Telegram Group & Telegram Channel
🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ሰባት

እጁን ዘርግቶ የተራቆተ እግሯን ሸፈነላት። ምን ነካኝ? አለ ራሱን ቆጣ ብሎ። የተገተረበትን ቦታ ለቆ ወደ መኝታ ቤቱ አመራና አልጋው ላይ ተወረወረ። ጎጃምን ለቆ ሲወጣ የሚያስታውሰው ነገር የለም። በዛን ጊዜ በጣም ልጅ ነበረ። ነገሮች ተረስተውታል። አንድ የማይረሳው ነገር ግን አለ። ታናሽ ወንድሙ እዮብ። በሁለት አመት ውስጥ አከታትላ የወለደቻቸው እናታቸው የ አራት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች እናት ናት። የእድሜ ልዩነታቸው ብዙም ስላይደለ እዮብና አልአዛር መንታ ይመስላሉ።

አባታቸው በእናታቸው ላይ የሚያደርሰውን ግፍ ማየት የሚችልበት ጥንካሬ ስላጣ አንድ ቀን ወንድሙ እዮብን ብቻ ተሰናብቶ ጎጃምን ለቀቀ። ለቀቀ የሚለው ቃል አልአዛር እዚህ ቦታ ለመድረስ ያየው መከራና ጊዜ ባይገልፀውም እንዲሁ ለቀቀ ይባል። የወሰደበት ጊዜ ረጅም ነው ምን አልባትም የእድሜውን እኩሌታ ያህላል።

እዮብ ወደእዚህ አገር ሲመጣ አልአዛር ትንሽ ሱቅ ከፍቶ በመነገድ ላይ ነበር። የስጋ ነገር ሆነና እንደገና ለመገናኘት ዝምድናቸውንም ለማደስ ጊዜ አልፈጀባቸውም። እዮብ አዲስ አበባ ሲመጣ እናታቸው ሆነ አባታቸው ወንድም እህቶቻቸው በወረርሽኝ አልቀው ነበር። ብቻውን የቀረው አንድ እዮብም የተመደበበት ወደነበረው ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ በጎጃም የቀረው አንድም ቤተሰብ የለም። ሁሉም አልቀዋል። ለዚህም ተጠያቂው በምንቸገረኝነት ከዳር ሆኖ ሲመለከት የነበረው መንግስት ለመሆኑ ደምድሟል።

ልቡ በቀልን እንዳረገዘ ዩኒቨርስቲውን ተቀላቀለ። ከአንድ ወር በኃላም በልጅነቱ የተለየውን ወንድሙን አገኘና የብቸኝነቱን ስቃይ መቋቋም ቻለ። የእዮብና የአልአዛር ገበያ ግንኙነት በሚስጥር እንዲሆን ሀሳብ ያቀረበው እዮብ ነበር። አልአዛር ከአገሩ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን ስም ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። "አንተነህ" ምን አይነት አስቀያሚ ስም ነው ሲል አሰበ። ገና አዲስ አበባ እንደገባ ወደ አልአዛር ቀየረ። ወንድማማቾቹ በእረፍት ቀናቸው በድብቅ ተገናኝተው ይወያያሉ። በመካከላቸው የነበረው ፍቅር ጠንካራ ነው። አልአዛር ወሩንና ቀኑን ባያስታውሰውም ብቻ የሆነ ቀን ወንድሙ እዮብ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ወደ እሱ ሲሮጥ ተመለከተ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጉቶ ስለነበር የእዮብ ትንፋሽ መለስ እስኪል ራሱ አልጠበቀም። ምን እንደሆነ ለማወቅ በጥያቄ ያጣድፈው ጀመር።

ፍቅር ይዞኛል! አለው ከእሱ መፍትሔ ያገኝ ይመስል። ታዲያ ምን ችግር አለው? አለ አልአዛር በፍቅር መያዝ እንዲህ ወንድሙን ያስጨነቀበት ምክንያት አልገባሁም። ባክህ አድምጠኝ አለ እዮብ የወንድሙ ቸልታ ቅር አሰኝቶት። የተማሪዎች ህብረት አባል ነኝ። ልጅቷም እንዲሁ አለ እዮብ ከወንድሙ የደበቀውን ሚስጥር ማጋለጡ እያስፈራው።

አልአዛር ስጋቱ እውን ሆኖ ሲያየው የሚያደርገውን አሳጣው። ድሮውኑ የወንድሙን ቆራጥነት ያውቀዋል። የህብረቱ አባል መሆን ማለት ራስን በሸምቀቆ ወደተዘጋጀ ገመድ ማስገባት ማለት ነው። የእዮብን ግትር ውሳኔ ማስቀረት ፍፁም እንደማይቻለው ስለተገነዘበ በሀዘን አንገቱን አቀርቅሮ ዝምታን መረጠ።

አሊ አንድ ነገር በል እንጂ! አለ እዮብ የወንድሙን ዝምታ ጠልቶ። ምን ልበልህ? ራስህን ለሞት አሳልፈህ ስትሰጥ ዳር ሆኖ ከመመልከት ውጪ ምን አይነት ምርጫ አለኝ? አለ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ። ከተል አድርጎም ነግረአታል? አለ አልአዛር ንግግሩ ህይወት አልባ ነበር። አልነገርኳትም ልነግራትም አልፈልግም። የህብረቱ አባል እንዳትሆን ያላዴግኩት ጥረት አልነበረም ሊሳካልኝ አልቻለም እንጂ።

ህብረታችን በቅርቡ በመንግስት ሀይል ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅት አድርጓል። በዚህ ነገር ላይ እንዳትሳተፍ ብፈልግም ቁርጠኛ ሀሳቧን ማስቀየር የማይቻል ነገር ነው። ይህንን ለወንድሙ መንገሩ እፎይታን ሰጥቶታል። አልአዛር ግራ ተጋብቶ ወንድሙ ላይ አሁንም እንዳፈጠጠ ነው። እርዳታ ሲያሻት ወደ አንተ ትመጣለች። ለእኔ ስትል እንዳታሳፍራት። አለ ታላቅ ወንድሙን እያየ። ብሌንን አደራ መስጠቱ አርክቶታል። ፍቅሩ በአስተማማኝ እጆች ላይ ትሆናለች። ይህ ደግሞ ለእሱ ትልቅ ረፍት ነው። የልቡን አውጥቶ መንገር አለመፈለጉ የብሌንን እሺታን አልያም እምቢታን ማወቅ የለመፈለጉ ምክንያት ለአልአዛር አልተገለጠለትም።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ



group-telegram.com/yabsiratesfaye/122
Create:
Last Update:

🛑 ፃማ 🛑

ክፍል ሰባት

እጁን ዘርግቶ የተራቆተ እግሯን ሸፈነላት። ምን ነካኝ? አለ ራሱን ቆጣ ብሎ። የተገተረበትን ቦታ ለቆ ወደ መኝታ ቤቱ አመራና አልጋው ላይ ተወረወረ። ጎጃምን ለቆ ሲወጣ የሚያስታውሰው ነገር የለም። በዛን ጊዜ በጣም ልጅ ነበረ። ነገሮች ተረስተውታል። አንድ የማይረሳው ነገር ግን አለ። ታናሽ ወንድሙ እዮብ። በሁለት አመት ውስጥ አከታትላ የወለደቻቸው እናታቸው የ አራት ወንዶችና የሁለት ሴቶች ልጆች እናት ናት። የእድሜ ልዩነታቸው ብዙም ስላይደለ እዮብና አልአዛር መንታ ይመስላሉ።

አባታቸው በእናታቸው ላይ የሚያደርሰውን ግፍ ማየት የሚችልበት ጥንካሬ ስላጣ አንድ ቀን ወንድሙ እዮብን ብቻ ተሰናብቶ ጎጃምን ለቀቀ። ለቀቀ የሚለው ቃል አልአዛር እዚህ ቦታ ለመድረስ ያየው መከራና ጊዜ ባይገልፀውም እንዲሁ ለቀቀ ይባል። የወሰደበት ጊዜ ረጅም ነው ምን አልባትም የእድሜውን እኩሌታ ያህላል።

እዮብ ወደእዚህ አገር ሲመጣ አልአዛር ትንሽ ሱቅ ከፍቶ በመነገድ ላይ ነበር። የስጋ ነገር ሆነና እንደገና ለመገናኘት ዝምድናቸውንም ለማደስ ጊዜ አልፈጀባቸውም። እዮብ አዲስ አበባ ሲመጣ እናታቸው ሆነ አባታቸው ወንድም እህቶቻቸው በወረርሽኝ አልቀው ነበር። ብቻውን የቀረው አንድ እዮብም የተመደበበት ወደነበረው ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ በጎጃም የቀረው አንድም ቤተሰብ የለም። ሁሉም አልቀዋል። ለዚህም ተጠያቂው በምንቸገረኝነት ከዳር ሆኖ ሲመለከት የነበረው መንግስት ለመሆኑ ደምድሟል።

ልቡ በቀልን እንዳረገዘ ዩኒቨርስቲውን ተቀላቀለ። ከአንድ ወር በኃላም በልጅነቱ የተለየውን ወንድሙን አገኘና የብቸኝነቱን ስቃይ መቋቋም ቻለ። የእዮብና የአልአዛር ገበያ ግንኙነት በሚስጥር እንዲሆን ሀሳብ ያቀረበው እዮብ ነበር። አልአዛር ከአገሩ ከመውጣቱ በፊት የነበረውን ስም ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። "አንተነህ" ምን አይነት አስቀያሚ ስም ነው ሲል አሰበ። ገና አዲስ አበባ እንደገባ ወደ አልአዛር ቀየረ። ወንድማማቾቹ በእረፍት ቀናቸው በድብቅ ተገናኝተው ይወያያሉ። በመካከላቸው የነበረው ፍቅር ጠንካራ ነው። አልአዛር ወሩንና ቀኑን ባያስታውሰውም ብቻ የሆነ ቀን ወንድሙ እዮብ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ ወደ እሱ ሲሮጥ ተመለከተ። ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ጓጉቶ ስለነበር የእዮብ ትንፋሽ መለስ እስኪል ራሱ አልጠበቀም። ምን እንደሆነ ለማወቅ በጥያቄ ያጣድፈው ጀመር።

ፍቅር ይዞኛል! አለው ከእሱ መፍትሔ ያገኝ ይመስል። ታዲያ ምን ችግር አለው? አለ አልአዛር በፍቅር መያዝ እንዲህ ወንድሙን ያስጨነቀበት ምክንያት አልገባሁም። ባክህ አድምጠኝ አለ እዮብ የወንድሙ ቸልታ ቅር አሰኝቶት። የተማሪዎች ህብረት አባል ነኝ። ልጅቷም እንዲሁ አለ እዮብ ከወንድሙ የደበቀውን ሚስጥር ማጋለጡ እያስፈራው።

አልአዛር ስጋቱ እውን ሆኖ ሲያየው የሚያደርገውን አሳጣው። ድሮውኑ የወንድሙን ቆራጥነት ያውቀዋል። የህብረቱ አባል መሆን ማለት ራስን በሸምቀቆ ወደተዘጋጀ ገመድ ማስገባት ማለት ነው። የእዮብን ግትር ውሳኔ ማስቀረት ፍፁም እንደማይቻለው ስለተገነዘበ በሀዘን አንገቱን አቀርቅሮ ዝምታን መረጠ።

አሊ አንድ ነገር በል እንጂ! አለ እዮብ የወንድሙን ዝምታ ጠልቶ። ምን ልበልህ? ራስህን ለሞት አሳልፈህ ስትሰጥ ዳር ሆኖ ከመመልከት ውጪ ምን አይነት ምርጫ አለኝ? አለ ተስፋ በቆረጠ ድምፅ። ከተል አድርጎም ነግረአታል? አለ አልአዛር ንግግሩ ህይወት አልባ ነበር። አልነገርኳትም ልነግራትም አልፈልግም። የህብረቱ አባል እንዳትሆን ያላዴግኩት ጥረት አልነበረም ሊሳካልኝ አልቻለም እንጂ።

ህብረታችን በቅርቡ በመንግስት ሀይል ላይ ጥቃት ለመሰንዘር ዝግጅት አድርጓል። በዚህ ነገር ላይ እንዳትሳተፍ ብፈልግም ቁርጠኛ ሀሳቧን ማስቀየር የማይቻል ነገር ነው። ይህንን ለወንድሙ መንገሩ እፎይታን ሰጥቶታል። አልአዛር ግራ ተጋብቶ ወንድሙ ላይ አሁንም እንዳፈጠጠ ነው። እርዳታ ሲያሻት ወደ አንተ ትመጣለች። ለእኔ ስትል እንዳታሳፍራት። አለ ታላቅ ወንድሙን እያየ። ብሌንን አደራ መስጠቱ አርክቶታል። ፍቅሩ በአስተማማኝ እጆች ላይ ትሆናለች። ይህ ደግሞ ለእሱ ትልቅ ረፍት ነው። የልቡን አውጥቶ መንገር አለመፈለጉ የብሌንን እሺታን አልያም እምቢታን ማወቅ የለመፈለጉ ምክንያት ለአልአዛር አልተገለጠለትም።

✍️✍️✍️✍️ይቀጥላል...
@yabsiratesfaye ለወዳጅ ለዘመዶ ያጋሩ

BY አርያም - ARYAM


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/yabsiratesfaye/122

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The regulator said it has been undertaking several campaigns to educate the investors to be vigilant while taking investment decisions based on stock tips. Ukrainian forces have since put up a strong resistance to the Russian troops amid the war that has left hundreds of Ukrainian civilians, including children, dead, according to the United Nations. Ukrainian and international officials have accused Russia of targeting civilian populations with shelling and bombardments. Under the Sebi Act, the regulator has the power to carry out search and seizure of books, registers, documents including electronics and digital devices from any person associated with the securities market. Emerson Brooking, a disinformation expert at the Atlantic Council's Digital Forensic Research Lab, said: "Back in the Wild West period of content moderation, like 2014 or 2015, maybe they could have gotten away with it, but it stands in marked contrast with how other companies run themselves today." The picture was mixed overseas. Hong Kong’s Hang Seng Index fell 1.6%, under pressure from U.S. regulatory scrutiny on New York-listed Chinese companies. Stocks were more buoyant in Europe, where Frankfurt’s DAX surged 1.4%.
from nl


Telegram አርያም - ARYAM
FROM American