Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/tikvahethiopia/-94087-94088-94089-94090-94091-): Failed to open stream: No space left on device in /var/www/group-telegram/post.php on line 50
TIKVAH-ETHIOPIA | Telegram Webview: tikvahethiopia/94090 -
Telegram Group & Telegram Channel
" ተመዝግበንና ክፍያም ከፍለናቸው ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ ባለንበት ዩኒቨርሲቲዉ አላስተምራችሁም ብሎናል " - የሪሚዲያል ተማሪዎች

➡️ " ዉሳኔዉ የትምህርት ሚንስቴ እንጂ የዩኒቨርሲቲው አይደለም " - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ

" የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከሁለት ወራት ፊት በሣምንቱ የዕረፍት ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ባወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት የምዝገባ እና የመማሪያ ክፍያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ እያለን ዩኒቨርሲቲው ሌሎች አማራጮችን መጠቀሚያ ጊዜ ባለፈብን በዚህ ወቅት አላስተምራችሁም ብሎናል " ሲሉ ተማሪዎሽ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

ቅሬታቸዉን ካደረሱን ተማሪዎች መካከል በመደበኛው የትምህርት ሚንስቴር ምደባ ጅግጅጋ ፣ሰላሌ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተመደብዉ እያለ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) በእረፍት ቀናት በክፍያ ለማስተማር ማስታወቂያ ማዉጣቱን ተከትሎ ከቤተሰብ ላለመራቅና በአንዳንድ አከባቢዎች ካለዉ የፀጥታ ችግር የተነሳ ከፍለዉ ለመማር በመወሰን የምዝገባና የትምህርት ክፍያ አጠናቀው የትምህርት መጀመርን ሲጠባበቁ እንደነበር ገልፀዉ ዩኒቨርሲቲዉ " ኃላፊነት በጎደለው መልኩ 'ትምህርት ሚንስቴር በግል ከፍሎ መማርን ስላልፈቀደ ማስተማር የማንችል በመሆኑ ክፍያችሁን መዉሰድ ትችላላችሁ ' ብሎ የለጠፈዉ ማስታወቂያ እጅግ አሳዝኖናል " ብለዋል።

በተመደብንባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች መሄድ በማንችልበትና ሌሎችም በግል ኮሌጆች ከፍለን የመማሪያ ጊዜዉ ካለፈብን በኋላ የተወሰነዉ ይህ ዉሳኔ ከጊዜ እና ገንዘብ ጉልበት ብክነት ባሻገር በስነልቦናም ጉዳት አድርሶብናል ብለዋል።

ተማሪዎቹ ቅሬታቸዉን ለዩኒቨርሲቲዉና በግልባጭ ለትምህርት ሚንስቴርም ማቅረባቸውን ገልፀዉ የሚመለከተዉ አካል አስፈላጊውን መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌን አግኝቶ በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግሯል።

ዶክተር ቅሬታዉ እንደደረሳቸዉና ዩኒቨርሲቲዉ ከዚህ ቀደም እንደሚያደርገዉ ሁሉ " በሣምንቱ መጨረሻ ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለመስጠት ማስታወቂያ ማዉጣቱንና 400 የሚሆኑ ተማሪዎች ተመዝግበው ክፍያ ላጠናቀቁ ተማሪዎች ትምህርት የመጀመር ሂደት ላይ እያለን ትምህርት ሚንስቴር በሰጠዉ ትዕዛዝ መሰረት ማስተማር ስለማንችል ማስታወቂያ ለጥፈናል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዩኒቨርቲዉ ለማስተማር ካለዉ ፍላጎት የተነሳ ተማሪዎችን መዝግቦ ወደ መማር ማስተማር ሂደት በመግባት ሂደት ላይ እንደነበር ያስታወሱት ፕሬዘረዳንቱ የተማሪዎችንና የወላጆችን ቅሬታ ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ትምህርት ሚንስቴር በማቅረብ ሂደት ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

" በሚንስትር መስሪያ ቤቱ ምላሽ ላይ ተመስርተን ' አስተምሩ ' የሚባል ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች የሚገኙ ከሆነ ለተማሪዎቹ ጥሪ እናቀርባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።

ጉዳዩን ተከታትለን ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/94090
Create:
Last Update:

" ተመዝግበንና ክፍያም ከፍለናቸው ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ ባለንበት ዩኒቨርሲቲዉ አላስተምራችሁም ብሎናል " - የሪሚዲያል ተማሪዎች

➡️ " ዉሳኔዉ የትምህርት ሚንስቴ እንጂ የዩኒቨርሲቲው አይደለም " - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ

" የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ከሁለት ወራት ፊት በሣምንቱ የዕረፍት ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ከፍለዉ መማር ለሚፈልጉ ተማሪዎች ባወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት የምዝገባ እና የመማሪያ ክፍያ አጠናቀን ትምህርት በመጀመር ሂደት ላይ እያለን ዩኒቨርሲቲው ሌሎች አማራጮችን መጠቀሚያ ጊዜ ባለፈብን በዚህ ወቅት አላስተምራችሁም ብሎናል " ሲሉ ተማሪዎሽ ቅሬታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድርሰዋል።

ቅሬታቸዉን ካደረሱን ተማሪዎች መካከል በመደበኛው የትምህርት ሚንስቴር ምደባ ጅግጅጋ ፣ሰላሌ እና ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲዎች ተመደብዉ እያለ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) በእረፍት ቀናት በክፍያ ለማስተማር ማስታወቂያ ማዉጣቱን ተከትሎ ከቤተሰብ ላለመራቅና በአንዳንድ አከባቢዎች ካለዉ የፀጥታ ችግር የተነሳ ከፍለዉ ለመማር በመወሰን የምዝገባና የትምህርት ክፍያ አጠናቀው የትምህርት መጀመርን ሲጠባበቁ እንደነበር ገልፀዉ ዩኒቨርሲቲዉ " ኃላፊነት በጎደለው መልኩ 'ትምህርት ሚንስቴር በግል ከፍሎ መማርን ስላልፈቀደ ማስተማር የማንችል በመሆኑ ክፍያችሁን መዉሰድ ትችላላችሁ ' ብሎ የለጠፈዉ ማስታወቂያ እጅግ አሳዝኖናል " ብለዋል።

በተመደብንባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች መሄድ በማንችልበትና ሌሎችም በግል ኮሌጆች ከፍለን የመማሪያ ጊዜዉ ካለፈብን በኋላ የተወሰነዉ ይህ ዉሳኔ ከጊዜ እና ገንዘብ ጉልበት ብክነት ባሻገር በስነልቦናም ጉዳት አድርሶብናል ብለዋል።

ተማሪዎቹ ቅሬታቸዉን ለዩኒቨርሲቲዉና በግልባጭ ለትምህርት ሚንስቴርም ማቅረባቸውን ገልፀዉ የሚመለከተዉ አካል አስፈላጊውን መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጉቼ ጉሌን አግኝቶ በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግሯል።

ዶክተር ቅሬታዉ እንደደረሳቸዉና ዩኒቨርሲቲዉ ከዚህ ቀደም እንደሚያደርገዉ ሁሉ " በሣምንቱ መጨረሻ ቀናት የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ለመስጠት ማስታወቂያ ማዉጣቱንና 400 የሚሆኑ ተማሪዎች ተመዝግበው ክፍያ ላጠናቀቁ ተማሪዎች ትምህርት የመጀመር ሂደት ላይ እያለን ትምህርት ሚንስቴር በሰጠዉ ትዕዛዝ መሰረት ማስተማር ስለማንችል ማስታወቂያ ለጥፈናል " ሲሉ ተናግረዋል።

ዩኒቨርቲዉ ለማስተማር ካለዉ ፍላጎት የተነሳ ተማሪዎችን መዝግቦ ወደ መማር ማስተማር ሂደት በመግባት ሂደት ላይ እንደነበር ያስታወሱት ፕሬዘረዳንቱ የተማሪዎችንና የወላጆችን ቅሬታ ተከትሎ ጉዳዩን ወደ ትምህርት ሚንስቴር በማቅረብ ሂደት ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

" በሚንስትር መስሪያ ቤቱ ምላሽ ላይ ተመስርተን ' አስተምሩ ' የሚባል ተስፋ ሰጪ ጉዳዮች የሚገኙ ከሆነ ለተማሪዎቹ ጥሪ እናቀርባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።

ጉዳዩን ተከታትለን ተጨማሪ መረጃ የምናደርስ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/94090

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

It is unclear who runs the account, although Russia's official Ministry of Foreign Affairs Twitter account promoted the Telegram channel on Saturday and claimed it was operated by "a group of experts & journalists." And indeed, volatility has been a hallmark of the market environment so far in 2022, with the S&P 500 still down more than 10% for the year-to-date after first sliding into a correction last month. The CBOE Volatility Index, or VIX, has held at a lofty level of more than 30. Perpetrators of these scams will create a public group on Telegram to promote these investment packages that are usually accompanied by fake testimonies and sometimes advertised as being Shariah-compliant. Interested investors will be asked to directly message the representatives to begin investing in the various investment packages offered. The Securities and Exchange Board of India (Sebi) had carried out a similar exercise in 2017 in a matter related to circulation of messages through WhatsApp. Founder Pavel Durov says tech is meant to set you free
from nl


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American