Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#የአእላፋትዝማሬ #TheMelodyofMyriads “ ኦርቶዶክሳዊያን ወጣቶች ልደትን በቤተ ክርስቲያን አሳልፉ ፤ በአዲስ አበባና በድሬዳዋ የምትገኙም በዝማሬው ላይ እንድትገኙ ” - የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ (ኢጃት) ታኅሳስ 29 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረውን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያው ጃንደረባ ትውልድ ያዘጋጀው “ልደትን በባለ ልደቱ ቤት” የተሰኘውን የአእላፍ…
#የአእላፋትዝማሬ #TheMelodyofMyriads

በዓልን በማይገባ ቦታ የሚያሳልፉ በእግዚአብሔር ቤት ሆነው እንዲያሳልፉ ለማድረግ ዓላማ ያለው የአእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads መርሐግብር ዛሬ ሰኞ በገና ዋዜማ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ይከናወናል።

ቦታው ፦
👉አዲስ አባባ ፦ ቦሌ በድብረ ሳሌም መድኃኔዓለም
👉 ድሬዳዋ ፦ ለገሀር አደባባይ


ከነዚህ ከተሞች ውጭ በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ / ኢጃት አማካኝነት  የተዘጋጀት የአእላፋት ዝማሬ መርሐግብር የሌለ ቢሆንም ሁሉም ምእመናን ፣ ኦርቶዶክሳዊያን ሁሉ በዓሉን ቤተክርስቲያን እንዲያሳልፉት ጥሪ ቀርቧል።

በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ምእመናን ከዝማሬው በፊት ልክ 10:00 ሰዓት ላይ ተገኝተው የአንድ ሰዓት ጸሎተ የምሕላና ጸሎተ ኪዳን ላይ እንዲሳተፉ አደራ ተብሏል።

የዘንድሮው የአእላፋት ዝማሬ ከአምናው በተለየ ጥራት ለማካሄድ በየትኛውም ቦታ የቆመ ሰው የሚሰማው ድምጽ ሆነ የሚያየው ምስል እኩል እንዲሆን ጥረት ተደርጓል።

ለነፍሰ ጡሮች  እና የአካል ጉዳተኞች ልዩ ስፍራ የተዘጋጀ ሲሆን ለአስተባባሪዎች በመንገር ቦታ ማግኘት ይቻላል።

የጤና እክል ለሚያጋጥማቸው ተንቀሳቃሽ ክሊኒኮች አሉ።

የመኪና ማቆሚያን በተመለከተ በቤተክርስቲያን ቅፅጽረ ግቢ ሆነ አስፋልት ዳር መኪና ማቆም ተከልክሏል። መኪና ማቆም የሚቻለው ከህንጻዎቹ ጀርባ ነው።

መኪና ያላችሁ መርሐግብሩ ሲጠናቀቅ ወደናተ አቅጣጫ የሚሄዱትን በመጫን የትራንስፖርት ሰርቪስ እንድትሰጡ አደራ ተብሏል።

ወደ መርሐግብሩ የምትመጡ ነጭ ልብስ አድርጋችሁ እንድትመጡ ያንን ማድረግ ያልቻላችሁ ያላችሁን ልብስ ንጹህ አድርጋችሁ እንድትመጡ ጥሪ ቀርቧል።

በቂ ከበሮ ስለተዘጋጀ ከበሮ ይዞ መምጣት አያስፈልግም።

ቦሌ መድኃኔዓለም በጊብሰን በኩል ያለው በር ለቅዱስ ፓትርያርኩና ለሊቃነ ጳጳሳት መግቢያ ስለሆነ ምእመናን ሌሎች በሮችን እንዲጠቀሙ ተብሏል።

ድሬዳዋ ምድር ባቡር አደባባይ የሚያስገቡትን 5 በሮች መጠቀም ይቻላል።

በመርሐግብሩ በቂ ጥበቃ የተመደበ ሲሆን ፍተሻም ይኖራል።

ምን ይዞ መገኘት / መግባት አይቻልም ?

መሳሪያዎች
ተቀጣጣይ ነገሮች
የግል ካሜራ ፣ ድሮን
ሽቶና ስፕሬይ
ኮስሞቲክስ
ክብሪት
ስክሪብቶና የሾሉ ነገሮች
የግል ከበሮ ይዞ መምጣት ክልክል ነው።


ወደ አእላፋት ዝማሬ የሚመጡ ምዕመናን እስከ 10 ጧፍ ይዘው እንዲመጡ ጥሪ ቀርቧል።

ሦስቱ ጧፎች የአእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads / እስኪጠናቀቅ የሚበሩ ሲሆን የቀሩትን ለደብሩ በመባ መልክ ያስረክቡ። በደብሩ በኩልም ለገጠር አብያተ ክርስትያናት ድጋፍ ይደረጋል ተብሏል።

NB. የዕለቱን ሁነት የሚቀርጹ ፣ በቀጥታም የሚያስተላልፉ መገናኛ ብዙሃን ስላሉ ምእመናን በዝማሬና ምስጋና ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

' ልደቱን በባለ ልደቱ ቤት ! '
#TheMelodyofMyriads


#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93482
Create:
Last Update:

#የአእላፋትዝማሬ #TheMelodyofMyriads

በዓልን በማይገባ ቦታ የሚያሳልፉ በእግዚአብሔር ቤት ሆነው እንዲያሳልፉ ለማድረግ ዓላማ ያለው የአእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads መርሐግብር ዛሬ ሰኞ በገና ዋዜማ በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ይከናወናል።

ቦታው ፦
👉አዲስ አባባ ፦ ቦሌ በድብረ ሳሌም መድኃኔዓለም
👉 ድሬዳዋ ፦ ለገሀር አደባባይ


ከነዚህ ከተሞች ውጭ በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ / ኢጃት አማካኝነት  የተዘጋጀት የአእላፋት ዝማሬ መርሐግብር የሌለ ቢሆንም ሁሉም ምእመናን ፣ ኦርቶዶክሳዊያን ሁሉ በዓሉን ቤተክርስቲያን እንዲያሳልፉት ጥሪ ቀርቧል።

በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ምእመናን ከዝማሬው በፊት ልክ 10:00 ሰዓት ላይ ተገኝተው የአንድ ሰዓት ጸሎተ የምሕላና ጸሎተ ኪዳን ላይ እንዲሳተፉ አደራ ተብሏል።

የዘንድሮው የአእላፋት ዝማሬ ከአምናው በተለየ ጥራት ለማካሄድ በየትኛውም ቦታ የቆመ ሰው የሚሰማው ድምጽ ሆነ የሚያየው ምስል እኩል እንዲሆን ጥረት ተደርጓል።

ለነፍሰ ጡሮች  እና የአካል ጉዳተኞች ልዩ ስፍራ የተዘጋጀ ሲሆን ለአስተባባሪዎች በመንገር ቦታ ማግኘት ይቻላል።

የጤና እክል ለሚያጋጥማቸው ተንቀሳቃሽ ክሊኒኮች አሉ።

የመኪና ማቆሚያን በተመለከተ በቤተክርስቲያን ቅፅጽረ ግቢ ሆነ አስፋልት ዳር መኪና ማቆም ተከልክሏል። መኪና ማቆም የሚቻለው ከህንጻዎቹ ጀርባ ነው።

መኪና ያላችሁ መርሐግብሩ ሲጠናቀቅ ወደናተ አቅጣጫ የሚሄዱትን በመጫን የትራንስፖርት ሰርቪስ እንድትሰጡ አደራ ተብሏል።

ወደ መርሐግብሩ የምትመጡ ነጭ ልብስ አድርጋችሁ እንድትመጡ ያንን ማድረግ ያልቻላችሁ ያላችሁን ልብስ ንጹህ አድርጋችሁ እንድትመጡ ጥሪ ቀርቧል።

በቂ ከበሮ ስለተዘጋጀ ከበሮ ይዞ መምጣት አያስፈልግም።

ቦሌ መድኃኔዓለም በጊብሰን በኩል ያለው በር ለቅዱስ ፓትርያርኩና ለሊቃነ ጳጳሳት መግቢያ ስለሆነ ምእመናን ሌሎች በሮችን እንዲጠቀሙ ተብሏል።

ድሬዳዋ ምድር ባቡር አደባባይ የሚያስገቡትን 5 በሮች መጠቀም ይቻላል።

በመርሐግብሩ በቂ ጥበቃ የተመደበ ሲሆን ፍተሻም ይኖራል።

ምን ይዞ መገኘት / መግባት አይቻልም ?

መሳሪያዎች
ተቀጣጣይ ነገሮች
የግል ካሜራ ፣ ድሮን
ሽቶና ስፕሬይ
ኮስሞቲክስ
ክብሪት
ስክሪብቶና የሾሉ ነገሮች
የግል ከበሮ ይዞ መምጣት ክልክል ነው።


ወደ አእላፋት ዝማሬ የሚመጡ ምዕመናን እስከ 10 ጧፍ ይዘው እንዲመጡ ጥሪ ቀርቧል።

ሦስቱ ጧፎች የአእላፋት ዝማሬ / The Melody of Myriads / እስኪጠናቀቅ የሚበሩ ሲሆን የቀሩትን ለደብሩ በመባ መልክ ያስረክቡ። በደብሩ በኩልም ለገጠር አብያተ ክርስትያናት ድጋፍ ይደረጋል ተብሏል።

NB. የዕለቱን ሁነት የሚቀርጹ ፣ በቀጥታም የሚያስተላልፉ መገናኛ ብዙሃን ስላሉ ምእመናን በዝማሬና ምስጋና ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

' ልደቱን በባለ ልደቱ ቤት ! '
#TheMelodyofMyriads


#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93482

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The original Telegram channel has expanded into a web of accounts for different locations, including specific pages made for individual Russian cities. There's also an English-language website, which states it is owned by the people who run the Telegram channels. Telegram, which does little policing of its content, has also became a hub for Russian propaganda and misinformation. Many pro-Kremlin channels have become popular, alongside accounts of journalists and other independent observers. "Someone posing as a Ukrainian citizen just joins the chat and starts spreading misinformation, or gathers data, like the location of shelters," Tsekhanovska said, noting how false messages have urged Ukrainians to turn off their phones at a specific time of night, citing cybersafety. But Telegram says people want to keep their chat history when they get a new phone, and they like having a data backup that will sync their chats across multiple devices. And that is why they let people choose whether they want their messages to be encrypted or not. When not turned on, though, chats are stored on Telegram's services, which are scattered throughout the world. But it has "disclosed 0 bytes of user data to third parties, including governments," Telegram states on its website. Also in the latest update is the ability for users to create a unique @username from the Settings page, providing others with an easy way to contact them via Search or their t.me/username link without sharing their phone number.
from pl


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American