Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ስድስት

ባሰበችው ቁጥርም ይሄ ንግግሩ ይገርማት ነበር። አሁን ግን ነገሮች እየተገለጡላት መጡ። "አፍቅሮኝ ነበር ማለት ነው" እራሷን ጠየቀች። ለዚህ ነው ወደ ንቅናቄው መግባቴን የተቃወመው? የመጨረሻውን ስብሰባ እንዳትካፈል ያላደረገው ጥረት እንዳልነበር ትዝ አላት። በተኩሱ መሀል መጥቶ ጎትቶ ሲወስዳት  ዐይኑ ላይ ይነበብ የነበረው ፍቅር ከየት እንደመጣ በዛን ጊዜ ለማወቅ ተቸግራ ነበር። ግን ለምን አልነገረኝም? እኮ ለምን? ልቧ በሀዘን ደምቷል።
      ታክሲው ካዛንቺስ ደርሶ ሲቆም ወረደች። የተባለው አድራሻ ጋ ለመድረስ ብዙ ሰአት አልወሰደባትም። አልአዛር ከተባለው ሰው የጥያቄዎቿን መልስ እንደምታገኝ ስለገመተች አድራሻው ላይ የሰፈረውን ቤት ለማግኘት ተቻኮለች። መለስተኛ ሆኖ የተደላደለ ኑሮ ሊኖርበት የሚችልበት ሰፊ ቤት አጠገብ ስትደርስ 'ይሄ መሆን አለበት' አለች በሆዷ። የበሩን መጥሪያ ተጫነችው። የሷን መምጣት በመጠባበቅ ላይ የነበሩ እስከሚመስላት ድረስ በሚያስደንቅ ፍጥነት የቤቱ በር ተከፈተ።
       ከፊት ለፊቷ የቆመውን ሰው ስታይ ደነገጠች።ቁርጥ እዮብን። ልቧ በድንጋጤ ምቷን ጨመረች። እንድትገባ በሩን ወለል አድርጎ ከፈተላት። ምንም ሳታመነታ ወደ ውስጥ ዘለቀች። ጊዜ ሳይፈጅ 'አልአዛር' ብሎ እጁን ለትውውቅ ዘረጋ። 'ብሌን' አለች ነገር ግን ራሷን ማስተዋወቅ አስፈላጊ መስሎ አልታያትም። ወጣቱ ካወቃት የቆየ ይመስላልና።
     አልአዛር ገና ብሌንን እንዳየ የወንድሙ እንደዛ በፍቅር መሰቃየት ተገለጠለት። ማንስ ቢሆን ከዚች ቆንጆ የፍቅር ወጥመድ ያመልጣል ሲል አሰበ። ሰውነቷ በድካምና በዱላ የተጎዳ ስለሚመስል ዛሬ ወንድሙ በአደራ ያስቀመጠውን ወረቀት ቢሰጣት ሊጎዳት ይችላል ብሎ ስለጠረጠረ ወረቀቱን ነገ ሊያሳያት ቀጠሮውን አራዘመ።
      ቤቱ የአንድ ወንድ መኖሪያ ብቻ አይመስልም። በፅዳት ተስተካክላ የተዘጋጀችው ሳሎን የሴት እጅ የግድ ያረፈባት መሆኑን ገመተች። እንደገባች ከፊቷ የነበረው ሶፋ ላይ ተዘረረች። ድካሙና ረሀቡ ተደራርበው አቅም አሳጥተዋታል። የልቧ ሀዘን ደግሞ ይበልጥ ሰውነቷን ጎዳው። "ወንድሙ  ነው?" እንዴት ወንድም እንዳለው ለማንም ሳይናገር ኖረ? ግራ ገብቷት ራሷን ጠየቀች።
      አልአዛር ፈጠን ብሎ የሚበላ አቀረበላት። ምግቡን ከፊት ለፊቷ ቀርቦ ስታየው የረሀብ ስሜቷ ተቀሰቀሰ። በልታ እንደጨረሰች ወጣቱ በአበላል ሁኔታዋ መገረሙ አይቀርም ብላ አሰበች። እሱ ግን የተረዳት ይመስላል።
       ራሷን በድንጋይ እንደተመታ ሰው ይፈልጣታል።መቋቋም እስኪያቅታት ድረስ ህመሙ እየጨመረ ሄደ። የራስ ምታት መድኃኒት ይኖርሃል? አለች ወጣቱን እያየች። ወደ መኝታ ክፍል ሄዶ ሁለት መድኃኒቶችን ይዞ መጣ። ይኸውና የራስ ምታት መድሀኒቱ ብሎ አንዱን ወደ እጇ አቀበላት። "ይሄ ደግሞ የእንቅልፍ ኪኒን ነው።" ብዙ እረፍት ያገኘሽ አትመስዪም አላት ፊቷን እያየ። ብሌን አላንገራገረችም ሁለቱንም መድኃኒቶች ዋጠቻቸው። የእንቅልፍ መድኃኒቱ ለመስራት ጊዜም አልወሰደበትም። ጭንቅላቷን ሶፋው ላይ አስደግፋ ለመተኛት ሞከረች። አልተመቻትም። ወጣቱ ሶፋው ላይ ሙሉ ለሙሉ ወጥታ እንድትተኛ ትራስና ወፍራም ጋቢ ከመኝታ ቤት አምጥቶ ሰጣት። መድኃኒቶቹን  መኝታ ቤት አስቀምጦ እስከሚመለስ እንቅልፍ ወስዷታል።
      ከሶፋው አጠገብ ቆሞ ሶፋው ላይ የተኛችሁን ብሌንን በአድናቆት ይመለከታታል። ሁለመናዋ ልብን ይማርካል። በብዙ ነገር ራሳቸውን አስጊጠው ከሚመለከታቸው ሴቶች ይልቅ በሷ ውስጥ ከጉስቁልናዋ በላይ ጎልቶ የሚታየው አፍዝዞታል። እጁን ዘርግቶ.......
✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/121
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ስድስት

ባሰበችው ቁጥርም ይሄ ንግግሩ ይገርማት ነበር። አሁን ግን ነገሮች እየተገለጡላት መጡ። "አፍቅሮኝ ነበር ማለት ነው" እራሷን ጠየቀች። ለዚህ ነው ወደ ንቅናቄው መግባቴን የተቃወመው? የመጨረሻውን ስብሰባ እንዳትካፈል ያላደረገው ጥረት እንዳልነበር ትዝ አላት። በተኩሱ መሀል መጥቶ ጎትቶ ሲወስዳት  ዐይኑ ላይ ይነበብ የነበረው ፍቅር ከየት እንደመጣ በዛን ጊዜ ለማወቅ ተቸግራ ነበር። ግን ለምን አልነገረኝም? እኮ ለምን? ልቧ በሀዘን ደምቷል።
      ታክሲው ካዛንቺስ ደርሶ ሲቆም ወረደች። የተባለው አድራሻ ጋ ለመድረስ ብዙ ሰአት አልወሰደባትም። አልአዛር ከተባለው ሰው የጥያቄዎቿን መልስ እንደምታገኝ ስለገመተች አድራሻው ላይ የሰፈረውን ቤት ለማግኘት ተቻኮለች። መለስተኛ ሆኖ የተደላደለ ኑሮ ሊኖርበት የሚችልበት ሰፊ ቤት አጠገብ ስትደርስ 'ይሄ መሆን አለበት' አለች በሆዷ። የበሩን መጥሪያ ተጫነችው። የሷን መምጣት በመጠባበቅ ላይ የነበሩ እስከሚመስላት ድረስ በሚያስደንቅ ፍጥነት የቤቱ በር ተከፈተ።
       ከፊት ለፊቷ የቆመውን ሰው ስታይ ደነገጠች።ቁርጥ እዮብን። ልቧ በድንጋጤ ምቷን ጨመረች። እንድትገባ በሩን ወለል አድርጎ ከፈተላት። ምንም ሳታመነታ ወደ ውስጥ ዘለቀች። ጊዜ ሳይፈጅ 'አልአዛር' ብሎ እጁን ለትውውቅ ዘረጋ። 'ብሌን' አለች ነገር ግን ራሷን ማስተዋወቅ አስፈላጊ መስሎ አልታያትም። ወጣቱ ካወቃት የቆየ ይመስላልና።
     አልአዛር ገና ብሌንን እንዳየ የወንድሙ እንደዛ በፍቅር መሰቃየት ተገለጠለት። ማንስ ቢሆን ከዚች ቆንጆ የፍቅር ወጥመድ ያመልጣል ሲል አሰበ። ሰውነቷ በድካምና በዱላ የተጎዳ ስለሚመስል ዛሬ ወንድሙ በአደራ ያስቀመጠውን ወረቀት ቢሰጣት ሊጎዳት ይችላል ብሎ ስለጠረጠረ ወረቀቱን ነገ ሊያሳያት ቀጠሮውን አራዘመ።
      ቤቱ የአንድ ወንድ መኖሪያ ብቻ አይመስልም። በፅዳት ተስተካክላ የተዘጋጀችው ሳሎን የሴት እጅ የግድ ያረፈባት መሆኑን ገመተች። እንደገባች ከፊቷ የነበረው ሶፋ ላይ ተዘረረች። ድካሙና ረሀቡ ተደራርበው አቅም አሳጥተዋታል። የልቧ ሀዘን ደግሞ ይበልጥ ሰውነቷን ጎዳው። "ወንድሙ  ነው?" እንዴት ወንድም እንዳለው ለማንም ሳይናገር ኖረ? ግራ ገብቷት ራሷን ጠየቀች።
      አልአዛር ፈጠን ብሎ የሚበላ አቀረበላት። ምግቡን ከፊት ለፊቷ ቀርቦ ስታየው የረሀብ ስሜቷ ተቀሰቀሰ። በልታ እንደጨረሰች ወጣቱ በአበላል ሁኔታዋ መገረሙ አይቀርም ብላ አሰበች። እሱ ግን የተረዳት ይመስላል።
       ራሷን በድንጋይ እንደተመታ ሰው ይፈልጣታል።መቋቋም እስኪያቅታት ድረስ ህመሙ እየጨመረ ሄደ። የራስ ምታት መድኃኒት ይኖርሃል? አለች ወጣቱን እያየች። ወደ መኝታ ክፍል ሄዶ ሁለት መድኃኒቶችን ይዞ መጣ። ይኸውና የራስ ምታት መድሀኒቱ ብሎ አንዱን ወደ እጇ አቀበላት። "ይሄ ደግሞ የእንቅልፍ ኪኒን ነው።" ብዙ እረፍት ያገኘሽ አትመስዪም አላት ፊቷን እያየ። ብሌን አላንገራገረችም ሁለቱንም መድኃኒቶች ዋጠቻቸው። የእንቅልፍ መድኃኒቱ ለመስራት ጊዜም አልወሰደበትም። ጭንቅላቷን ሶፋው ላይ አስደግፋ ለመተኛት ሞከረች። አልተመቻትም። ወጣቱ ሶፋው ላይ ሙሉ ለሙሉ ወጥታ እንድትተኛ ትራስና ወፍራም ጋቢ ከመኝታ ቤት አምጥቶ ሰጣት። መድኃኒቶቹን  መኝታ ቤት አስቀምጦ እስከሚመለስ እንቅልፍ ወስዷታል።
      ከሶፋው አጠገብ ቆሞ ሶፋው ላይ የተኛችሁን ብሌንን በአድናቆት ይመለከታታል። ሁለመናዋ ልብን ይማርካል። በብዙ ነገር ራሳቸውን አስጊጠው ከሚመለከታቸው ሴቶች ይልቅ በሷ ውስጥ ከጉስቁልናዋ በላይ ጎልቶ የሚታየው አፍዝዞታል። እጁን ዘርግቶ.......
✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM

❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/121

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The account, "War on Fakes," was created on February 24, the same day Russian President Vladimir Putin announced a "special military operation" and troops began invading Ukraine. The page is rife with disinformation, according to The Atlantic Council's Digital Forensic Research Lab, which studies digital extremism and published a report examining the channel. "Your messages about the movement of the enemy through the official chatbot … bring new trophies every day," the government agency tweeted. He said that since his platform does not have the capacity to check all channels, it may restrict some in Russia and Ukraine "for the duration of the conflict," but then reversed course hours later after many users complained that Telegram was an important source of information. And indeed, volatility has been a hallmark of the market environment so far in 2022, with the S&P 500 still down more than 10% for the year-to-date after first sliding into a correction last month. The CBOE Volatility Index, or VIX, has held at a lofty level of more than 30. At this point, however, Durov had already been working on Telegram with his brother, and further planned a mobile-first social network with an explicit focus on anti-censorship. Later in April, he told TechCrunch that he had left Russia and had “no plans to go back,” saying that the nation was currently “incompatible with internet business at the moment.” He added later that he was looking for a country that matched his libertarian ideals to base his next startup.
from ms


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American