Telegram Group & Telegram Channel
ኃጢአት ምን እንደሆነና ፍፃሜውንም ብታውቅ ትሸሸዋለህ!

ኃጢአት የኀሊናና የመንፈስ ሞት ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ‹‹የኃጢአት ደሞዝ ሞት ነው›› (ሮሜ.፮፥፲፫) ሰው በዚህች በዓለም ውስጥ ሲኖር በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ኃጢአት ይሠራል፤ በመታገስ ኃጢአትን ማሸንፍ አቅቶት ክፉት ሲሠራ ለኃጢአት ይሸነፋል፡፡ ይህም ከልጅነቱ ያርቀዋል፡፡ አዳም ከልጅነቱ ተዋርዶ ከገነት የወጣው ለኃጢአት በመሸነፉ ነበር፡፡ ‹‹ክፉን በመልካም አሸንፉ እንጂ በክፉ አታሸንፉ›› (ሮሜ.፲፪፥፳፩) ከአባቱ ቤት የወጣ ልጅ፣ ከእረኛው የተለየ በግ፣ ባለቤት የሌለው ገንዘብ ነውና ኃጢአተኖች የጠፉ ናቸው፤ ዓለማዊ ሕይወት የሚያሸንፋቸው ይጠፋሉና፤ ‹‹ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም››፡፡ (፩ ዮሐ. ፪፥፲፮)

ኃጢአት የሚሠራ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር መተባበር የለውምና ከፈጣሪው ይርቃል፤ ለዚህም ነው ኃጢአትም ከእግዚብሔር መለየት ነው የተባለው፤ ‹‹ብርሃን ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?፤ ክርስቶስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?›› ( ፪ ቆሮ. ፮፥፲፬-፲፭)

ኃጢአት እግዚብሔርን ማጣትም ነው፤ በኃጢአት የሚኖር ሰው ራሱንና ልቡናውን ከእግዚአብሔር በመለየቱ እግዚአብሔርን ያጣል፤ ‹‹የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል››፤ (ዮሐ.፲፬፥፳፫) ፈጣሪን የማያምን ግን ኃጢአትን አብዝቶ ይሠራል፤ መጥፎ ሥራዎችን የሚሠራ ሰው መንፈስ ቅዱስ ይርቀዋል፤ የመንፈስ ቅዱስንም ሥራ ይቃወማል፡፡ ‹‹ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ›› (ኤፌ.፬፥፴) መንፈስ ቅዱስ በሰው ልቡና ውስጥ ሥራውን ካልሠራ ሰው ንስሓ ሊገባ አይችልም፤ ሰው በኃጢአቱ እንደተጸጸተና ንስሓ እንዲገባ የሚያበረታው መንፈስ ቅዱስ ነውና፡፡ ኃጢአተኛ ሰው የሕይወትን ትርጉም አያውቅም፤ ስለንስሓ ቢነገረው ‹በሕይወቴ እንድደሰት ተውኝ› ይላል፤ ምድራዊና ዓለማዊ ደስታ ሕይወት እንደሆነ ያስባልና፡፡

በኃጢአት ውስጥ የኖረ ሰው ውስጣዊ ሰላም የለውም፤ ‹‹ለክፎዎች ሰላም የላቸውም ይላል እግዚአብሔር›› (ኢሳ. ፵፰፥፳፪) ልቡናውም በጭንቀት ስለሚሞላ ፈሪ ይሆናል፡፡ መጥፎ ባሕርይን ይወርሳል፡፡ አዳም ኃጢአትን በሠራ ጊዜ ከዚያ በፊት ያልነበሩ ሦስት ነገሮችን ገንዘብ አደረገ፤ ፍርሀት፣ ድንጋጤና ሰላም ማጣት፤ ፍርሀት የሥነ ልቡና ሕመምተኛ ያደርጋል፤ ኃጢአት ሕሊናን ያደክማል፡፡ ጻድቃን ግን በሰላም፣ በፍቅርና በድስታ ይኖራሉ፡፡ የመንፈስ ፍሬ ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣ እምነት፣ የውሃት፣ ራስን መግዛት ነውና፤(ገላ. ፭፥፳፪-፳፫)

በዚህ ምድር ስንኖር ሕገ እግዚአብሔርን በመተላለፍ የተነሳ መርገሞች የሚያስከትሉአቸው ቅጣቶች ብዙ ናቸው፡፡ ‹‹የዚህን ሕግ ቃሎች ያደርግ ዘንድ የማያጸና ርጉም ይሁን…››(ዘዳ. ፳፰፥፳፮) ሰው ንስሓ ሳይገባ ለድንገተኛ ሞት ሊዳረግ ይችላል፤ በበሽታ ይቀጣል፤ ረኃብ፣ ቸነፈርና ድኅነት ይበዛበታል፤ በደልም ይደርስበታል፡፡

ሰው ንስሓ ከገባ ከዘለዓለማዊ ቅጣት ይድናል፡፡ ነገር ግን በእግዚአብሔር የተወሰነበትን ምድራዊ ቅጣት መቀበል ይኖርበታል፡፡ ያም የሚወሰነው ከሚሠራው የኃጢአት ዓይነት ነው፡፡ በእርግጥ የኃጢአት ትንሽና ትልቅ የለውም፤ ሆኖም ሰው ዐሥርቱ ትእዛዛትን በተላለፈበት መጠን ይቀጣል፡፡ ከእግዚአብሔር ቁጣ የተነሳ የሚመጣ ቅጣትና በፍትሐ ብሔር ወይም በቤተ ክርስቲያን የሚመጣ ቅጣት ሊቀበል ይቻላል፡፡ ይህም ለተወሰነ ጊዜ ከቅዱስ ቁርባን መከልከና ቤተክርስቲያን እንዳይገባ መከልከል ሊሆን ይችላል፡፡

ኃጢአትን አብዝቶ መሥራት በእግዚአብሔር አርአያና ምሳሌ መሆንን ያስቀራል፤ የኅሊና ነጻነትንና የልቡና ንጽሕናንም ያሳጣል፡፡ ‹‹እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ›› (ዘሌ.፲፩፥፵፬) ኃጢአትን የማይተው፣ እስከዕለተ ሞቱም ንስሓ የማይገባ ሰው ግን የዘላለም ቅጣት ይፈረድበታል፡፡ እግዚአብሔር መሓሪና ምሕረቱም የበዛ እንደሆነ ሁሉ ፍርዱም እውነትና ፍጹም መሆኑን፣ በደልን ይቅር የሚል፣ ኃጢአትንም የማይወድ መሆኑን ማወቅ ይገባል፡፡ ከእግዚአብሔር ቸርነትና ምሕረት አንጻር ፍርዱንና ቅጣቱንም አስቦና ተረድቶ ወደ ንስሓ መመለስ ያስፈልጋል፡፡ ቸርነቱን በመተማመን ጭከናውን መርሳት፣ ምሕረቱንም ተስፋ በማድረግ ፍርዱንም ደግሞ መዘንጋት አይገባም፡፡ ‹‹እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ጭከና ተመልከት፤ጭከናውም በውድቀቱ ላይ ነው፤ በቸርነቱ ግን ጸንተህ ብትኖር የእግዚአብሔር ቸርነት በአንተ ላይ ነው፤ ያለዚያ አንተ ደግሞ ትቆረጣለህ›› (ሮሜ. ፲፩፥፳፪)

እግዚአብሔር እውነተኛ ፈራጅ ነው፤ ፍርዱም በትክክል ነው፤ ንስሓ ገብተን ከፊቱ ብንቆም የእግዚአብሔርን ቸርነት እናያለን፡፡ በግድ የለሽነት የምንኖር ንስሓ የማንገባ ሆነን በፊቱ ብንቆም ደግሞ በጭካኔውና በፈራጅነቱ እግዚአብሔርን እናየዋለን፡፡

የዓለም ፍጻሜ የፍርድ ቀን አስደንጋጭና አስፈሪ ነው፤ ‹‹እነሆ ምድሪቱን ባድማ ሊያደርግ፣ ኃጢአተኞቿንም ከእርሷ ዘንድ ሊያጠፋ ጨካኝ ሆኖ በመዓትና በጽኑ ቁጣ ተሞልቶ የእግዚአብሔር ቀን ይመጣል›› (ኢሳ. ፲፫፥፱) በዚያም ቀን እግዚአብሔር ብቻ ከፍ ከፍ ይላል፡፡ ጣኦቶቻቸውም ሁሉ ፈጽመው ይጠፋሉ፡፡ እግዚአብሔርም ምድርን ያናውጥ ዘንድ በተነሣ ጊዜ ሰዎችን ከማስደንገጡና ከግርማው ክብር የተነሣ ወደ ድንጋይ ዋሻና ወደ ምድር ንቃት ውስጥ ይገባሉ፡፡ (ኢሳ.፪፥፲፯-፳) ፭ኛው የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳም እንዳሉትም ‹‹ኃጢአት ምን እንደሆነና ፍፃውንም ብታውቅ ትሸሸዋለህ››፡፡ ጻድቃን መንግሥተ ሰማያትን ሲወርሱ ኃጥኣን ግን ዘለዓለማዊ ቅጣት ወዳለበት ገሀነመ እሳት ውስጥ ይጣላሉ፡፡ ‹‹እነዚያም ወደ ዘለዓለም ቅጣት፣ ጻድቃን ግን ወደ ዘለዓለም ሕይወት ይሄዳሉ›› (ማቴ.፳፭፥፵፮)

በዚያች በፍርድ ቀን ለቅሶ፤ ዋይታና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል፤ ሆኖም ሁሉም የማይጠቅም ጩኸት ነው፡፡ ጨለማውና የማይጠፋው እሳት እጅግ ከባድና አስፈሪ ነው፡፡ ከባድነቱንም ለመረዳት የሚቻለው ግን የጻድቃንን ሕይወት በማየት፣ በመረዳትና በማወቅ ነው፡፡

ምንጭ፤ የንስሓ ሕይወት መጽሐፍ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ፤ ውርስ ትርጉም ቀሲስ እሸቱ ታደሰ ወንድምአገኘሁ በ፳፻፱ ዓ.ም.

ኃጢአት ምን እንደሆነና ፍፃሜውንም ብታውቅ ትሸሸዋለህ!

ኃጢአት የኀሊናና የመንፈስ ሞት ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ‹‹የኃጢአት ደሞዝ ሞት ነው›› (ሮሜ.፮፥፲፫) ሰው በዚህች በዓለም ውስጥ ሲኖር በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ኃጢአት ይሠራል፤ በመታገስ ኃጢአትን ማሸንፍ አቅቶት ክፉት ሲሠራ ለኃጢአት ይሸነፋል፡፡ ይህም ከልጅነቱ ያርቀዋል፡፡ አዳም ከልጅነቱ ተዋርዶ ከገነት የወጣው ለኃጢአት በመሸነፉ ነበር፡፡ ‹‹ክፉን በመልካም አሸንፉ እንጂ በክፉ አታሸንፉ›› (ሮሜ.፲፪፥፳፩) ከአባቱ ቤት የወጣ ልጅ፣ ከእረኛው የተለየ በግ፣ ባለቤት የሌለው ገንዘብ ነውና ኃጢአተኖች የጠፉ ናቸው፤ ዓለማዊ ሕይወት የሚያሸንፋቸው ይጠፋሉና፤ ‹‹ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም››፡፡ (፩ ዮሐ. ፪፥፲፮)



group-telegram.com/TIBEBnegni/2553
Create:
Last Update:

ኃጢአት ምን እንደሆነና ፍፃሜውንም ብታውቅ ትሸሸዋለህ!

ኃጢአት የኀሊናና የመንፈስ ሞት ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ‹‹የኃጢአት ደሞዝ ሞት ነው›› (ሮሜ.፮፥፲፫) ሰው በዚህች በዓለም ውስጥ ሲኖር በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ኃጢአት ይሠራል፤ በመታገስ ኃጢአትን ማሸንፍ አቅቶት ክፉት ሲሠራ ለኃጢአት ይሸነፋል፡፡ ይህም ከልጅነቱ ያርቀዋል፡፡ አዳም ከልጅነቱ ተዋርዶ ከገነት የወጣው ለኃጢአት በመሸነፉ ነበር፡፡ ‹‹ክፉን በመልካም አሸንፉ እንጂ በክፉ አታሸንፉ›› (ሮሜ.፲፪፥፳፩) ከአባቱ ቤት የወጣ ልጅ፣ ከእረኛው የተለየ በግ፣ ባለቤት የሌለው ገንዘብ ነውና ኃጢአተኖች የጠፉ ናቸው፤ ዓለማዊ ሕይወት የሚያሸንፋቸው ይጠፋሉና፤ ‹‹ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም››፡፡ (፩ ዮሐ. ፪፥፲፮)

ኃጢአት የሚሠራ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር መተባበር የለውምና ከፈጣሪው ይርቃል፤ ለዚህም ነው ኃጢአትም ከእግዚብሔር መለየት ነው የተባለው፤ ‹‹ብርሃን ከጨለማ ጋር ምን ኅብረት አለው?፤ ክርስቶስ ከቤልሆር ጋር ምን መስማማት አለው? ወይስ የሚያምን ከማያምን ጋር ምን ክፍል አለው?›› ( ፪ ቆሮ. ፮፥፲፬-፲፭)

ኃጢአት እግዚብሔርን ማጣትም ነው፤ በኃጢአት የሚኖር ሰው ራሱንና ልቡናውን ከእግዚአብሔር በመለየቱ እግዚአብሔርን ያጣል፤ ‹‹የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል››፤ (ዮሐ.፲፬፥፳፫) ፈጣሪን የማያምን ግን ኃጢአትን አብዝቶ ይሠራል፤ መጥፎ ሥራዎችን የሚሠራ ሰው መንፈስ ቅዱስ ይርቀዋል፤ የመንፈስ ቅዱስንም ሥራ ይቃወማል፡፡ ‹‹ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ›› (ኤፌ.፬፥፴) መንፈስ ቅዱስ በሰው ልቡና ውስጥ ሥራውን ካልሠራ ሰው ንስሓ ሊገባ አይችልም፤ ሰው በኃጢአቱ እንደተጸጸተና ንስሓ እንዲገባ የሚያበረታው መንፈስ ቅዱስ ነውና፡፡ ኃጢአተኛ ሰው የሕይወትን ትርጉም አያውቅም፤ ስለንስሓ ቢነገረው ‹በሕይወቴ እንድደሰት ተውኝ› ይላል፤ ምድራዊና ዓለማዊ ደስታ ሕይወት እንደሆነ ያስባልና፡፡

በኃጢአት ውስጥ የኖረ ሰው ውስጣዊ ሰላም የለውም፤ ‹‹ለክፎዎች ሰላም የላቸውም ይላል እግዚአብሔር›› (ኢሳ. ፵፰፥፳፪) ልቡናውም በጭንቀት ስለሚሞላ ፈሪ ይሆናል፡፡ መጥፎ ባሕርይን ይወርሳል፡፡ አዳም ኃጢአትን በሠራ ጊዜ ከዚያ በፊት ያልነበሩ ሦስት ነገሮችን ገንዘብ አደረገ፤ ፍርሀት፣ ድንጋጤና ሰላም ማጣት፤ ፍርሀት የሥነ ልቡና ሕመምተኛ ያደርጋል፤ ኃጢአት ሕሊናን ያደክማል፡፡ ጻድቃን ግን በሰላም፣ በፍቅርና በድስታ ይኖራሉ፡፡ የመንፈስ ፍሬ ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣ እምነት፣ የውሃት፣ ራስን መግዛት ነውና፤(ገላ. ፭፥፳፪-፳፫)

በዚህ ምድር ስንኖር ሕገ እግዚአብሔርን በመተላለፍ የተነሳ መርገሞች የሚያስከትሉአቸው ቅጣቶች ብዙ ናቸው፡፡ ‹‹የዚህን ሕግ ቃሎች ያደርግ ዘንድ የማያጸና ርጉም ይሁን…››(ዘዳ. ፳፰፥፳፮) ሰው ንስሓ ሳይገባ ለድንገተኛ ሞት ሊዳረግ ይችላል፤ በበሽታ ይቀጣል፤ ረኃብ፣ ቸነፈርና ድኅነት ይበዛበታል፤ በደልም ይደርስበታል፡፡

ሰው ንስሓ ከገባ ከዘለዓለማዊ ቅጣት ይድናል፡፡ ነገር ግን በእግዚአብሔር የተወሰነበትን ምድራዊ ቅጣት መቀበል ይኖርበታል፡፡ ያም የሚወሰነው ከሚሠራው የኃጢአት ዓይነት ነው፡፡ በእርግጥ የኃጢአት ትንሽና ትልቅ የለውም፤ ሆኖም ሰው ዐሥርቱ ትእዛዛትን በተላለፈበት መጠን ይቀጣል፡፡ ከእግዚአብሔር ቁጣ የተነሳ የሚመጣ ቅጣትና በፍትሐ ብሔር ወይም በቤተ ክርስቲያን የሚመጣ ቅጣት ሊቀበል ይቻላል፡፡ ይህም ለተወሰነ ጊዜ ከቅዱስ ቁርባን መከልከና ቤተክርስቲያን እንዳይገባ መከልከል ሊሆን ይችላል፡፡

ኃጢአትን አብዝቶ መሥራት በእግዚአብሔር አርአያና ምሳሌ መሆንን ያስቀራል፤ የኅሊና ነጻነትንና የልቡና ንጽሕናንም ያሳጣል፡፡ ‹‹እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ›› (ዘሌ.፲፩፥፵፬) ኃጢአትን የማይተው፣ እስከዕለተ ሞቱም ንስሓ የማይገባ ሰው ግን የዘላለም ቅጣት ይፈረድበታል፡፡ እግዚአብሔር መሓሪና ምሕረቱም የበዛ እንደሆነ ሁሉ ፍርዱም እውነትና ፍጹም መሆኑን፣ በደልን ይቅር የሚል፣ ኃጢአትንም የማይወድ መሆኑን ማወቅ ይገባል፡፡ ከእግዚአብሔር ቸርነትና ምሕረት አንጻር ፍርዱንና ቅጣቱንም አስቦና ተረድቶ ወደ ንስሓ መመለስ ያስፈልጋል፡፡ ቸርነቱን በመተማመን ጭከናውን መርሳት፣ ምሕረቱንም ተስፋ በማድረግ ፍርዱንም ደግሞ መዘንጋት አይገባም፡፡ ‹‹እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ጭከና ተመልከት፤ጭከናውም በውድቀቱ ላይ ነው፤ በቸርነቱ ግን ጸንተህ ብትኖር የእግዚአብሔር ቸርነት በአንተ ላይ ነው፤ ያለዚያ አንተ ደግሞ ትቆረጣለህ›› (ሮሜ. ፲፩፥፳፪)

እግዚአብሔር እውነተኛ ፈራጅ ነው፤ ፍርዱም በትክክል ነው፤ ንስሓ ገብተን ከፊቱ ብንቆም የእግዚአብሔርን ቸርነት እናያለን፡፡ በግድ የለሽነት የምንኖር ንስሓ የማንገባ ሆነን በፊቱ ብንቆም ደግሞ በጭካኔውና በፈራጅነቱ እግዚአብሔርን እናየዋለን፡፡

የዓለም ፍጻሜ የፍርድ ቀን አስደንጋጭና አስፈሪ ነው፤ ‹‹እነሆ ምድሪቱን ባድማ ሊያደርግ፣ ኃጢአተኞቿንም ከእርሷ ዘንድ ሊያጠፋ ጨካኝ ሆኖ በመዓትና በጽኑ ቁጣ ተሞልቶ የእግዚአብሔር ቀን ይመጣል›› (ኢሳ. ፲፫፥፱) በዚያም ቀን እግዚአብሔር ብቻ ከፍ ከፍ ይላል፡፡ ጣኦቶቻቸውም ሁሉ ፈጽመው ይጠፋሉ፡፡ እግዚአብሔርም ምድርን ያናውጥ ዘንድ በተነሣ ጊዜ ሰዎችን ከማስደንገጡና ከግርማው ክብር የተነሣ ወደ ድንጋይ ዋሻና ወደ ምድር ንቃት ውስጥ ይገባሉ፡፡ (ኢሳ.፪፥፲፯-፳) ፭ኛው የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳም እንዳሉትም ‹‹ኃጢአት ምን እንደሆነና ፍፃውንም ብታውቅ ትሸሸዋለህ››፡፡ ጻድቃን መንግሥተ ሰማያትን ሲወርሱ ኃጥኣን ግን ዘለዓለማዊ ቅጣት ወዳለበት ገሀነመ እሳት ውስጥ ይጣላሉ፡፡ ‹‹እነዚያም ወደ ዘለዓለም ቅጣት፣ ጻድቃን ግን ወደ ዘለዓለም ሕይወት ይሄዳሉ›› (ማቴ.፳፭፥፵፮)

በዚያች በፍርድ ቀን ለቅሶ፤ ዋይታና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል፤ ሆኖም ሁሉም የማይጠቅም ጩኸት ነው፡፡ ጨለማውና የማይጠፋው እሳት እጅግ ከባድና አስፈሪ ነው፡፡ ከባድነቱንም ለመረዳት የሚቻለው ግን የጻድቃንን ሕይወት በማየት፣ በመረዳትና በማወቅ ነው፡፡

ምንጭ፤ የንስሓ ሕይወት መጽሐፍ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ፤ ውርስ ትርጉም ቀሲስ እሸቱ ታደሰ ወንድምአገኘሁ በ፳፻፱ ዓ.ም.

ኃጢአት ምን እንደሆነና ፍፃሜውንም ብታውቅ ትሸሸዋለህ!

ኃጢአት የኀሊናና የመንፈስ ሞት ነው፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዳለው ‹‹የኃጢአት ደሞዝ ሞት ነው›› (ሮሜ.፮፥፲፫) ሰው በዚህች በዓለም ውስጥ ሲኖር በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ኃጢአት ይሠራል፤ በመታገስ ኃጢአትን ማሸንፍ አቅቶት ክፉት ሲሠራ ለኃጢአት ይሸነፋል፡፡ ይህም ከልጅነቱ ያርቀዋል፡፡ አዳም ከልጅነቱ ተዋርዶ ከገነት የወጣው ለኃጢአት በመሸነፉ ነበር፡፡ ‹‹ክፉን በመልካም አሸንፉ እንጂ በክፉ አታሸንፉ›› (ሮሜ.፲፪፥፳፩) ከአባቱ ቤት የወጣ ልጅ፣ ከእረኛው የተለየ በግ፣ ባለቤት የሌለው ገንዘብ ነውና ኃጢአተኖች የጠፉ ናቸው፤ ዓለማዊ ሕይወት የሚያሸንፋቸው ይጠፋሉና፤ ‹‹ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም››፡፡ (፩ ዮሐ. ፪፥፲፮)

BY ሰው መሆን...


Warning: Undefined variable $i in /var/www/group-telegram/post.php on line 260

Share with your friend now:
group-telegram.com/TIBEBnegni/2553

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The account, "War on Fakes," was created on February 24, the same day Russian President Vladimir Putin announced a "special military operation" and troops began invading Ukraine. The page is rife with disinformation, according to The Atlantic Council's Digital Forensic Research Lab, which studies digital extremism and published a report examining the channel. "There are several million Russians who can lift their head up from propaganda and try to look for other sources, and I'd say that most look for it on Telegram," he said. The Security Service of Ukraine said in a tweet that it was able to effectively target Russian convoys near Kyiv because of messages sent to an official Telegram bot account called "STOP Russian War." So, uh, whenever I hear about Telegram, it’s always in relation to something bad. What gives? The perpetrators use various names to carry out the investment scams. They may also impersonate or clone licensed capital market intermediaries by using the names, logos, credentials, websites and other details of the legitimate entities to promote the illegal schemes.
from pl


Telegram ሰው መሆን...
FROM American