Telegram Group & Telegram Channel
❤️ም.. ኞ.....ት

🔥ክፋል 51
.
.
#የመጨረሻ ክፍል
.
.
ድንገት መካከላቸው ወጣ ገባ ስትል የነበረች አንዲት መኪና አቅጣጫ ቀይራ ከመሀላቸው ስትወጣ ሚኪ ዞሮ መኪናዋን የሚያሽከረክረው መሳይ መሆኑን ሲመለከት በድንጋጤ እየጮኽ
ፅናት መንገድ መንገድ ዘግታ እንድታስቆመው አደረገ። መሳይም በሁኔታው እየተደነባበረ ከመኪናው ወርዶ ሮጦ ከመጣው ሚኪ ጋር ተቃቀፈ። ተያይዘው ወደ አንድ ሆቴል በማምራት እንዴት ነገሮች ተቀይረው ለዚህ እንደበቃ እየጠየቀው በመሀል የፅናት ስልክ ጠራ ። ከቦርሳዋ ውስጥ አውጥታ ተመለከተችው። ፊቷ ተለዋወጠ።
" ይኼ የማያፍር ሰይጣን ደግሞ ስልኬ ይደውላል እንዴ!" ብላ ስልኩን በመዝጋት በንዴት ስትንጨረጨር ከመሳይ ጋር የጀመረውን ጫወታ አቋርጦ•••
"ማነው ፅኑዬ?
" ያ ብሩክ ተብየው ነዋ!"
"ተይው አትበሳጪ ስራው ካንቺ በላይ እኔን ማበሳጨት እንደነበረበት አውቃለሁ። ግን ደነዘዝኩ ባንዱ ጉዳት የተሰበረው ልብሽ ሳይጠገን በጉዳት ላይ ጉዳት ሲደራረብብሽ የመበሳጨትም
አቅም ያጥርሽና ትደነዝዣለሽ። እንደ ብሩኬ አይነት ሰዎች ብዙ ናቸው። ሲበዛ እራስ ወዳዴች ከመሆናቸው የተነሳ አንቺ ችግር ውስጥ ስትገቢ ከዛ ችግር እንድትወጪ ከመርዳት ይልቅ
-በችግርሽ
-በእጦትሽ
-በስጋት እና በፍርሀትሽ
ሁሉ ተጠቅመው አንቺን እንዴት አድርገው ለፍላጎትና ለጥቅማቸው መሳካት እንደሚጠቀምቡሽ ነው የሚያስቡት።
ብሩኬም እንደዚሁ ነው ያደረገው። በምኞት ላይ በፈፀምኩት ክህደትና በደል ከባድ ፀፀት ውስጥ መውደቄን በፀፀት ውስጥ ባገረሸው ፍቅሯ መጎዳቴንና የትም አለች ቢሉኝ እሷን ለማግኘት የማልወጣው ተራራ የማልፈነቅለው ድንጋይ አለመኖሩን ሲረዳ ሰው ቢሆን ኖሮ አጠገቤ ሆኖ ጉዳቴን በተጎዳ። ፍቅሬን ምኞቴን ፀፀቴን እንዳገኛት ከጎኔ ሆኖ በደከመ። ግን እሱ ሰው ቢሆንም
እንደሰው እየኖረ አልነበረምና የኔን መጥፎ አጋጣሚ እራሱን ጠቅሞ እኔን ለመጉዳት ተጠቀመበት አንድ ያለችኝ መፅናኛ እህቴን አንቺን ሊያሳጣኝ ተሯሯጠ። ፈጣሪም ሩጫውን ገታው። ሀሳቡ ሳይሳካ መንገድ ላይ አስቀረው። የኔ ምኞት ግን ጠፍታ አትቀርም!"
አለና እንባ ያቀረሩ አይኖቹን ጨምቆ አቀረቀረ። መሳይ ሚኪ ያወራውን ሲሰማ በተቀመጠበት ልቡ መምታት ያቆመች መሰለው ምድርና ሰማዩ ተገለባበጠበት።
በዛች ቅፅበት ምን እንደሚያወራ ፣ምን እንደሚል፣ ምን ማድረግ እንዳለበት ማወቅ ተሳነው!። ምኞት ታየችው የሚያጣት ሚኪ የሚወስድበት መሰለው። ብድግ ብሎ ወደ ሽንት ቤት ለመሄድ አሰበና ጭንቅላቱ ውስጥ የተፈጠረው ውጥረት፣ፍጭት እና ጩኸት ገና ከወንበሩ ሲነሳ አዙሮ የሚደፋው መሰለውና መነሳቱን አልደፈረም።
እዛው በተቀመጠበት በሁለት እጆቹ ፊቱን ሸፍኖ እሱም እንደሚኪ አቀረቀረ።
መሀላቸው ቁጭ ያለችው ፅናት ብሩክ ሲደውል የተንቀለቀለው ንዴቷ ጠፍቶ በረዶ ሆነች። የሁለቱንም ስሜት በየተራ እየተመለከተች ነበርና ሚኪ ባውራው
ነገር መሳይ ለእብደት የዳረገውን ያለፈ መጥፎ የፍቅር ሂወቱን አስቦ የተረበሸ መሰላት ። "እባክህ ሚኪ እንደዚህ አትሁን እሱንም ረበሽከው እኮ! እባክህ
ተረጋጋ!" ብላው ደሞ ወደ መሳይ ዞራ "ድንገት አግኝተንህ ማሰብ የማትፈልገውን መጥፎ ትዝታህን ስለቀሰቀስንብህ ይቅርታ እባክህ
አትረበሽ። መሳይ ለፅናት መልስም አልሰጣትም። ቀናም አላለም።
ግራ ሲገባት ወደ ሚኪ ተጠግታ ገና ሚኪዬ ብሏ እንደተጣራች ሚኪ ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ድፍት ያለውን መሳይን እየተመለከተ•••
"ከሁሉም ነገር በፊት ትልቅ ይቅርታ እጠይቅሀለሁ መሳይ ወንድሜ! ይቅርታ የምጠይቅህ ግን ዛሬ ስለረበሽኩ ሳይሆን ለቆየ በደሌ ነው። በደሌ ምን እንደሆነና ለምን ይቅር በለኝ እንዳልኩህ ኑዛዜየን ስጨርስ ትረዳዋለህ። "አዋ ዛሬ ትክክለኛው ቀን ነው ከዚህ በፊት ብዙ ግዜ አግኝቼህ ሊሆን ይችላል። ፍቅርህን ናርዶስን ከማጣትህ በፊትም እሷን
አጥተህ ልክ እኔ ዛሬ ቀን እንደጨለመብኝ በቀን ጨለማ ተውጠኽም እንዳገኘሁኽ አስታውሳለሁ። ግን መጎዳትህን አየሁ እንጂ ጉዳትህን አልተጎዳሁትም ነበር።
በፍቅር ህመም ክፉኛ መታመምህን ተመለከትኩ እንጂ ህመምህን አልታመምኩትም ነበር። ካጠገብህ ዘወር ስል እረሳዋለሁ። ያንተ እንደዛ መሆን አይገባኝም፣ አያስጨንቀኝም፣ አይቆረቁረኝም። ዛሬ ግን ሕመምኽን ታምሜዋለሁና ጉዳትህን ተጎድቼዋለሁና ልክ እንዳየሁኽ ስላንተና ስለናርዶስ የማውቀውን ሚስጥር ሳልነግርህ
ማለፍ አልቻልኩም። አቃተኝ። ሚኪ ስለፍቅረኛው ናርዶስ እኔ የማላውቀውን ሚስጥር ይነግረኛል ብሎ አልጠበቀምና ስለምኞት እያሰበ እሱን ከማድመጥ ውጪ ቀናም አላለም።
"መሳይ ወላጅ አባትህ ጓደኛዬ ነው እሱን ይቅር የማለት እና ያለማለት ያንተ ፋንታ ነው ለኔ ግን ሁለቱም ጓደኛቼ አንድ አይነት
ሰይጣኖች ናቸው አባትህ እና ብሩኬ!" አለ። እኼን ግዜ እንኳንስ የመሳይ የፅናት የልብ ትርታ እጥፍ ሆነ ሚኪ ምን ሊያወራ ነው ብላ ሁሉ ነገሯ ስራ ፈትቶ ሚኪ ላይ ተተከለች። መሳይ "ይኼ ሰው ደሞ ምን ሊያሰማኝ ነው ፈጣሪዬ እባክህ የምችልበትን አቅም ስጠኝ። አለ አንገቱን እንደደፋ ፍርሀት ከላይ እስከታች እየናጠው። ሚኪ ቀጠለ••• " አባትህ ከናርዶስ ጋር የነበረኽን የፍቅር ግኑኝነት በጭራሽ አይፈልገውም ነበር።
ይኽን አንተም ታውቀዋለኽ። ናርዶስን ያልፈለጋት ያጠፋችው ወይ ያጎደለችው ነገር ስለነበር አይደለም። ጥፋቷም ጉድለቷም ድሃ መኾኗ : ከድሃ ቤተሰብ መፈጠሯ ብቻ ነበር። በአባትህ አይን ይቺ ያንተ ድሃዋ ናርዶስ እሱ ሊድርህ ለፈለገው ሰው እንዳይድርኽ መዃል የገባች የፍላጎቱ ፀር የእቅዱ ጠንቅ
ነበረች።

ይሄን ግዜ መሳይ ካቀረቀረበት ቀና እለና ሚኪ ላይ አፈጠጠበት ። አይኖቹ ደም ለብሰዋል። ፅናት መሳይን ስትመለከተው ጥርሶቹ እርስ በርሳቸው እየተፋጩ ነው።
ፈራች መሳይ እብደቱ የጀመረው መሰላት "ሚኪ አብደሃል ምንድን ነው የምታወራው ተነስ በቃ እንሂድ !" አለች ብድግ ብላ ቀና ብሎ እየተመለከታት"የትም አልሄድምም! አላበድኩምም!
ያበድኩት ይሄን እውነት እያወቅኩ ሳልቃወም እውነቱን ደብቄ ለመሳይ እብደት ተባባሪ የሆንኩ እለት ነበር ፅናቴ ። እባክሽ አታቋርጭኝ! "ቀጠለ•••
" እናም ይቺን የእቅዱ ጠንቅ የሆነችውን ናርዶስን በዘበኝነት ተቀጥረው እየሰሩ እንደ እናትም እንደ አባትም ሆነው ባሳደጓት በአባቷ መጣባት። ለአቧታ ያላትን ፍቅር ለመግለፅ ቃላት ለሚያጥሯት ናርዶስ ! አባቷን በሸረበው ተንኮል ወንጀል ውስጥ መግባታቸውን መስማት ከባድ ነበር። አባቷ እስር ቤት ገብተው እንዲማቅቁ የማትፈልግ ከሆነ
አንተን እስከመጨረሻው ትታ እሱ ወደ ሚላት ቦታ ጨርቄን ማቄን ሳትል መሄድ እንዳለባት ሲጠይቃት ምርጫ አልነበራትምና ተስማማች። "
መሳይ በዛን ግዜ የነበረው የአባቱ ሁኔታ በሙሉ ፊቱ ተደቀነበት ከእናቱ ሞት ቡሀላ የህይወቱን መራር ለቅሶ እያለቀሰ " እባክህ ወዴት እንደወሰዳት የት እንዳስቀመጣት ንገረኝ ሚኪ!" ፅናትም ሚኪም አብረውት አነቡ። ሚኪ ብድግ ብሎ ወደ መሳይ በመሄድ "እራስህን አረጋጋ መሳይ ወንድሜ ከዚህ ሰአት ቡኻላ በፈለግከው ሰአት ያንተ ናርዶስ ወዳለችበት ልወስድህ ዝግጁ ነኝ!! አንድ ቀን እንዲህ በአጋጣሚ እኔንም የኔ ምኞት ወዳለችበት ቦታ የሚወስደኝ ሰው ይልክልኝ ይሆናል ፈጣሪ !!" አለው።
መሳይ ውስጡ ያለውን የተደበላለቀ ስሜት መረዳት ከበደው ተነስቶ ሚኪን አቅፎት ለሰከንዶች ቆየና ለቆት ወደ ሆቴሉ መታጠቢያ ቤት አመራ ። መታጠቢያ ቤት ገብቶ እራሱን
በመስታወት እየተመለከተ ሚኪ ይቅር በለኝ ምን ማለት እንዳለብኝ እና እንደሌለብኝ መለየት አልቻልኩም ። ለምን ይሆን ስለምኞት

ላንተ ለመንገር አቅም



group-telegram.com/bookstorej/284
Create:
Last Update:

❤️ም.. ኞ.....ት

🔥ክፋል 51
.
.
#የመጨረሻ ክፍል
.
.
ድንገት መካከላቸው ወጣ ገባ ስትል የነበረች አንዲት መኪና አቅጣጫ ቀይራ ከመሀላቸው ስትወጣ ሚኪ ዞሮ መኪናዋን የሚያሽከረክረው መሳይ መሆኑን ሲመለከት በድንጋጤ እየጮኽ
ፅናት መንገድ መንገድ ዘግታ እንድታስቆመው አደረገ። መሳይም በሁኔታው እየተደነባበረ ከመኪናው ወርዶ ሮጦ ከመጣው ሚኪ ጋር ተቃቀፈ። ተያይዘው ወደ አንድ ሆቴል በማምራት እንዴት ነገሮች ተቀይረው ለዚህ እንደበቃ እየጠየቀው በመሀል የፅናት ስልክ ጠራ ። ከቦርሳዋ ውስጥ አውጥታ ተመለከተችው። ፊቷ ተለዋወጠ።
" ይኼ የማያፍር ሰይጣን ደግሞ ስልኬ ይደውላል እንዴ!" ብላ ስልኩን በመዝጋት በንዴት ስትንጨረጨር ከመሳይ ጋር የጀመረውን ጫወታ አቋርጦ•••
"ማነው ፅኑዬ?
" ያ ብሩክ ተብየው ነዋ!"
"ተይው አትበሳጪ ስራው ካንቺ በላይ እኔን ማበሳጨት እንደነበረበት አውቃለሁ። ግን ደነዘዝኩ ባንዱ ጉዳት የተሰበረው ልብሽ ሳይጠገን በጉዳት ላይ ጉዳት ሲደራረብብሽ የመበሳጨትም
አቅም ያጥርሽና ትደነዝዣለሽ። እንደ ብሩኬ አይነት ሰዎች ብዙ ናቸው። ሲበዛ እራስ ወዳዴች ከመሆናቸው የተነሳ አንቺ ችግር ውስጥ ስትገቢ ከዛ ችግር እንድትወጪ ከመርዳት ይልቅ
-በችግርሽ
-በእጦትሽ
-በስጋት እና በፍርሀትሽ
ሁሉ ተጠቅመው አንቺን እንዴት አድርገው ለፍላጎትና ለጥቅማቸው መሳካት እንደሚጠቀምቡሽ ነው የሚያስቡት።
ብሩኬም እንደዚሁ ነው ያደረገው። በምኞት ላይ በፈፀምኩት ክህደትና በደል ከባድ ፀፀት ውስጥ መውደቄን በፀፀት ውስጥ ባገረሸው ፍቅሯ መጎዳቴንና የትም አለች ቢሉኝ እሷን ለማግኘት የማልወጣው ተራራ የማልፈነቅለው ድንጋይ አለመኖሩን ሲረዳ ሰው ቢሆን ኖሮ አጠገቤ ሆኖ ጉዳቴን በተጎዳ። ፍቅሬን ምኞቴን ፀፀቴን እንዳገኛት ከጎኔ ሆኖ በደከመ። ግን እሱ ሰው ቢሆንም
እንደሰው እየኖረ አልነበረምና የኔን መጥፎ አጋጣሚ እራሱን ጠቅሞ እኔን ለመጉዳት ተጠቀመበት አንድ ያለችኝ መፅናኛ እህቴን አንቺን ሊያሳጣኝ ተሯሯጠ። ፈጣሪም ሩጫውን ገታው። ሀሳቡ ሳይሳካ መንገድ ላይ አስቀረው። የኔ ምኞት ግን ጠፍታ አትቀርም!"
አለና እንባ ያቀረሩ አይኖቹን ጨምቆ አቀረቀረ። መሳይ ሚኪ ያወራውን ሲሰማ በተቀመጠበት ልቡ መምታት ያቆመች መሰለው ምድርና ሰማዩ ተገለባበጠበት።
በዛች ቅፅበት ምን እንደሚያወራ ፣ምን እንደሚል፣ ምን ማድረግ እንዳለበት ማወቅ ተሳነው!። ምኞት ታየችው የሚያጣት ሚኪ የሚወስድበት መሰለው። ብድግ ብሎ ወደ ሽንት ቤት ለመሄድ አሰበና ጭንቅላቱ ውስጥ የተፈጠረው ውጥረት፣ፍጭት እና ጩኸት ገና ከወንበሩ ሲነሳ አዙሮ የሚደፋው መሰለውና መነሳቱን አልደፈረም።
እዛው በተቀመጠበት በሁለት እጆቹ ፊቱን ሸፍኖ እሱም እንደሚኪ አቀረቀረ።
መሀላቸው ቁጭ ያለችው ፅናት ብሩክ ሲደውል የተንቀለቀለው ንዴቷ ጠፍቶ በረዶ ሆነች። የሁለቱንም ስሜት በየተራ እየተመለከተች ነበርና ሚኪ ባውራው
ነገር መሳይ ለእብደት የዳረገውን ያለፈ መጥፎ የፍቅር ሂወቱን አስቦ የተረበሸ መሰላት ። "እባክህ ሚኪ እንደዚህ አትሁን እሱንም ረበሽከው እኮ! እባክህ
ተረጋጋ!" ብላው ደሞ ወደ መሳይ ዞራ "ድንገት አግኝተንህ ማሰብ የማትፈልገውን መጥፎ ትዝታህን ስለቀሰቀስንብህ ይቅርታ እባክህ
አትረበሽ። መሳይ ለፅናት መልስም አልሰጣትም። ቀናም አላለም።
ግራ ሲገባት ወደ ሚኪ ተጠግታ ገና ሚኪዬ ብሏ እንደተጣራች ሚኪ ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ድፍት ያለውን መሳይን እየተመለከተ•••
"ከሁሉም ነገር በፊት ትልቅ ይቅርታ እጠይቅሀለሁ መሳይ ወንድሜ! ይቅርታ የምጠይቅህ ግን ዛሬ ስለረበሽኩ ሳይሆን ለቆየ በደሌ ነው። በደሌ ምን እንደሆነና ለምን ይቅር በለኝ እንዳልኩህ ኑዛዜየን ስጨርስ ትረዳዋለህ። "አዋ ዛሬ ትክክለኛው ቀን ነው ከዚህ በፊት ብዙ ግዜ አግኝቼህ ሊሆን ይችላል። ፍቅርህን ናርዶስን ከማጣትህ በፊትም እሷን
አጥተህ ልክ እኔ ዛሬ ቀን እንደጨለመብኝ በቀን ጨለማ ተውጠኽም እንዳገኘሁኽ አስታውሳለሁ። ግን መጎዳትህን አየሁ እንጂ ጉዳትህን አልተጎዳሁትም ነበር።
በፍቅር ህመም ክፉኛ መታመምህን ተመለከትኩ እንጂ ህመምህን አልታመምኩትም ነበር። ካጠገብህ ዘወር ስል እረሳዋለሁ። ያንተ እንደዛ መሆን አይገባኝም፣ አያስጨንቀኝም፣ አይቆረቁረኝም። ዛሬ ግን ሕመምኽን ታምሜዋለሁና ጉዳትህን ተጎድቼዋለሁና ልክ እንዳየሁኽ ስላንተና ስለናርዶስ የማውቀውን ሚስጥር ሳልነግርህ
ማለፍ አልቻልኩም። አቃተኝ። ሚኪ ስለፍቅረኛው ናርዶስ እኔ የማላውቀውን ሚስጥር ይነግረኛል ብሎ አልጠበቀምና ስለምኞት እያሰበ እሱን ከማድመጥ ውጪ ቀናም አላለም።
"መሳይ ወላጅ አባትህ ጓደኛዬ ነው እሱን ይቅር የማለት እና ያለማለት ያንተ ፋንታ ነው ለኔ ግን ሁለቱም ጓደኛቼ አንድ አይነት
ሰይጣኖች ናቸው አባትህ እና ብሩኬ!" አለ። እኼን ግዜ እንኳንስ የመሳይ የፅናት የልብ ትርታ እጥፍ ሆነ ሚኪ ምን ሊያወራ ነው ብላ ሁሉ ነገሯ ስራ ፈትቶ ሚኪ ላይ ተተከለች። መሳይ "ይኼ ሰው ደሞ ምን ሊያሰማኝ ነው ፈጣሪዬ እባክህ የምችልበትን አቅም ስጠኝ። አለ አንገቱን እንደደፋ ፍርሀት ከላይ እስከታች እየናጠው። ሚኪ ቀጠለ••• " አባትህ ከናርዶስ ጋር የነበረኽን የፍቅር ግኑኝነት በጭራሽ አይፈልገውም ነበር።
ይኽን አንተም ታውቀዋለኽ። ናርዶስን ያልፈለጋት ያጠፋችው ወይ ያጎደለችው ነገር ስለነበር አይደለም። ጥፋቷም ጉድለቷም ድሃ መኾኗ : ከድሃ ቤተሰብ መፈጠሯ ብቻ ነበር። በአባትህ አይን ይቺ ያንተ ድሃዋ ናርዶስ እሱ ሊድርህ ለፈለገው ሰው እንዳይድርኽ መዃል የገባች የፍላጎቱ ፀር የእቅዱ ጠንቅ
ነበረች።

ይሄን ግዜ መሳይ ካቀረቀረበት ቀና እለና ሚኪ ላይ አፈጠጠበት ። አይኖቹ ደም ለብሰዋል። ፅናት መሳይን ስትመለከተው ጥርሶቹ እርስ በርሳቸው እየተፋጩ ነው።
ፈራች መሳይ እብደቱ የጀመረው መሰላት "ሚኪ አብደሃል ምንድን ነው የምታወራው ተነስ በቃ እንሂድ !" አለች ብድግ ብላ ቀና ብሎ እየተመለከታት"የትም አልሄድምም! አላበድኩምም!
ያበድኩት ይሄን እውነት እያወቅኩ ሳልቃወም እውነቱን ደብቄ ለመሳይ እብደት ተባባሪ የሆንኩ እለት ነበር ፅናቴ ። እባክሽ አታቋርጭኝ! "ቀጠለ•••
" እናም ይቺን የእቅዱ ጠንቅ የሆነችውን ናርዶስን በዘበኝነት ተቀጥረው እየሰሩ እንደ እናትም እንደ አባትም ሆነው ባሳደጓት በአባቷ መጣባት። ለአቧታ ያላትን ፍቅር ለመግለፅ ቃላት ለሚያጥሯት ናርዶስ ! አባቷን በሸረበው ተንኮል ወንጀል ውስጥ መግባታቸውን መስማት ከባድ ነበር። አባቷ እስር ቤት ገብተው እንዲማቅቁ የማትፈልግ ከሆነ
አንተን እስከመጨረሻው ትታ እሱ ወደ ሚላት ቦታ ጨርቄን ማቄን ሳትል መሄድ እንዳለባት ሲጠይቃት ምርጫ አልነበራትምና ተስማማች። "
መሳይ በዛን ግዜ የነበረው የአባቱ ሁኔታ በሙሉ ፊቱ ተደቀነበት ከእናቱ ሞት ቡሀላ የህይወቱን መራር ለቅሶ እያለቀሰ " እባክህ ወዴት እንደወሰዳት የት እንዳስቀመጣት ንገረኝ ሚኪ!" ፅናትም ሚኪም አብረውት አነቡ። ሚኪ ብድግ ብሎ ወደ መሳይ በመሄድ "እራስህን አረጋጋ መሳይ ወንድሜ ከዚህ ሰአት ቡኻላ በፈለግከው ሰአት ያንተ ናርዶስ ወዳለችበት ልወስድህ ዝግጁ ነኝ!! አንድ ቀን እንዲህ በአጋጣሚ እኔንም የኔ ምኞት ወዳለችበት ቦታ የሚወስደኝ ሰው ይልክልኝ ይሆናል ፈጣሪ !!" አለው።
መሳይ ውስጡ ያለውን የተደበላለቀ ስሜት መረዳት ከበደው ተነስቶ ሚኪን አቅፎት ለሰከንዶች ቆየና ለቆት ወደ ሆቴሉ መታጠቢያ ቤት አመራ ። መታጠቢያ ቤት ገብቶ እራሱን
በመስታወት እየተመለከተ ሚኪ ይቅር በለኝ ምን ማለት እንዳለብኝ እና እንደሌለብኝ መለየት አልቻልኩም ። ለምን ይሆን ስለምኞት

ላንተ ለመንገር አቅም

BY Book store


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/bookstorej/284

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Messages are not fully encrypted by default. That means the company could, in theory, access the content of the messages, or be forced to hand over the data at the request of a government. The account, "War on Fakes," was created on February 24, the same day Russian President Vladimir Putin announced a "special military operation" and troops began invading Ukraine. The page is rife with disinformation, according to The Atlantic Council's Digital Forensic Research Lab, which studies digital extremism and published a report examining the channel. Telegram has gained a reputation as the “secure” communications app in the post-Soviet states, but whenever you make choices about your digital security, it’s important to start by asking yourself, “What exactly am I securing? And who am I securing it from?” These questions should inform your decisions about whether you are using the right tool or platform for your digital security needs. Telegram is certainly not the most secure messaging app on the market right now. Its security model requires users to place a great deal of trust in Telegram’s ability to protect user data. For some users, this may be good enough for now. For others, it may be wiser to move to a different platform for certain kinds of high-risk communications. This provided opportunity to their linked entities to offload their shares at higher prices and make significant profits at the cost of unsuspecting retail investors. It is unclear who runs the account, although Russia's official Ministry of Foreign Affairs Twitter account promoted the Telegram channel on Saturday and claimed it was operated by "a group of experts & journalists."
from ms


Telegram Book store
FROM American