Telegram Group & Telegram Channel
“ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” - የአቶ ክርስቲያን ታደለ ቤተሰብ

ለ1 አመት ከ4 ወራት በእስር ላይ ሆነው ፍትህ እየተጠባበቁ የሚገኙት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አበል አቶ ክርስቲያን ታደለ ከባድ የጤና እከል ስለገጠማቸው በሕይወት እንዲቆዩ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዲጎበኟቸው የቅርብ ቤተሰባቸው አሳሰቡ።

ከፍትህ በፊት በሕይወት መቆየታቸው እንደሚቀድም ገልጸው፣ “ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።

የአቶ ክርስቲያን የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ የጤናው ሁኔታ አሁንም በጣም አሳሰቢ ነው። ሰርጀሪ ተደርጎለት በሰዓታት ልዩነት ነው ወደ ማረሚያ ቤት የተመለሰው። እዛም ሆኖ የደም መፍሰስ አለበት።

ሰኞ እለት ቀጠሮ ስለነበር ሂዶ ነበር የሚፈሰው ደም ምን እንደሆነ ለማወቅ ብለው ደም ወስደዋል። ባለፈው ከአንጀቱ ውስጥ በሰርጀሪ የወጣውንና የተወሰደውን ደም ውጤት ለማወቅ ለነገ ሐሙስ ተቀጥሯል።

ህመም አለው። ‘ከፍተኛ ህመም ነው የሚሰማኝ’ ነው የሚለው። ለጊዜው የሚያስታግስለትን መድኃኒት ነው የሚጠቀመው።

ከዚህ ቀደም አያመውም ነበር። አዋሽ አርባ ከሄደ በኋላ ነው የታመመው። አሁን ሲነግረን አሟቸው ከአዋሽ ወደ አዲስ አበባ አምጥተዋቸው ነበር። የዛኔም ምርመራና በቂ ህክምና አላደረገም። 

የዛኔ አብረዋቸው ከአዋሽ የመጡ አካላት ፕራይቬሲያቸውን በሚጥስ ሁኔታ ‘አብረን ገብተን እንመለከታለን ህክምናውን’ በሚል አለመግባባት ተፈጥሮ ህክምና ሳያገኙ ተመልሱ።

የዛኔ ቢታከም መታጠብ ነበር የሚጠበቅበት ለሰርጀሪም አይደርስም ነበር። ህመሙ በድርቀት የሚመጣ ሲሆን፣  አንጀቱ ውስጥ ሌላ የቋጠረ ነገር ነበር።

እሱንም አሁን ሀኪሞቹ ለማብራራት ቆርጠው ካወጡት በኋላ ለምርመራ ተወስዷል። ነገ ነው ውጤቱ የሚገለጸው።

የፍርድ ሂደቱን በተመለከተ በሚገርም ሁኔታ በጣም ረጅም፣ ረጅም የሆነ ቀጠሮ ነው የሚሰጠው። አሁንም ገና ለጥር 13 ነው ቀጠሮ የተሰጣቸው።
 
እንደ ቤተሰብ ከምንናገረው በላይ እጅግ በጣም ከባድ ነው ያለንበት ሁኔታ። እሱ በነበረበት ወቅት ጥሩ በሚባል ሁኔታ ላይ ነው የነበርነው፣ አሁን ላይ እንደዛ አይደለም።

ፍትህ እንጠብቃለን። ተስፋ አንቆርጥም። ግን አሁን ያለው ሂደት በፍትህ ስርዓቱ ክርስቲያንንም ተስፋ እንዳቆረጠው ነው በተደጋጋሚ የሚነግረን፣ እኛም የምናየው።

የደም መፍሰሱ እንኳ አልቆመለትም በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ነው ያለው። የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ።

በቂ የሆነ ህክምና እንዲያገኝ ያለበትን ሁኔታ ተረድተው የሰብዓዊ መብት አካላት እንዲጎበኙት እንፈልጋለን ”
ሲሉ ተማጽነዋል።

(የአቶ ዮሐንስ ቧ ያለው የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ያቀረቡት እሮሮ በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/92943
Create:
Last Update:

“ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” - የአቶ ክርስቲያን ታደለ ቤተሰብ

ለ1 አመት ከ4 ወራት በእስር ላይ ሆነው ፍትህ እየተጠባበቁ የሚገኙት የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አበል አቶ ክርስቲያን ታደለ ከባድ የጤና እከል ስለገጠማቸው በሕይወት እንዲቆዩ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዲጎበኟቸው የቅርብ ቤተሰባቸው አሳሰቡ።

ከፍትህ በፊት በሕይወት መቆየታቸው እንደሚቀድም ገልጸው፣ “ የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ ” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስበዋል።

የአቶ ክርስቲያን የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?

“ የጤናው ሁኔታ አሁንም በጣም አሳሰቢ ነው። ሰርጀሪ ተደርጎለት በሰዓታት ልዩነት ነው ወደ ማረሚያ ቤት የተመለሰው። እዛም ሆኖ የደም መፍሰስ አለበት።

ሰኞ እለት ቀጠሮ ስለነበር ሂዶ ነበር የሚፈሰው ደም ምን እንደሆነ ለማወቅ ብለው ደም ወስደዋል። ባለፈው ከአንጀቱ ውስጥ በሰርጀሪ የወጣውንና የተወሰደውን ደም ውጤት ለማወቅ ለነገ ሐሙስ ተቀጥሯል።

ህመም አለው። ‘ከፍተኛ ህመም ነው የሚሰማኝ’ ነው የሚለው። ለጊዜው የሚያስታግስለትን መድኃኒት ነው የሚጠቀመው።

ከዚህ ቀደም አያመውም ነበር። አዋሽ አርባ ከሄደ በኋላ ነው የታመመው። አሁን ሲነግረን አሟቸው ከአዋሽ ወደ አዲስ አበባ አምጥተዋቸው ነበር። የዛኔም ምርመራና በቂ ህክምና አላደረገም። 

የዛኔ አብረዋቸው ከአዋሽ የመጡ አካላት ፕራይቬሲያቸውን በሚጥስ ሁኔታ ‘አብረን ገብተን እንመለከታለን ህክምናውን’ በሚል አለመግባባት ተፈጥሮ ህክምና ሳያገኙ ተመልሱ።

የዛኔ ቢታከም መታጠብ ነበር የሚጠበቅበት ለሰርጀሪም አይደርስም ነበር። ህመሙ በድርቀት የሚመጣ ሲሆን፣  አንጀቱ ውስጥ ሌላ የቋጠረ ነገር ነበር።

እሱንም አሁን ሀኪሞቹ ለማብራራት ቆርጠው ካወጡት በኋላ ለምርመራ ተወስዷል። ነገ ነው ውጤቱ የሚገለጸው።

የፍርድ ሂደቱን በተመለከተ በሚገርም ሁኔታ በጣም ረጅም፣ ረጅም የሆነ ቀጠሮ ነው የሚሰጠው። አሁንም ገና ለጥር 13 ነው ቀጠሮ የተሰጣቸው።
 
እንደ ቤተሰብ ከምንናገረው በላይ እጅግ በጣም ከባድ ነው ያለንበት ሁኔታ። እሱ በነበረበት ወቅት ጥሩ በሚባል ሁኔታ ላይ ነው የነበርነው፣ አሁን ላይ እንደዛ አይደለም።

ፍትህ እንጠብቃለን። ተስፋ አንቆርጥም። ግን አሁን ያለው ሂደት በፍትህ ስርዓቱ ክርስቲያንንም ተስፋ እንዳቆረጠው ነው በተደጋጋሚ የሚነግረን፣ እኛም የምናየው።

የደም መፍሰሱ እንኳ አልቆመለትም በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ነው ያለው። የሰብዓዊት መብት ተቋማት ባለበት ቦታ ሂደው ይመልከቱት ቢያንስ መጀመሪያ በሕይወት እንዲቆይ።

በቂ የሆነ ህክምና እንዲያገኝ ያለበትን ሁኔታ ተረድተው የሰብዓዊ መብት አካላት እንዲጎበኙት እንፈልጋለን ”
ሲሉ ተማጽነዋል።

(የአቶ ዮሐንስ ቧ ያለው የቅርብ ቤተሰብ ለቲክቫህ ያቀረቡት እሮሮ በቀጣይ ይቀርባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/92943

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Groups are also not fully encrypted, end-to-end. This includes private groups. Private groups cannot be seen by other Telegram users, but Telegram itself can see the groups and all of the communications that you have in them. All of the same risks and warnings about channels can be applied to groups. Crude oil prices edged higher after tumbling on Thursday, when U.S. West Texas intermediate slid back below $110 per barrel after topping as much as $130 a barrel in recent sessions. Still, gas prices at the pump rose to fresh highs. In this regard, Sebi collaborated with the Telecom Regulatory Authority of India (TRAI) to reduce the vulnerability of the securities market to manipulation through misuse of mass communication medium like bulk SMS. In view of this, the regulator has cautioned investors not to rely on such investment tips / advice received through social media platforms. It has also said investors should exercise utmost caution while taking investment decisions while dealing in the securities market. Also in the latest update is the ability for users to create a unique @username from the Settings page, providing others with an easy way to contact them via Search or their t.me/username link without sharing their phone number.
from ms


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American