Notice: file_put_contents(): Write of 16406 bytes failed with errno=28 No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94839 -
Telegram Group & Telegram Channel
#የሠራተኞችድምጽ🔈

🔴 “ የምናደርገው አጥተን ነው ተማረን በእንባ የወጣነው። 3 ልጆች አሉኝ  በ1,000 ብር ደመወዝ ነው የምተዳደረው፤ አሁን የት እንውደቅ ? ” - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች

➡️ “ ፕሬዚዳንቱ ተስፋ አስቆረጠን። 'እናንተን ዩንቨርሲቲው እንጂ የቀጠራችሁ የመንግስት ሰራተኞች አይደላችሁም' አለን ” - የ1,100 ብር ደሞዝተኛ

እስከ 20 ዓመታት ' አገለገልን ' ያሉ ከ800 በላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምገባና የሌሎች ሠራተኞች " ዩኒቨርሲቲው ከሥራ ሊያሰናብተን ነው " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ስሞታ አሰሙ።

ሠራተኞቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?

አንድ አባት ፥ “ ከ2004 ዓ/ም ጀምሮ ከከተማው ተደራጅቼ በመስተንግዶና ሁለገብ ሥራ ግቢው እንደፈለገ ነው የምሰራው። የአባቶች እግራቸው ተሰብሯል፤ ጥርሳቸው ወልቋል፤ እጃቸው በእሳት ተቃጥሏል ” ብለዋል።

“ የዩኒቨርሲቲ ዋናው ፕሬዚዳንት ‘መንግስት መዋቅር እያስተካከለ ነው። ይህ ሂደት ካለቀ በኋላ ማኀበራትን ሁሉ ያሰናብታል። መንግስት ከዚህ ግቢ አያውቃችሁም’ ብሏል። እንደ አሮጌ እቃ ቆጥረውናልና መፍትሄ የሚሰጠን የህግ አካል መጥቶ ይመልከተን ” ሲሉም ተማጽነዋል።

ልላኛው አባት፣ “ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከ16 ዓመታት በላይ ከባልደረቦቻችን ጋር እንጨት እየፈለጥን እየተሸከምን ብዙ የሥራ ጫና ነበረብን ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ወድቄ ከተሰበርኩ ከአንድ ዓመት በላይ ሆኖኛል፤ ነገር ግን ህክምና አላገኘሁም። ሦስት ልጆች አሉኝ በ1000 ብር ደመወዝ ነው የምንተዳደረው። አሁን የት እንውደቅ ? የት እንግባ ? ” ሲሉም ጠይቀዋል።

ሌላኛው ቅሬታ አቅራቢም፣ “ 9 ቤተሰብ የቤት ኪራይ እየከፈልኩ አስተዳድራለሁ። እኔ ራሴ መማር እፈልጋለሁ። ግን በገንዘብ ማነስ ምክንያት አልቻልኩም። 1,100 ብር ነው የሚከፈለኝ። ይቺን 1100 ብር ታዲያ ወስጄ ምንድን ነው የማደርጋት ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።

ሌላኛዋ እናት፣ “ ለፍተን እየሰራን ቆይተን አሁን ሁለት ፀጉር አብቅለን በሽተኛ ከሆንን በኋላ ጅብ ይብላችሁ ጎዳና ውጡ ተብለናል።  አራት፣ አምስት ወራት የቆዩትን ቋሚ አድርጎ 20 ዓመት በላይ ቆይታ እያለን ምንም አንዳልጠቀምን ተደርገናል ” ብለዋል።

“ 7 ልጆች አሉኝ ደመወዜ 1000 ብር ነች ከሌሎቹ እኩል አድርጉን እኛም ኢትዮጵያዊ ነን፤ አዋጁ ይመለከተናል፤ ይጨምርልን ስላልን ነው ‘ውጡ’ የተባልነው አንዲያውም አረጋውያን ይደገፉ እንጂ ይጣሉ አይባልም ነበር ” ሲሉም ወቅሰዋል።

ሌላኛዋ ቅሬታ አቅራቢ፣ “ 17 ዓመት ከጅብ ጋር እየተጋፋን እንደ ሻማ ቀልጠን አገልግለናል። ደመወዝ ጭማሪ ስንጠይቅ ‘እንዲያውም እስካሁን አገልግላችኋል አንፈልጋችሁም’ ተባልን ” የሚል ወቀሳ አቅርበዋል።

አክለው፣ “ እኔስ ቆሜ በሚዲያ ተናገርሁ ስንቱ ነው እግሩ የተቀደደው! ስንቱ ነው ሰባራ ሆኖ በየቤቱ ያለው። ቋሚ ሰራተኛ አድርጉን አላልንም ደመወዝ ይጨመርልን ነው የኛ ጥያቄ ” ነው ያሉት።

ሌላኛዋ እናት፣ “ ሙሉ 30 ቀናት ነው አፈር ግጠን የምንሰራው። ስንቀጠር 330 ብር ነበር ትንሽ፣ ትንሽ እየተጨመረልን 1100 ደረሰ። በኋላ ይጨመረናል ብለን ስንጠብቅ አዲሱ ፕሬዚዳንት ጭራሽ ተስፋ አስቆረጠን። ‘እናንተን ዩንቨርስቲው ነው እንጂ የቀጠራችሁ የመንግስት ሠራተኞች አይደላችሁም’ አለን ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ዩኒቨርስቲው ትንሽ፣ ትንሽ እየጨመረ ቆይቷል፤ አሁንስ ለምን አይጨምርም? ኑሮ ውድነቱ በኛስ አልጨመረም ወይ? ብለን ስንጠይቅ፥ ‘እናንተን አናወቃችሁም። እንዲያውም ተንሳፋፊ ሰራተኛ ተመድቦ ይሰራል። እናንተን እናስወጣለን ብዙ ስላገለገላችሁ ይበቃችኋል’ አለን ” ብለዋል።

አክለው፣ “ የምናደርገው አጥተን ነው ተማረን በእንባ የወጣነው ” ያሉ ሲሆን፣ ልላኛው አባትም፣ “ ከ2002 ጀምሬ ነው ዩኒቨርሲቲ ላይ በመስተንግዶ የሰራሁት። በሳምንት፤ በሁለት ሳምንታት ህክምና ለልዩ ልዩ ነገሮች ይኖራሉ። ሁሉን ትተን እየሰራን ቆይተናል ” ብለዋል።

“ ልጆች እናስተምራለን፤ የቤት ኪራይ አንከፍላለን በወር 1,100 በቀን 33 ብር እየተከፈለው በዚህ ኑሮ ውድነት ሰው እንዴት ይኖራል? ብለን ጥያቄ ስናቀርብ ‘በኔ በኩል ጨርሻለሁ ወደ ሚመለከተው ሂዱ የምታመጡት ነገር የለም’ ነው ያለን ፕሬዝዳንቱ ” ሲሉም አማረዋል። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቅሬታው ምላሽ ለመጠየቅ ወደ ዩኒቨርሲቲው ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜው ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

(ጥረቱ ይቀጥላል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM



group-telegram.com/tikvahethiopia/94839
Create:
Last Update:

#የሠራተኞችድምጽ🔈

🔴 “ የምናደርገው አጥተን ነው ተማረን በእንባ የወጣነው። 3 ልጆች አሉኝ  በ1,000 ብር ደመወዝ ነው የምተዳደረው፤ አሁን የት እንውደቅ ? ” - የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሠራተኞች

➡️ “ ፕሬዚዳንቱ ተስፋ አስቆረጠን። 'እናንተን ዩንቨርሲቲው እንጂ የቀጠራችሁ የመንግስት ሰራተኞች አይደላችሁም' አለን ” - የ1,100 ብር ደሞዝተኛ

እስከ 20 ዓመታት ' አገለገልን ' ያሉ ከ800 በላይ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምገባና የሌሎች ሠራተኞች " ዩኒቨርሲቲው ከሥራ ሊያሰናብተን ነው " ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ስሞታ አሰሙ።

ሠራተኞቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?

አንድ አባት ፥ “ ከ2004 ዓ/ም ጀምሮ ከከተማው ተደራጅቼ በመስተንግዶና ሁለገብ ሥራ ግቢው እንደፈለገ ነው የምሰራው። የአባቶች እግራቸው ተሰብሯል፤ ጥርሳቸው ወልቋል፤ እጃቸው በእሳት ተቃጥሏል ” ብለዋል።

“ የዩኒቨርሲቲ ዋናው ፕሬዚዳንት ‘መንግስት መዋቅር እያስተካከለ ነው። ይህ ሂደት ካለቀ በኋላ ማኀበራትን ሁሉ ያሰናብታል። መንግስት ከዚህ ግቢ አያውቃችሁም’ ብሏል። እንደ አሮጌ እቃ ቆጥረውናልና መፍትሄ የሚሰጠን የህግ አካል መጥቶ ይመልከተን ” ሲሉም ተማጽነዋል።

ልላኛው አባት፣ “ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከ16 ዓመታት በላይ ከባልደረቦቻችን ጋር እንጨት እየፈለጥን እየተሸከምን ብዙ የሥራ ጫና ነበረብን ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ወድቄ ከተሰበርኩ ከአንድ ዓመት በላይ ሆኖኛል፤ ነገር ግን ህክምና አላገኘሁም። ሦስት ልጆች አሉኝ በ1000 ብር ደመወዝ ነው የምንተዳደረው። አሁን የት እንውደቅ ? የት እንግባ ? ” ሲሉም ጠይቀዋል።

ሌላኛው ቅሬታ አቅራቢም፣ “ 9 ቤተሰብ የቤት ኪራይ እየከፈልኩ አስተዳድራለሁ። እኔ ራሴ መማር እፈልጋለሁ። ግን በገንዘብ ማነስ ምክንያት አልቻልኩም። 1,100 ብር ነው የሚከፈለኝ። ይቺን 1100 ብር ታዲያ ወስጄ ምንድን ነው የማደርጋት ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።

ሌላኛዋ እናት፣ “ ለፍተን እየሰራን ቆይተን አሁን ሁለት ፀጉር አብቅለን በሽተኛ ከሆንን በኋላ ጅብ ይብላችሁ ጎዳና ውጡ ተብለናል።  አራት፣ አምስት ወራት የቆዩትን ቋሚ አድርጎ 20 ዓመት በላይ ቆይታ እያለን ምንም አንዳልጠቀምን ተደርገናል ” ብለዋል።

“ 7 ልጆች አሉኝ ደመወዜ 1000 ብር ነች ከሌሎቹ እኩል አድርጉን እኛም ኢትዮጵያዊ ነን፤ አዋጁ ይመለከተናል፤ ይጨምርልን ስላልን ነው ‘ውጡ’ የተባልነው አንዲያውም አረጋውያን ይደገፉ እንጂ ይጣሉ አይባልም ነበር ” ሲሉም ወቅሰዋል።

ሌላኛዋ ቅሬታ አቅራቢ፣ “ 17 ዓመት ከጅብ ጋር እየተጋፋን እንደ ሻማ ቀልጠን አገልግለናል። ደመወዝ ጭማሪ ስንጠይቅ ‘እንዲያውም እስካሁን አገልግላችኋል አንፈልጋችሁም’ ተባልን ” የሚል ወቀሳ አቅርበዋል።

አክለው፣ “ እኔስ ቆሜ በሚዲያ ተናገርሁ ስንቱ ነው እግሩ የተቀደደው! ስንቱ ነው ሰባራ ሆኖ በየቤቱ ያለው። ቋሚ ሰራተኛ አድርጉን አላልንም ደመወዝ ይጨመርልን ነው የኛ ጥያቄ ” ነው ያሉት።

ሌላኛዋ እናት፣ “ ሙሉ 30 ቀናት ነው አፈር ግጠን የምንሰራው። ስንቀጠር 330 ብር ነበር ትንሽ፣ ትንሽ እየተጨመረልን 1100 ደረሰ። በኋላ ይጨመረናል ብለን ስንጠብቅ አዲሱ ፕሬዚዳንት ጭራሽ ተስፋ አስቆረጠን። ‘እናንተን ዩንቨርስቲው ነው እንጂ የቀጠራችሁ የመንግስት ሠራተኞች አይደላችሁም’ አለን ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ ዩኒቨርስቲው ትንሽ፣ ትንሽ እየጨመረ ቆይቷል፤ አሁንስ ለምን አይጨምርም? ኑሮ ውድነቱ በኛስ አልጨመረም ወይ? ብለን ስንጠይቅ፥ ‘እናንተን አናወቃችሁም። እንዲያውም ተንሳፋፊ ሰራተኛ ተመድቦ ይሰራል። እናንተን እናስወጣለን ብዙ ስላገለገላችሁ ይበቃችኋል’ አለን ” ብለዋል።

አክለው፣ “ የምናደርገው አጥተን ነው ተማረን በእንባ የወጣነው ” ያሉ ሲሆን፣ ልላኛው አባትም፣ “ ከ2002 ጀምሬ ነው ዩኒቨርሲቲ ላይ በመስተንግዶ የሰራሁት። በሳምንት፤ በሁለት ሳምንታት ህክምና ለልዩ ልዩ ነገሮች ይኖራሉ። ሁሉን ትተን እየሰራን ቆይተናል ” ብለዋል።

“ ልጆች እናስተምራለን፤ የቤት ኪራይ አንከፍላለን በወር 1,100 በቀን 33 ብር እየተከፈለው በዚህ ኑሮ ውድነት ሰው እንዴት ይኖራል? ብለን ጥያቄ ስናቀርብ ‘በኔ በኩል ጨርሻለሁ ወደ ሚመለከተው ሂዱ የምታመጡት ነገር የለም’ ነው ያለን ፕሬዝዳንቱ ” ሲሉም አማረዋል። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቅሬታው ምላሽ ለመጠየቅ ወደ ዩኒቨርሲቲው ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜው ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

(ጥረቱ ይቀጥላል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA





Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94839

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

In a statement, the regulator said the search and seizure operation was carried out against seven individuals and one corporate entity at multiple locations in Ahmedabad and Bhavnagar in Gujarat, Neemuch in Madhya Pradesh, Delhi, and Mumbai. Right now the digital security needs of Russians and Ukrainians are very different, and they lead to very different caveats about how to mitigate the risks associated with using Telegram. For Ukrainians in Ukraine, whose physical safety is at risk because they are in a war zone, digital security is probably not their highest priority. They may value access to news and communication with their loved ones over making sure that all of their communications are encrypted in such a manner that they are indecipherable to Telegram, its employees, or governments with court orders. Meanwhile, a completely redesigned attachment menu appears when sending multiple photos or vides. Users can tap "X selected" (X being the number of items) at the top of the panel to preview how the album will look in the chat when it's sent, as well as rearrange or remove selected media. In December 2021, Sebi officials had conducted a search and seizure operation at the premises of certain persons carrying out similar manipulative activities through Telegram channels. Oh no. There’s a certain degree of myth-making around what exactly went on, so take everything that follows lightly. Telegram was originally launched as a side project by the Durov brothers, with Nikolai handling the coding and Pavel as CEO, while both were at VK.
from ms


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American