Telegram Group & Telegram Channel
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF : ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል። ምርጫ ቦርድ ፤ ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አስታውሷል። ፖርቲው ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ…
#TPLF

" የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " - በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ

በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ከጥር 5 እስከ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ አተኩሮ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።

ይህንን ተከትሎ ዛሬ ምሽት መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም ቡድኑ ፦
- እስከ አሁን ያልተረጋገጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት፤
- ተፈናቃዮች እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው አለመመለስ፤
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያወጣውን መግለጫ፤
- የፕሪቶሪያ የሰላም ውል አፈፃፀም በሚሉ አጀንዳዎች ላይ መወያየቱን ገልጾ " ቀጣይ የመፍትሄ እና የትግል አቅጣጫ አስቀምጫለሁ " ብሏል።

የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ ፤ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት እውቅና የሰጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት አለመረጋገጡ ጠቅሶ " ተፈናቃይ እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው ሃዘን እና ቁጣ ተስምተኞናል ይህንን አስመልክቶ ' ይበቃል ' በሚል የተካሄደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ እደግፋለሁ " ብሏል።

ቡድኑ በመግለጫው " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ እንዳይፈፀም የኢትዮጵያ መንግስት እንቅፋት እየሆነ ነው ፡ በትግራይ ውስጥ የበቀለ #ከሃዲ_ሃይልም በተጨማሪ ስምምነቱ እያደናቀፈ ነው " የሚል ክስ አሰምቷል።

እንዴት እንደሆነ ባያብራራም " ችግሩ ከስር መሰረቱ ለመለወጥ ቆርጬ ተነስቻለሁ " ብሏል።

በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ DDR ተቀባይነት ያለው እንደሆነ የገለፀም ሲሆን " ይሁን እንጂ DDR እንደምክንያት በመጠቀም የትግራይ ሰራዊት ለማፍረስ እየተደረገ ያለው ሴራ ተቀባይነተ የለውም " ሲል ገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ህወሓት ህጋዊ ጉባኤ እንዲያካሂድ በማስመልከት በቅርቡ ያወጣው ቀን ገደብ ያካተተ መግለጫ አስመልክቶ በሰጠው ምላሽ ፥ " ቦርዱ ' ጉባኤ አካሂዱ ' የሚል ጨምሮ በተንኮል የተተበተቡ የተለያዩ  ትእዛዞች ከመስጠት ተቆጥቦ የተፈጠሩ ልዩነቶች  በፓለቲካዊ ውይይት ለመፍታት የተጀመረው ጥረት በማስቀጠሉ ላይ ያተኩር "  ብሏል።

" ህወሓት ሁሌም ለሁለትዮሽ ውይይት ዝግጁ ነው ፤ የትግራይ ህዝብ ትግል እና መስዋእትነት የሚያራክስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔ ግን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " ሲል አቋሙን አንጸባርቋል።

ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደሩ በማቋቋም የአንበሳ ድርሻ እንደነበረው እና እንዳለው የጠቀሰው መግለጫው " አሁንም እንዲጠናከር ይሰራል ይሁን እንጂ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማጠናከር እና ለመቆጣጠር በሚል ይቋቋማል የሚባለው ካውንስል አካል መሆን አልፈግም " ሲል ግልፅ አድርጓል።

በሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ በመግለጫው ማጠቃለያ ፤ " የኢትዮጵያ መንግስት ከጣልቃ ገብነት ተቆጥቦ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በቅን ልቦና በመፈፀም ለዘላቂ ሰላም እንዲሰራ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል። 

የህወሓት ቡድን ለሁለት ተከፍሎ የለየለት አለመግባባት ውስጥ ከገባ ወራት የተቆጠሩ ሲሆን ከወራት በፊት ለሁለት የተከፈሉት አመራሮች እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች አዲስ አበባ ሄደው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት አድርገው ነበር።

ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ግን እስከ ዛሬ መግባባት ሳይፈጥሩ በመግላጫ ምልልስ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ደግሞ ህወሓት በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን በመግለጽ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑንም ገልጾ ነበር።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም። በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia



group-telegram.com/tikvahethiopia/93809
Create:
Last Update:

#TPLF

" የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " - በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ

በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ከጥር 5 እስከ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ አተኩሮ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።

ይህንን ተከትሎ ዛሬ ምሽት መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም ቡድኑ ፦
- እስከ አሁን ያልተረጋገጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት፤
- ተፈናቃዮች እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው አለመመለስ፤
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያወጣውን መግለጫ፤
- የፕሪቶሪያ የሰላም ውል አፈፃፀም በሚሉ አጀንዳዎች ላይ መወያየቱን ገልጾ " ቀጣይ የመፍትሄ እና የትግል አቅጣጫ አስቀምጫለሁ " ብሏል።

የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ ፤ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት እውቅና የሰጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት አለመረጋገጡ ጠቅሶ " ተፈናቃይ እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው ሃዘን እና ቁጣ ተስምተኞናል ይህንን አስመልክቶ ' ይበቃል ' በሚል የተካሄደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ እደግፋለሁ " ብሏል።

ቡድኑ በመግለጫው " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ እንዳይፈፀም የኢትዮጵያ መንግስት እንቅፋት እየሆነ ነው ፡ በትግራይ ውስጥ የበቀለ #ከሃዲ_ሃይልም በተጨማሪ ስምምነቱ እያደናቀፈ ነው " የሚል ክስ አሰምቷል።

እንዴት እንደሆነ ባያብራራም " ችግሩ ከስር መሰረቱ ለመለወጥ ቆርጬ ተነስቻለሁ " ብሏል።

በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ DDR ተቀባይነት ያለው እንደሆነ የገለፀም ሲሆን " ይሁን እንጂ DDR እንደምክንያት በመጠቀም የትግራይ ሰራዊት ለማፍረስ እየተደረገ ያለው ሴራ ተቀባይነተ የለውም " ሲል ገልጿል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ህወሓት ህጋዊ ጉባኤ እንዲያካሂድ በማስመልከት በቅርቡ ያወጣው ቀን ገደብ ያካተተ መግለጫ አስመልክቶ በሰጠው ምላሽ ፥ " ቦርዱ ' ጉባኤ አካሂዱ ' የሚል ጨምሮ በተንኮል የተተበተቡ የተለያዩ  ትእዛዞች ከመስጠት ተቆጥቦ የተፈጠሩ ልዩነቶች  በፓለቲካዊ ውይይት ለመፍታት የተጀመረው ጥረት በማስቀጠሉ ላይ ያተኩር "  ብሏል።

" ህወሓት ሁሌም ለሁለትዮሽ ውይይት ዝግጁ ነው ፤ የትግራይ ህዝብ ትግል እና መስዋእትነት የሚያራክስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔ ግን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " ሲል አቋሙን አንጸባርቋል።

ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደሩ በማቋቋም የአንበሳ ድርሻ እንደነበረው እና እንዳለው የጠቀሰው መግለጫው " አሁንም እንዲጠናከር ይሰራል ይሁን እንጂ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማጠናከር እና ለመቆጣጠር በሚል ይቋቋማል የሚባለው ካውንስል አካል መሆን አልፈግም " ሲል ግልፅ አድርጓል።

በሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ በመግለጫው ማጠቃለያ ፤ " የኢትዮጵያ መንግስት ከጣልቃ ገብነት ተቆጥቦ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በቅን ልቦና በመፈፀም ለዘላቂ ሰላም እንዲሰራ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል። 

የህወሓት ቡድን ለሁለት ተከፍሎ የለየለት አለመግባባት ውስጥ ከገባ ወራት የተቆጠሩ ሲሆን ከወራት በፊት ለሁለት የተከፈሉት አመራሮች እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች አዲስ አበባ ሄደው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት አድርገው ነበር።

ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ግን እስከ ዛሬ መግባባት ሳይፈጥሩ በመግላጫ ምልልስ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ደግሞ ህወሓት በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን በመግለጽ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ አሳስቧል።

ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑንም ገልጾ ነበር።

ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም። በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia

BY TIKVAH-ETHIOPIA








Share with your friend now:
group-telegram.com/tikvahethiopia/93809

View MORE
Open in Telegram


Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The SC urges the public to refer to the SC’s I nvestor Alert List before investing. The list contains details of unauthorised websites, investment products, companies and individuals. Members of the public who suspect that they have been approached by unauthorised firms or individuals offering schemes that promise unrealistic returns "This time we received the coordinates of enemy vehicles marked 'V' in Kyiv region," it added. DFR Lab sent the image through Microsoft Azure's Face Verification program and found that it was "highly unlikely" that the person in the second photo was the same as the first woman. The fact-checker Logically AI also found the claim to be false. The woman, Olena Kurilo, was also captured in a video after the airstrike and shown to have the injuries. In the United States, Telegram's lower public profile has helped it mostly avoid high level scrutiny from Congress, but it has not gone unnoticed. 'Wild West'
from pl


Telegram TIKVAH-ETHIOPIA
FROM American