂ! አለ እዮብ የወንድሙን ዝምታ ጠልቶ። ምን ልበልህ? ራስህን ለሞት አሳልፈህ ስትሰጥ ዳር ሆኖ ከመመልከት ውጪ ምን አይነት ምርጫ አለኝ? አለ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ። ከተል አድርጎም ነግረአታል? አለ አልአዛር ንግግሩ ህይወት አልባ ነበር። አልነገርኳትም ልነግራትም አልፈልግም። የህብረቱ አባል እንዳትሆን ያላዴግኩት ጥረት አልነበረም ሊሳካልኝ አልቻለም እንጂ።

ህብረታችን በቅርቡ በመንግስት ሀይል ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅት አድርጓል። በዚህ ነገር ላይ እንዳትሳተፍ ብፈልግም ቁርጠኛ ሀሳቧን ማስቀየር የማይቻል ነገር ነው። ይህንን ለወንድሙ መንገሩ እፎይታን ሰጥቶታል። አልአዛር ግራ ተጋብቶ ወንድሙ ላይ አሁንም እንዳፈጠጠ ነው። እርዳታ ሲያሻት ወደ አንተ ትመጣለች። ለእኔ ስትል እንዳታሳፍራት። አለ ታላቅ ወንድሙን እያየ። ብሌንን አደራ መስጠቱ አርክቶታል። ፍቅሩ በአስተማማኝ እጆች ላይ ትሆናለች። ይህ ደግሞ ለእሱ ትልቅ ረፍት ነው። የልቡን አውጥቶ መንገር አለመፈለጉ የብሌንን እሺታን አልያም እምቢታን ማወቅ የለመፈለጉ ምክንያት ለአልአዛር አልተገለጠለትም።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/122
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ሰባት

እጁን ዘርግቶ የተራቆተ እግሯን ሸፈነላት። ምን ነካኝ? አለ ራሱን ቆጣ ብሎ። የተገተረበትን ቦታ ለቆ ወደ መኝታ ቤቱ አመራና አልጋው ላይ ተወረወረ። ጎጃምን ለቆ ሲወጣ የሚያስታውሰው ነገር የለም። በዛን ጊዜ በጣም ልጅ ነበረ። ነገሮች ተረስተውታል። አንድ የማይረሳው ነገር ግን አለ። ታናሽ ወንድሙ እዮብ። በሁለት አመት ውስጥ አከታትላ የወለደቻቸው እናታቸው የ አራት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች እናት ናት። የእድሜ ልዩነታቸው ብዙም ስላይደለ እዮብና አልአዛር መንታ ይመስላሉ።

አባታቸው በእናታቸው ላይ የሚያደርሰውን ግፍ ማየት የሚችልበት ጥንካሬ ስላጣ አንድ ቀን ወንድሙ እዮብን ብቻ ተሰናብቶ ጎጃምን ለቀቀ። ለቀቀ የሚለው ቃል አልአዛር እዚህ ቦታ ለመድረስ ያየው መከራና ጊዜ ባይገልፀውም እንዲሁ ለቀቀ ይባል። የወሰደበት ጊዜ ረጅም ነው ምን አልባትም የእድሜውን እኩሌታ ያህላል።

እዮብ ወደእዚህ አገር ሲመጣ አልአዛር ትንሽ ሱቅ ከፍቶ በመነገድ ላይ ነበር። የስጋ ነገር ሆነና እንደገና ለመገናኘት ዝምድናቸውንም ለማደስ ጊዜ አልፈጀባቸውም። እዮብ አዲስ አበባ ሲመጣ እናታቸው ሆነ አባታቸው ወንድም እህቶቻቸው በወረርሽኝ አልቀው ነበር። ብቻውን የቀረው አንድ እዮብም የተመደበበት ወደነበረው ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ በጎጃም የቀረው አንድም ቤተሰብ የለም። ሁሉም አልቀዋል። ለዚህም ተጠያቂው በምንቸገረኝነት ከዳር ሆኖ ሲመለከት የነበረው መንግስት ለመሆኑ ደምድሟል።

ልቡ በቀልን እንዳረገዘ ዩኒቨርስቲውን ተቀላቀለ። ከአንድ ወር በኃላም በልጅነቱ የተለየውን ወንድሙን አገኘና የብቸኝነቱን ስቃይ መቋቋም ቻለ። የእዮብና የአልአዛር ገበያ ግንኙነት በሚስጥር እንዲሆን ሀሳብ ያቀረበው እዮብ ነበር። አልአዛር ከአገሩ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን ስም ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። "አንተነህ" ምን አይነት አስቀያሚ ስም ነው ሲል አሰበ። ገና አዲስ አበባ እንደገባ ወደ አልአዛር ቀየረ። ወንድማማቾቹ በእረፍት ቀናቸው በድብቅ ተገናኝተው ይወያያሉ። በመካከላቸው የነበረው ፍቅር ጠንካራ ነው። አልአዛር ወሩንና ቀኑን ባያስታውሰውም ብቻ የሆነ ቀን ወንድሙ እዮብ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ወደ እሱ ሲሮጥ ተመለከተ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጉቶ ስለነበር የእዮብ ትንፋሽ መለስ እስኪል ራሱ አልጠበቀም። ምን እንደሆነ ለማወቅ በጥያቄ ያጣድፈው ጀመር።

ፍቅር ይዞኛል! አለው ከእሱ መፍትሔ ያገኝ ይመስል። ታዲያ ምን ችግር አለው? አለ አልአዛር በፍቅር መያዝ እንዲህ ወንድሙን ያስጨነቀበት ምክንያት አልገባሁም። ባክህ አድምጠኝ አለ እዮብ የወንድሙ ቸልታ ቅር አሰኝቶት። የተማሪዎች ህብረት አባል ነኝ። ልጅቷም እንዲሁ አለ እዮብ ከወንድሙ የደበቀውን ሚስጥር ማጋለጡ እያስፈራው።

አልአዛር ስጋቱ እውን ሆኖ ሲያየው የሚያደርገውን አሳጣው። ድሮውኑ የወንድሙን ቆራጥነት ያውቀዋል። የህብረቱ አባል መሆን ማለት ራስን በሸምቀቆ ወደተዘጋጀ ገመድ ማስገባት ማለት ነው። የእዮብን ግትር ውሳኔ ማስቀረት ፍፁም እንደማይቻለው ስለተገነዘበ በሀዘን አንገቱን አቀርቅሮ ዝምታን መረጠ።

አሊ አንድ ነገር በል እንጂ! አለ እዮብ የወንድሙን ዝምታ ጠልቶ። ምን ልበልህ? ራስህን ለሞት አሳልፈህ ስትሰጥ ዳር ሆኖ ከመመልከት ውጪ ምን አይነት ምርጫ አለኝ? አለ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ። ከተል አድርጎም ነግረአታል? አለ አልአዛር ንግግሩ ህይወት አልባ ነበር። አልነገርኳትም ልነግራትም አልፈልግም። የህብረቱ አባል እንዳትሆን ያላዴግኩት ጥረት አልነበረም ሊሳካልኝ አልቻለም እንጂ።

ህብረታችን በቅርቡ በመንግስት ሀይል ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅት አድርጓል። በዚህ ነገር ላይ እንዳትሳተፍ ብፈልግም ቁርጠኛ ሀሳቧን ማስቀየር የማይቻል ነገር ነው። ይህንን ለወንድሙ መንገሩ እፎይታን ሰጥቶታል። አልአዛር ግራ ተጋብቶ ወንድሙ ላይ አሁንም እንዳፈጠጠ ነው። እርዳታ ሲያሻት ወደ አንተ ትመጣለች። ለእኔ ስትል እንዳታሳፍራት። አለ ታላቅ ወንድሙን እያየ። ብሌንን አደራ መስጠቱ አርክቶታል። ፍቅሩ በአስተማማኝ እጆች ላይ ትሆናለች። ይህ ደግሞ ለእሱ ትልቅ ረፍት ነው። የልቡን አውጥቶ መንገር አለመፈለጉ የብሌንን እሺታን አልያም እምቢታን ማወቅ የለመፈለጉ ምክንያት ለአልአዛር አልተገለጠለትም።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/122

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The gold standard of encryption, known as end-to-end encryption, where only the sender and person who receives the message are able to see it, is available on Telegram only when the Secret Chat function is enabled. Voice and video calls are also completely encrypted. At its heart, Telegram is little more than a messaging app like WhatsApp or Signal. But it also offers open channels that enable a single user, or a group of users, to communicate with large numbers in a method similar to a Twitter account. This has proven to be both a blessing and a curse for Telegram and its users, since these channels can be used for both good and ill. Right now, as Wired reports, the app is a key way for Ukrainians to receive updates from the government during the invasion. Given the pro-privacy stance of the platform, it’s taken as a given that it’ll be used for a number of reasons, not all of them good. And Telegram has been attached to a fair few scandals related to terrorism, sexual exploitation and crime. Back in 2015, Vox described Telegram as “ISIS’ app of choice,” saying that the platform’s real use is the ability to use channels to distribute material to large groups at once. Telegram has acted to remove public channels affiliated with terrorism, but Pavel Durov reiterated that he had no business snooping on private conversations. Telegram boasts 500 million users, who share information individually and in groups in relative security. But Telegram's use as a one-way broadcast channel — which followers can join but not reply to — means content from inauthentic accounts can easily reach large, captive and eager audiences. Apparently upbeat developments in Russia's discussions with Ukraine helped at least temporarily send investors back into risk assets. Russian President Vladimir Putin said during a meeting with his Belarusian counterpart Alexander Lukashenko that there were "certain positive developments" occurring in the talks with Ukraine, according to a transcript of their meeting. Putin added that discussions were happening "almost on a daily basis."
from kr


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American